Thursday, August 1, 2013

ዜና በጨዋታ፤ ኢትዮጵያ 2ኛ ወጣች… በሩጫ አይደለም!

Ethiopia_shaded_relief_map_1999,_CIAዜና በጨዋታ፤ ኢትዮጵያ 2ኛ ወጣች… በሩጫ አይደለም!

ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት ተርታ መሆኗ ይታወቃል፡፡ ከአፍሪካ ብቻ ደግሞ እንዳይመስለን ከአለምም ፈጣን እድገት እስመዘገቡ ካሉ ግንባር ቀደሞቹ ውስጥ ናት፡፡ ከዚህ አርፍተ ነገር ጋር ልንጋጭ ነው… ልንጋጭ ነው…. ቀበትዎትን ያጥብቁ ራስዎን ያዘጋጁ….
ኢትዮጵያ በምድር ላይ ካሉ ደሀ ሀገሮች ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡





በዚህ ዝርዝር ውስጥ የሚገኙት ሀገሮች በሙሉ አፍሪካዊ ሀገሮች ሲሆኑ ሱማሌ እንኳ ከአቅሟ ስድስተኛ ሆና፤ ባለ ፈጣን እድገቷ ኢትዮጵያ እንደ አትሌቲክስ ሩጫው ሁሉ በድህነት ሩጫም የሚደርስባት ሳይገኝ ሁለተኛ መውጣቷ የሃያ ሁለት አመት ልፋታችን ውጤት ነው ሲሉ አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የለመኑን ባለስልጣን ጠቅሰዋል፡፡ ወሬው የተገኘው ዘ አፍሪካን ኢኮኖሚስት ከተባለ ድረ ገጽ ነው፡፡



ቆይማ እንደውም ከአንድ እስከ አስር ያለውን ዝርዝራቸውን ኮፒ ፔስት ላድርግልዎ…
  1. Niger
  2. Ethiopia
  3. Mali
  4. Burkina Faso
  5. Burundi
  6. Somalia
  7. Central African Republic
  8. Liberia
  9. Guinea
  10. Sierra Leone
ከዚህ በፊት ከአለም ጠቅላይ ሚኒስተሮች ሶስተኛው ሃብታም እርሳቸው መሆናቸውን፣ እንዲሁም በቅርቡ ከአለም ጠቅላይ ሚኒስትር ሴት ልጆች ደግሞ የእርሳቸው ልጅ አንደኛ ሳትሆን እንደማትቀር መዘገባችን እና መጠርጠራችን ይታወቃል፡፡
አሁንም እንላለን፤ እንኳንም ሁላችንም ተያይዘን ደሃ አልሆንን፡፡ የሀብታም ሀገራት ባልስልጣኖች ልብ ካላቸው፤ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እስመዘገቡ ካሉት ባለስልጣኖቻችን እና ከልጆቻቸው ጋር ጋር ይፎካከሩ!

