Thursday, June 5, 2014

ጅቡቲን ውሃ ጠማት አለ /TPLF/

ሔለን ንጉሴ/ከኖርዌ

ገዢው ፓርቲ ወያኔ ጅቡቲን ውሃ ጠማት እሷን ከሚጠማት እኛን ይጥማን በሚል ይመስላል ጅቡቲ የኢትዮጵያ ድንበር አቋርጣ ሐገር ውስጥ ድረስ ገብታ ከድሬደዋ ሰባት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሽንሌ የከርሰምድር ንፁህ ውሃ በነፃ አውጥታ እንድትጠጣ መሬት ለመስጠት የሚያስችል ረቂቅ ወጥቶ በምክር ቤት ለውይይት የቀረበ መሆኑ ተሰማ። የራስዋ ሲያርባት የሰው ታማስላለች ይላሉ ይሄ ነው! ህዝባችን መቼ ውሃ ጠጣና ነው ለጎረቤት ማሰብ የተጀመረው ምላሹን ለራሳችን እንተወውና

በሐገራችን ቁጥር አንድ ችግር የውሃ እጥረት መሆኑ እየታወቀ ህዝብ በውሃ እጥረት ምክንያት ከፍተኛ ችግር ውስጥ መውደቁንና ውሃ በመሃል አዲስ አበባ ከተማ ሳይቀር በመጥፋቱ ዜጎች ውሃ ፍለጋ ከሰፈር ሰፈር እየተንከራተቱ መሆኑንና ህዝባችን በውሃ ችግር እየተሰቃየ እያለ ይህንን ችግር መፍታት አቅቷቸው ጅቡቲን ውሃ ጠማት የጅቡቲ ህዝብ የንፁህ ውሃ መጠጥ ያስፈልገዋል ብለው በምክር ቤት ውይይት መጀመራቸው እጅግ በጣም ያስገርማል። ወያኔ መሬት ቆርሶ ለጅቡቲ ውሃ ትጠጣ ብሎ ለሰላሳ አመታት የሚቆይ ኮንትራት ፈርሞ እንደሚሰጥ የቀረበው እረቂቅ የሚገልፅ ቢሆንም በአንፃሩ ኢትዮጵያ ይህንን መሬት በመስጠቷ በምትኩ የምታገኘው ጥቅም እንዳለ ቢጠየቅም ምላሹ የፓለቲካ ጥቅም እንዳለው ብቻ ከመናገር ውጪ ዝርዝሩን ለምክር ቤቱ ማስረዳት አልቻሉም። ጅቡቲ ይህንን መሬት ከኢትዮጵያ ለሰላሳ አመት ኮንትራት ወስዳ ህዝቦችዋን ንፁህ ውሃ ስታጠጣ ጅቡቲን ውሃ ለማጠጣት ከስፍራው የሚፈናቀሉ ዜጎቻችንስ እጣ ፋንታ ምን ሊሆን እንደሚችል ሁላችንም መገመት እንችላለን በየቦታው በልማት ሰበብ ከተፈናቀሉት ካለፉት ተፈናቃዮች ተሞክሮ አለንና በከፍተኛ ሁኔታ ሊታሰብበት ይገባል።

  
ጅቡቲ እንደሚታወው ከወደብ ኪራይ ከኢትዮጵያ በአመት አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር እንደምታገኝ ይታወቃል። ከዚህ በተጨማሪም በሐገራችን በከተሞች ሳይቀር የመብራት እጥረት  በከፍተኛ ሁኔት እየታየ ባለበት ሁኔታ ጅቡቲ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ታገኛለች። ኢትዮጵያ ከጅቡቲ የምታገኘው ምንም አይነት ጥቅም ሳይኖር ለምን የጅቡቲ ጉዳይ እንዲህ እንዳሳሰባትና ወያኔ በዚህ ዙሪያ ያለው ድብቅ የፓለቲካ አጀንዳ ምን እንደሆነ በግልፅ ባያሳውቀንም መገመት ግን እንችላለን። በሌላ መልኩ ወያኔ በማንአለብኝነት ሐገሪቷን እየሸነሸነ መሸጡን መቀጠሉን እያሳየን ነው ትላንት 17 ቀበሌዎችን ለሱዳን አሳልፎ በመስጠቱ የተፈናቀሉ ዜጎች ምን ያህል እንደተቸገሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ሆኖ ሳለ ዛሬ ደግሞ ጅቡቲ ሐገራችን ገብታ ውሃ እንድትጠጣ መሬት ተሰጣት ነገስ ማን ይሆን ባለተራው!!