የሥላሴዎች እርግማን፤ (አንድ) አዳክሞ ማደህየት


August 1, 2013

መስፍን ወልደ ማርያም
ፋክት መጽሔት
አዳክሞ ማደህየት የወያኔ ትልቅና ዋና መሣሪያ ሆኖ አገልግሎአል፤ ወያኔ ከኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አርባ ያህል መምህራንን ያስወጣው ገና በጠዋቱ ነበር፤ ከቴሌ ከመብራት ኃይልና ከባንክ ሰዎችን እየመነጠረ ያስወጣው በዘር አመካኝቶ ቢሆንም በትምህርታቸውና በልምዳቸው የጠጠሩበትን ሰዎች እንደሆነ ሁሉም የሚያውቀው ነው፤ እንደፐሮፌሰር ዓሥራት ያለውን በሁለት የታወቁ የእንግሊዝ ዩኒቨርሲቲዎች የተመሰከረለትን ሰው በችሎታ ማነስ ብሎ ማስወጣት ችሎታ ያነሰው ማን አንደሆነ የሚያውቅ ያውቀዋል፤ እነዚህን የተለያዩ ባለሙያዎች በማስወጣት ወያኔ ሰዎቹን አልጎዳም፤ ሁሉም የተሻለ ኑሮና የተሻለ የሥራ እርካታ አግኝተዋል፤ የተጎዱት መሥሪያ ቤቶቹ ናቸው፤ ከወያኔ ጋር ወደኋላ የሄደችው ኢትዮጵያ ነች፤ ወደኋላ የሄደው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው።
Prof. Mesfin Woldemariam
Prof. Mesfin Woldemariam
በመሬት ያየነው እንደሆነ የወልቃይት-ጸገዴና የራያ-ቆቦ ድንበር ለትግራይ በሚጠቅም መልኩ ቢለወጥና ጎንደርንና ወሎን ቢያስቀይምም አዲስ የመሬት ድልድልን ፈጥሮአል፤ ከመሬቱም ጋር የ‹‹አማራ›› ሕዝብ ቁጥር እንዲቀንስ ሆኖአል፤ ይህ ሁሉ ማዳከም አይሆንም? አዳክሞ ማደህየት አይሆንም? ምርጥ የአገሪቱ መሬት ለውጭ አገር ባለሀብቶች በቸርነት የሚቸበቸበው ገበሬውን ለማዳከምና ወደኩሊነት ለመለወጥ አይደለም? ወደኩሊነት በመለወጥ የራሱን ዕድል በራሱ በመወሰን ፋንታ ሌላ ሰው፣ ምናልባትም ባዕድ ይወስንለታል፤ ከዚህ የበለጠ አዳክሞ ማደህየት ምን አለ?
አንድን ሕዝብ ካዳከሙ በኋላ ማደህየቱ በጣም ቀላል ነው፤ ደርግ ባያውቅበትም በማርክሳዊ-ሌኒናዊ ሰይፍ ደሀዎችን ከደሀነት ለማውጣት ሞክሮ ነበር፤ የደርግ ችግር ደሀዎችን ከደሀነት ለማውጣት ሀብታሞቹን በጠመንጃ ማደህየት ግዴታ አድርጎ መከተሉ ነበር፤ መሬት የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት ነው ብሎ አላቆመም፤ ወይም በባለቤቱ በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም መሬትን ለውጭ አገር ሰዎች አልቸበቸበም፤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ አደላደለ፤ የቤት ኪራይን ቀነሰ፤ በኅብረት ቤት ለመሥራት ለሚፈልጉ ሁሉ መሬቱንም ሆነ ገንዘቡን በቀላሉ የሚያገኙበት ሥርዓትን አመቻቸ፤ ብዙ ሰዎች ቤት ለመሥራት ቻሉ፤ ደርግ በጠመንጃ ደሀነትን ለማጥፋት ሲሞክር ሀብታሞች መቃብሩን ቆፈሩለት፤ ወያኔ ደግሞ ሀብታምነትን በጠመንጃ ለመትከልና ደሀነትንም በጠመንጃ ከአገር ለማስወጣት ሰፊ እቅድ አውጥቶ እየሠራበት ነው፤ ወያኔ መሬት የግል የሚሆነው በመቃብራችን ላይ ነው በማለት ተንብዮ ነበር፤ ትንቢቱ ከደረሰ ቀባሪዎቹ ደሀዎች ሳይሆኑ አይቀሩም።
ወያኔ ሕገ መንግሥቱን አሳምሮ የመደራጀት መብትን ከሥራ ውጭ በማድረግ የሠራተኞች ማኅበርን፣ የመምህራን ማኅበርን፣ የነጻ ጋዜጠኞች ማኅበርን፤ የገበሬ ማኅበርንና ሌሎችንም በቁጥጥሩ ስር አደረጋቸው፤ አዳከማቸው ማለት ነው፤ እነዚህ ሁሉ ማኅበሮች ዛሬ ነጻ ህልውና የሌላቸው፣ ነፍስ የሌላቸው አካሎች ናቸው ለማለት ይቻላል፤ የሴቶች ማኅበርና የወጣቶች ማኅበር የሚባሉትም ሁኔታቸው ያው ነው፤ የተለያዩ የማኅበረሰብ ድርጅቶችም እንደእድር ያሉ ባህላዊ የሆኑትም ጭምር ወይ በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ ወይ ከሥራ ውጭ ሆነዋል፤ የፖሊቲካ ፓርቲዎችና ነጻ ጋዜጦች አሜሪካ በሽብርተኛነት ላይ ጦርነትን እስቲያውጅ ድረስ አሜሪካንን ለማባበያ ጠቅመው ነበር፤ ኢትዮጵያ የአሜሪካ ረዳት ሆና በሽብርተኞች ላይ በሚደረገው ጦርነት ላይ ከአሜሪካ ጋር መሰለፍ ስትጀምር የኢትዮጵያ የፖሊቲካ ፓርቲዎችና ነጻ ጋዜጦች የአሜሪካን የይስሙላ ድጋፍም ማጣት ጀመሩ፤ ከዚህ ጋር ተያይዞም የፖሊቲካ ፓርቲዎችና ነጻ ጋዜጦች አፈና በከፋ መልኩ ተጀመረ፡፡
በሃይማኖት በኩል ያየነው እንደሆነ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በቁጥጥር ስር የዋለችው ገና ከመጀመሪያው ነው ለማለት ይቻላል፤ እንዲያውም በቅርቡ የቀድሞው የወያኔ መሪ እንደተናገረው የወያኔ ተዋጊዎችን መነኮሳት እያስመሰሉ በየገዳሞቹ ሰግስገው እንደነበረ አውቀናል፤ ስብሐት ነጋም ጳጳሳቱ ውስጥ ‹‹አንድም ሰው የለም፤ ቢገኝ አንዲሸለም አደርጋለሁ፤›› ብሎ በአደባባይ ሲናገር ቆብ ጭነው በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሰፈሩት ሁሉ ከመምህራን ማኅበርና ከሠራተኞች ማኅበር ሹሞች የማይሻሉ መሆናቸውን በተደጋጋሚ አስመስክረዋል፤ አሁንም በመንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ላይ የሚፈጽሙት የሚያሳየው የመንፈሳዊ አባቶችን ጠባይ ሳይሆን የጉልበተኞችን ማንአለብኝነት ነው፤
ለካህናትሰ ሰመዮሙ ጼወ፤ ወዓዲ ለካህናትሰ ሰመዮሙ ማኅቶተ፤ ካዕበ ሰመዮሙ ብርሃኖ ለዓለም፤ ወካዕበ ሰመዮሙ ጸሐየ ዘያበርህ ጽልመተ እንዘ ክርስቶስ ጸሐየ ጽድቅ ውስተ አልባቢሆሙ፤ ወካህንሰ ዘቦቱ ልቦና ይገሥጾ ለንጉሥ በእንተ ምግባራት ዘርእየ፤ … ክብረ ነገሥት