ለማንኛውም ወያኔ ሐገሪቱን ሸንሽኖ ከመጨረሱ በፊት ሁላችንም ልናስብበት ይገባል ሐገር የማዳን ስራ መስራት ያለብን ወሳኝ ጊዜ ላይ እንገኛለን በመሆኑም እኛ ውሃ እየጠማን ለጅቡቲ ውሃ አንሰጥም ብለን ተቃውሟችንን ማሰማት መቻል አለብን ከሀገር ይልቅ ስለሌሎች የሚቆረቆር ወራሪ በመሆኑ ይህን ብልሹ አስተዳደር ተባብረን ከሐገራችን ማባረር መቻል አለብን እላለሁ።

ኢትዮጵያ ሐገራችንን እግዚአብሄር ይባርክልን

Ethiopia arrests 25 in 'terror' sweep

By AFP
Addis Ababa (AFP) - Ethiopian police arrested 25 people accused of plotting attacks in the country and suspected of having links to Somalia's Al-Qaeda-linked Shebab rebels, officials said Thursday.
Government spokesman Shimeles Kemal told AFP that those detained had been trained by the militants in Somalia and were planning a series of attacks in Jimma, about 305 kilometres (189 miles) southwest of the Ethiopian capital and where the arrests were made.
"About 25 people have been apprehended on suspicion of organising an underground terrorist cell," he said, adding that "a number of weapons" were also seized and the suspects likely to be charged.
Ethiopia, which shares a 1,600 kilometre border with Somalia, sent troops into the country in 2011 to help African Union and Somali defence forces fight the Shebab. It currently has around 4,500 troops in the country and has spearheaded a recent offensive against the Islamists.
Neighbouring Kenya has been a frequent target of attacks by Shebab rebels, who have demanded that Kenyan troops leave Somalia and claimed responsibility for last year's attack on the Westgate shopping mall in Nairobi that left at least 67 dead.
Uganda and Djibouti, both contributors to the AU force in Somalia, have also been attacked by the Shebab.
The US and British embassies have upgraded their travel warnings for Ethiopia in recent weeks, alerting visitors and residents to an increased threat of attacks.
Shimeles said while Ethiopia "has been and will remain vulnerable to terrorist attacks," the threat has not necessarily increased.
"I don't think that there is a special risk that warrants an extraordinary alert," he said.
Shebab leaders have vowed to attack Ethiopia to avenge the presence of its troops in Somalia, and last October two Somali nationals blew themselves up while crafting a bomb in Addis Ababa, which police said they planned to detonate at a crowded football match.

ኢ- ፍትሃዊው እስሬ! እየፈሩ ጋዜጠኝነት የለም! (ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ጎዳና )


June 5, 2014
Elias Gibru

(ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታችን ትልቅ አደጋ ላይ ነው)