ይህንን ትእዛዝ ለመፈጸም ቃል ኪዳን የገባ ሰው ማንም ቢሆን ጥፋት ሲሠራ ከተመለከተ ‹‹ስደትንም ሆነ ሰይፍን ሳትፈራ›› ተቆጣው የተባለና ሥልጣን የተሰጠው ካህን እንዲያውም የጥፋቱ ተሳታፊ ሲሆን ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስን ተልእኮ ማስተላለፍ አትችልም፤ በዚህም ምክንያት መሳለቂያ እየሆነች በሌሎች ባልተሻሉ ቤተ ክርስቲያኖች እየተገፋች ነው።
በእስልምናውም በኩል መንፈሳዊ መሪ ነጥሮ ሊወጣ አልተቻለም፤ ምእመናኑም እምነታቸውን እነሱ በፈለጉት መንገድ ለማስተናገድ ባለመቻላቸው ለመብታቸው ሲታገሉ ዓመት አለፋቸው፤ አሁንም እየታገሉ ነው፤ በእስልምናውና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በኩል ያለው ቸግር ተመሳሳይነት ቢኖረውም የእስልምና ምእመናኑ በትግል ጥንካሬ በጣም ልቀው ሄደዋል፤ የትግሉ አካሄድ ግን እንቅፋቶች እያጋጠሙት በመሆኑ ጠመዝማዛ የሚሆን ይመስላል።
ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት በጎሣ ላይ አተኩሮ የነበረው የኢትዮጵያ ሕዝብ መከፋፈል በአጠቃላይ ሲታይ ያልተከፋፈለበት ነገር የለም፤ የሁለተኛ ደረጃን ትምህርት በጣም አዳክሞ የስም ዩኒቨርሲቲዎችን በቁጥር የበዙ በማስመሰል ትምህርትን ማዳከሙ ዋናና መሠረታዊ ነው፤ ከዚህ ጋር ተያይዞም በማናቸውም ዓይነት ማኅበራዊ ጉዳይ በነጻነት መደራጀትን አንቆ በመቆጣጠር ሕዝቡ መፈናፈኛ እንዳያገኝ አድርጎት ቆየ፤ ሌላውን ሁሉ መንገድ መቆጣጠሩ ከሞላ-ጎደል የተሳካ መሰለ፤ አሁን መጨረሻው ላይ የሃይማኖት ጉዳይ ከረር እያለ መጣ፤ ሰው ከሰው ጋር ያለውን ግንኙነት ለሃያ አንድ ዓመታት በማሻከርና በማዳከም ከፍተኛ ጉዳትን አደረሰ፤ አሁን ደግሞ ሰዎች ከፈጣሪ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማሻከርና ለማዳከም ቀድሞ የተጀመረው የቁጥጥር ጥረት አይሎ በአደባባይ ወጣ፤ በዚህ ጊዜ እንዳጋጣሚም ለወጉም ቢሆን ሃይማኖት ያለው ሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ወንበር ላይ ተቀመጠ፤ ክብረ ነገሥት ‹‹እግዚአብሔርን ፈሪና አስተዋይ ካልሆነ አለቃ ይሆን ዘንድ አይገባውም፤›› ይላል።
በአገር ውስጥ ያለውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከላይ በአጭሩና በአጠቃላይ እንደተገለጸው ከታትፈው በቁጥጥራቸው ስር አድርገው እያሹ አዳከመው አልጋ ላይ ካዋሉት በኋላ ስደተኛውን እየመለመሉ በመሬትና በተለያዩ መደለያዎች እያባበሉ እየተስገበገበና እየተክለፈለፈ የሚገብርላቸውን አገኙ፤ እንዲህም ስደተኛውን በቤተ ክርስቲያን ሳይቀር ከፋፍለው አዳከሙት፤ የተዳከመ አይታገልም፤ ቢታገልም አያሸንፍም።
የተሸነፈንና የተዳከመን ሁሉ በኩርኩም ማደህየቱ ቀላል ነው፤ ነገር ግን ሁሉም ተከታትፎ ለመሸነፍና ለመደህየት የበቃው በወያኔ ኩርኩም ብቻ ሳይሆን በራሱ ስግብግብነትም ጭምር ነው፤ የሥላሴዎች እርግማን!