አርብ ግንቦት 15 ቀን 2006 ዓ.ም ከወዳጄ ጋዜጠኛ ዳዊት ሠለሞን ጋር ቀጠሮ ነበረኝ፡፡ ረፋድ 5፡25 ሰዓት ላይ የሞባይል ስልኬ ጠራች፡፡ ከአምባሳደር ወደአራት ኪሎ በሚጓዝ ታክሲ ውስጥ ተሳፍሬ ነበር፡፡ የመስመር (የቢሮ) ስልክ መሆኑን አየሁትና “ሃሎ” አልኩኝ፡፡ ‹‹አቶ ኤልያስ፣ የዕንቁ መጽሔት ዋና አዘጋጅ?›› የሚል የሴት ድምጽ ተሰማኝ፡፡ ‹‹አዎን›› ስል መለስኩላት፡፡ ብዙ ጊዜ አንባቢዎች ስለሚደውሉ፣ ምን ዓይነት ግብረ-መልስ (feed back) ይኖራት ይሆን ነበር ሀሳቤ፡፡ ሳይሆን ቀረ፡፡ ‹‹የምደውለው ከፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ነው፣ በአንድ ጉዳይ ላይ ስለምንፈልግዎት ቃልዎትን መጥተው እንዲሰጡን ነበር፡፡›› …‹‹እሺ፣ ሰኞ ጥዋት ልምጣ?›› በማለት ጠየኳት፡፡ ‹‹ቆይ አንዴ?›› ብላኝ ባልደረቦቿን ካነጋገረች በኋላ ‹‹ይቻላል›› አለችኝ፡፡ ቀጭን የጌታ ትዕዛዝ፡፡ ከዚህ የስልክ ጥሪ በኋላ የመጽሔቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ማኅተመወርቅ (ፍቄ) ደውሎልኝ ስለጉዳዩ ሐሳብ ተለዋወጥን፡፡ ሰኞ በጥዋት ለመገናኘት ተቀጣጥረን ስልኩ ተዘጋ፡፡
ለምርመራ መጠራቴ በኢትዮጵያ የነጻ ፕሬስ ሕይወት ውስጥ የሚያጋጥም፣ የተለመደ ጉዳይ በመሆኑ ብዙ አልተገረምኩኝም፡፡ በቀድሞ አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ እሰራ በነበረበት ወቅት አሸባሪ ተብሎ በፓርላማ በተሰየመው የ‹‹ግንቦት 7›› የፖለቲካ ድርጅት አመራሮች እና በአገር ውስጥ በነበሩ ከፍተኛ ጄኖራሎች፣ የመከላካለያ ሰራዊት አባላትና ሌሎች ዜጎች ላይ ከባድ ክስ ቀርቦ ነበር፡፡ የፍርድ ሂደቱን ተከታትዬ የምዘግበው እኔ ነበረኩ፡፡ እኔ ከሰራሁት ዘገባ ጋር በተያያዘ አቃቤ ሕግ ክስ አቅርቦ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ከባልደረባዬ ጋዜጠኛ ፍጹም ማሞ (ዋና አዘጋጅ የነበረ) ተጠርተን ቃል በመስጠት በ5000 ሺህ ብር ከወጣን በኋላ ፍርድ ቤት ቀርበን ነበር፡፡ ፍ/ቤቱም ክሱን ተመልክቶ ለእኔ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የሰጠኝ አጋጣሚ ስለነበረ ጉዳዩን አስታውሼ በአዕምሮዬ ለአፍታም ቢሆን ማሰላሰሌ አልቀረም ነበር፡፡
ሰኞ ግንቦት18 ቀን 2006 ዓ.ም ጥዋት ከባልደረባዬ ፍቃዱ ጋር ቀጠሮ ስለነበረን ወደ ቢሮ አመራሁ፡፡ በአጋጣሚ ፍቃዱ ያለወትሮው ቢሮ አልነበረም፡፡ ስልኩ ይጠራል፣ ግን አይነሳም፡፡ ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ገደማ ፍቃዱ ደወለልኝ፡፡ ሞባይል ስልኩን ያላነሳው ጓደኛው ቤት ረስቶት በመውጣቱ ምክንያት መሆኑን ነገረኝ፡፡ ከሰዓት የተጠራሁበት ቦታ ለመሄድ በድጋሚ ተቀጣጠርን፡፡ ከሰዓት በኋላ ጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ እና ነብዩ ሐይሉ ተቀላቅለውን አራት ሆነን ወደማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ሄድን፡፡