Wednesday, July 31, 2013

UN staff in Ethiopia helicopter crash

July 31, 2013
Addis Ababa – Officials say a helicopter carrying UN personnel aboard has crash-landed in Ethiopia and that some of them were injured.

helicopter crashed on Wednesday in the town of Debre Zeit
Dina Mufti, the spokesman for Ethiopia’s Ministry of Foreign Affairs, told The Associated Press that the helicopter crashed on Wednesday in the town of Debre Zeit, about 50 kilometers (30 miles) outside Addis Ababa.
Dina said there were multiple injuries but he did not immediately have further details.
However, the state-run news agency reported that the Ethiopian Civil Aviation Authority said two Russian-made helicopters were traveling from Djibouti to Addis Ababa on a U.N. mission. It said one helicopter crashed with four people on board, including two pilots. The helicopters were scheduled to stop in Addis Ababa on their way to Juba, South Sudan.
Source: AP

Tuesday, July 30, 2013

Ethiopian High Court’s Institutional capacity, bleak: Clients


ESAT News
July 30, 2013
 Clients of the Ethiopian High Court have said that the institutional capacity of the court is at a critical state. They said the Court has moved down both in quality and capacity terms. They also said that the current High Court has been worse than the former regime’s Kebele Courts.
The Ethiopian High Court deals with financial and material cases and at times also courts criminal cases. The Court has no proper sanitation and electric generators that serve when power blackouts occur affecting the legal processes.
Some of the other problems that the clients stated are: giving verdict before evidences were sufficiently gathered, cancelling impounding orders and helping suspects to sell their properties and flee, selecting and removing files from charge files, some staffers of the Court, who also act as brokers, influencing judges on their decisions, failure of judges to pay attention and seriously  read charge files, and attempting to establish contact with clients involved in cases that involve huge sums of money.  Judges have also complained that they are given too many cases and files to handle and stated that they sought the Administration to appoint additional human resource.
In related news, it has been leant that a serious problem is being observed in the purchase of land in Addis Abeba. Many people that have purchased and retained a map have found themselves in conflict with other people that presented similar rights of possession.

Monday, July 15, 2013

Ethiopian opposition holds rare protests in Gonder and Dessie


July 14, 2013

ADDIS ABABA (AFP) – Ethiopian opposition activists on Sunday demanded the release of journalists and political prisoners jailed under anti-terror legislation in demonstrations in two major towns.
Ethiopian opposition activists on Sunday demanded the release of journalists
In rare public outpours of anger, people marched peacefully in the towns of Gondar and Dessie, chanting “freedom” and carrying pictures of jailed politicians and journalists.
Government officials said there were around 1,500 protesters in total in both towns, while the activists themselves claimed the number to be as high as 20,000.
“The protests were peaceful and successful,” said Senegas Gidada, protest organiser and chairman of the Unity for Democracy and Justice Party (UDJ) party.
“We are unhappy about the lack of human rights and democratic freedom in Ethiopia,” he added.
The demonstrations follow a rally last month in the capital Addis Ababa when several thousand activists demanded the government adhere to basic human rights.
The recent rallies are the largest since post-election violence in 2005 resulted in 200 people being killed and 30,000 arrested.
“The cost of living is too high. We have no rights. They took away my family’s property and land and gave us no compensation,” said one young unemployed protester, who asked not be named, but who was speaking by telephone from Gondar.
“The dogs on the street have more freedom than we do. We are here to demand freedom and we will continue to protest until the government makes fundamental changes.”
But the government dismissed the protesters’ calls.
“The protesters are demanding the release of prisoners who have been convicted of terrorism, these are not pro-democracy protests,” government spokesman Shemeles Kemal told AFP.
“Most of these demonstrators are Islamic extremists. The government is not concerned by these demonstrations. They are meddling in religious issues and mixing them with political matters.”
The government had allowed the protests to go ahead despite earlier saying they had not received official permission.
Protesters have said they will continue to demonstrate until the government addresses their grievances.
Journalists, opposition members and religious leaders have been jailed under Ethiopia’s 2009 anti-terrorism legislation, which rights groups say is used by the government to stifle peaceful dissent.
Ethiopian journalist, Eskinder Nega, and UDJ Vice-Chairman, Andualem Arage, were both jailed last year under the government’s anti-terror legislation for treason and conspiring to commit acts of terror.
Read more: http://www.foxnews.com/world/2013/07/14/ethiopian-opposition-holds-rare-protests/#ixzz2Z3YXotSp

Sunday, July 14, 2013

አንድነት ፓርቲ በጎንደር እና ደሴ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በድምቀት ተካሄደ