ምርመራ ቢሮ ቁጥር – 76
እኔ እና ፍቃዱ ተፈትሸን እና ሞባይላችንን ጥበቃ ጋር አድርገን ወደቢሮ ቁጥር 76 አቀናን፡፡ እኔ አንኳኩቼ ወደ ቢሮዋ ገባሁ፡፡ ፍቃዱ ውጭ ቁጭ አለ፡፡ አንድ ወንድ እና ሴት የመ/ቤቱ ባልደረቦች ቢሮ ውስጥ ነበሩ፡፡ ከየት እንደመጣሁ ነገርኳቸው፡፡ ‹‹ቁጭ በል›› ተባልኩ፡፡ ‹‹ጥዋት ነበር እመጣለሁ እኮ ያልከው?›› ብሎ ወንዱ ፖሊስ ሀሳቡን ሰነዘረ፡፡ ‹‹አዎን›› ካልኩት በኋላ ጠዋት ያልመጣሁት በሁኔታዎች አለመመቻቸት መሆኑን አስረዳሁት፡፡ በምን ጉዳይ ልጠራ እንደቻልኩ መረጃው ካለኝ እንድነግረው ፈገግ እያለ ወዲያው እኔኑ ጠየቀኝ፡፡ መረጃው እንደሌለኝ ነገርኩት፡፡ አንድ የክስ መዝገብ ሲገልጥ የመጽሔታችንን ቁጥር 113ኛ ዕትም አየኋት፡፡ በመጽሔቱ ፊት ገጽ ላይ ‹‹በቃን! የጠባብ ብሔርተኝነት ዘመቻ›› በሚል ትልቅ ርዕስ ሥር የቀድሞ ጠ/ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ፣ የቀድሞ ም/ ጠ/ሚንስትር አቶ ታምራት ላይኔ፣ የኤርትራ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ፣ የኦነግ መስራች አቶ ሌንጮ ለታ፣ የቀድሞ ም/ ጠ/ሚንስትር እና የብአዴን ሊቀመንበር አቶ አዲሱ ለገሰ፣ የቀድሞ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር እና የብአዴን ሊቀመንበር አቶ ተፈራ ዋልዋና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን ፎቶግራፎች አለ፡፡ ይህ ጽሁፍ መጽሔቷ ዝግጅት ክፍል የተሰራ እና ከወራቶች በፊት አቶ አለምነው መኮንን የአማራን ሕዝብ ጸያፍ ስድቦች መሳደባቸውን ተከትሎ መሰል ድርጊቶች ሥርዓቱ ሥልጣን ከያዘ ጀምሮ በተለያዩ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት፣ በኤርትራው ፕሬዚዳንት እና በቀድሞ የኦነግ መስራች መደረጋቸውን በማስታወስ ጠባብ ብሄርተኝነትን የሚቃወም እና ለችግሩ መፍትሄ ጠቋሚ ጽሁፍ ነበር፡፡
በዚያን ዕለት ለፖሊስ ቃሌን እንድሰጥ የተጠራሁትም በዚሁ ጽሑፍ መስሎኝ ነበር፡፡ መርማሪ መሆን አለመሆኑን ያላረጋገጥኩት እያነጋገረኝ ያለው ወጣት ግን የተጠራሁት በቅርቡ በኦሮሚያ ክልሎች በተነሳው ግጭት እና ብጥብጥ ጋር በመሆኑ ላይ ጥቁምታ ሰጠኝ፡፡ በአጋጣሚ በእጅ ላይ ሁለት የዕንቁ መጽሔት ዕትሞችን ይዜ ገብቼ ነበር፡፡ ወጣቱ ልጅ ‹‹አንዴ ልመልከታቸው?›› ብሎኝ ግንቦት 20 በተመለከተ ባለፈው ቅዳሜ የወጣውን የመጽሔቱን ዕትም ሰጥቼው እያገላበጠ ተመለከታቸው፡፡ ከሌላ ክፍል የመጣ አንድ መርማሪም ክስ ያቀረበብኝን ዕትም ከፋይሉ ውስጥ ነጥሎ በመውሰድ የሆነ ጽሑፍን በተመስጦ አንብቦ ክፍሉን ለቅቆ ወጣ፡፡