(ECADF) – ሰሞኑን የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት በጎንደርና ደሴ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ሲያስተላልፉና ቅስቀሳ ሲያደርጉ ነው የከረሙት። ሂደቱ በራሱ ከፍተኛ ትግል የተካሄደበት ነበር፣ አባላቱ ሲታሰሩ ሲፈቱ ከርመዋል፣ በደሴ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አመራር አባላት በቀን ውስጥ ሁለት ጊዜ ታስረው ተፈተዋል። ኢህአዴግ/ወያኔ ሰልፉን በቀጥታ ለማገድ ከሞሞከር አንስቶ መላ ካድሬዎቹን አሰማርቶ ህዝቡ አንድነት በጠራው ሰልፍ ላይ እንዳይገኝ ሲያግባባና ሲያስፈራራ ሰንብቶ ነው ሰልፉ የተጠራበት ቀን ሀምሌ 7 እንዳይደርስ የለም የደረሰው።
ፖሊሱና የፖለቲካ ካደሬው አንድ አካል ሆነው በሚኖሩበት ኢትዮጵያ ህዝብን ከአደጋ እንዲከላከል ከህዝብ በሚሰበሰብ ገንዘብ ደሞዝ ተቆርጦለት የተሰማራው የፖሊስ ሀይል ያለምንም እፍረት የካድሬ ስራ ያከናውናል።
በጎንደር ሰላማዊ ሰልፈኛው የሚጓዝባቸው ጎዳናዎች መጋቢ መንገዶች በፌደራል ፖሊሶች ተዘግተው ውለዋል፣ አላማቸው በተቻለ መጠን የሰላማዊ ሰልፈኛውን ቁጥር መቀነስ ነበር። ይሁንና የጎንደር ህዝብ መንገዶችን እያሳበረ፣ የሚጥለው ዝናብና መንገድ የዘጋው የፌደራል ፖሊስ ሳይበግረው ሰልፉን ተቀላቅሏል።


ብቸኛው ተቃዋሚ የፓርላማ አባል አቶ ግርማ ሴይፉ የተገኙበትና ንግግርም ያደረጉበት ስልፍ ደግሞ በደሴ ሞቅ ባለ ሁኔታ ተካሂዷል።
በደሴ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ኢህአዴግ ተቃዋሚዎች አባይ እንዳይገደብ ይፈልጋሉ… በሚል የሚረጨውን ፕሮፓጋንዳ ያመከነ ንግግሮች አድርገዋል።
አቶ ግርማ ሴይፉ “ኢህአዴግ በካድሬዎቹ አማካኝነት ነጻነታችንን ቀምቷል ነጻነታችንን ማስመለስና ወደፊትም እንዳይወሰድብን መከላከል ይኖርብናል” ብለዋል… አቶ ግርማ አያይዘውም “…የሚያሳዝነው ነገር ነጻነታችንን የሚቀሙን ካድሬዎች ለራሳቸውም ነጻነት የላቸውም…” ብለዋል።
በጎንደር እና ደሴ የተደረጉትን የሰላማዊ ሰልፎች የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎች መወያያ መድረክ (ECADF Paltalk room) በቀጥታ በዓለም ዙሪያ ላሉ ኢትዮጵያውያን ሲያስተላልፍ ውሏል።
protest in Gonder, Ethiopia
Andenet protest in Gonder, Ethiopia












Saturday, July 13, 2013

Forum says its application for demo refused

ESAT News   July 12, 2013 
Forum for Democratic Dialogue in Ethiopia (Medrek), an opposition political coalition founded in 2008, has stated that its application to the Addis Abeba City Administration for the recognition of the mass demonstration that it planned to hold from Sidest Kilo to Dilachen Statue in Addis Abeba on July 14, 2013 has been refused.

The Administration in its response to the party said “The road that you plan to walk through during your protest is congested due to the ongoing light railway construction. Therefore, you cannot hold the demonstration on the stated road and time.”

The Addis Abeba City Administration further said at the moment the only free roads available were Piassa and Churchill and the road that has been chosen by the Forum for the demonstration was the only leeway that is available at the moment, thus considering the presence of hospitals and governmental organizations on this same road, the application was rebuffed.

Professor Beyene Petros confirmed that the City Administration has refused their application.