ወጣቱ ልጅ፣ ‹‹ያው ጥዋት እመጣለሁ ብለህ እኛም ስንጠብቅህ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ እኛ በተራችን እናስጠብቅሃለን፡፡›› አለኝ – ፈገግ እያለ፡፡ ፈገግታው ከልብ የመነጨ ነው ለማለት ግን እቸገራለሁ፡፡ ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ አንዲት ወፈር ያለች፣ የፖሊስ ማዕረግ ያለው የደንብ ልብስ የለበሰች ሴት ወዳለሁበት ክፍል መጣች፡፡ ‹‹ኤልያስ አንተ ነህ?›› አለችኝ፡፡
‹‹አዎን›› አልኳት፡፡
‹‹መጣሁ›› ብላኝ ከአፍታ ቆይታ በኋላ ተመልሳ በመምጣት እኔ የተቀመጥኩበት ወንበር ጋር ባለው ሰፋ ያለ ጠረጴዛ ትይዩ ተቀመጠች፡፡
‹‹ጥዋት ለምን አልመጣህም?›› የመጀመሪያ ጥያቄዋ ነበር፡፡
በአጋጣሚ በተፈጠረ ጉዳይ መምጣት አለመቻሌን አስረዳኋት፡፡ በዚህ ጊዜ ወጣቱ ልጅ አድራሻዬን፣ ዜግነቴን፣ የትውልድ ቦታዬን፣ የተማርኩባቸውን ትምህርት ቤቶች እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ የሰራሁባቸውን የሚዲያ ድርጅቶች፣ የትዳር ሁኔታ …እየጠየቀኝ ፎርም ላይ እየሞላ ነበር፡፡
‹‹ብሔርህስ?›› አለኝ፡፡ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› አልኩት፡፡
‹‹ያ’ማ ዜግነት ነው፣ መናገር አለብህ›› አለኝ፡፡ በግሌ የማልወደው ጥያቄ መሆኑን ነገርኩት፡፡ [የሰው ልጆች በሙሉ ምንጫችን አንድ ነው ብዬ አጥብቄ ስለማምን የዘር ጥያቄ ከልጅነቴ ጀምሮ የማይመቸኝ እና የማላምንበት የግል ጉዳይ ነው] ስለብሄር ሊያስረዳኝ ሞከረ፡፡ መታወቂያዬ ላይ የተጻፈውን ነገርኩት፡፡
ወ/ሮ በላይነሽ የተባለችው ምርማሪዬ ፋይሉን ተቀብላ እና በመጽሔቱ የተከሰስኩበትን ጉዳይ ነገረችኝ፡፡ በታሪክ አምድ ሥር ‹‹የተገነቡት እና በመገንባት ላይ ያሉት የመታሰቢያ ሐውልቶች የእነማን እና ለእነማንስ ናቸው?›› በሚል ርዕስ ሰዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን የተባለው ጸሐፊ በጻፈው ጽሑፍ ውስጥ የኦሮሞን ብሔር የሚያጥላላ፣ ዘርን ከዘር የሚያጋጭ፣ የኦሮሞ ሕዝብ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ የመጣ መሆኑን የሚጠቅስ፣ ለኢትዮጵያ እንግዳ ሕዝብ መሆኑን የሚናገር …ወዘተ በጣም ጥሩ ያልሆነ ጽሑፍ መሆኑን ነገረችኝ፡፡ አያይዛም ይህን ጽሑፍ ተከትሎ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ቁጣ መቀስቀሱን፣ ተማሪዎች ጽሑፉን የጻፈው ግለሰብ ለሕግ እንዲቀርብ ሁለት ጊዜ ያህል ለዩኒቨርሲቲው የሚመለከተው አካል በደብዳቤ ቢያሳውቁም መልስ ሳይሰጣቸው በመቅረቱ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣታቸውን፣ መስታወቶች መሰባበራቸውን፣ ንብረቶች መውደማቸው፣ በሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን፣ ሆስፒታል ገብተው በሞት እና በሕይወት መካከል ያሉ ተማሪዎች መኖራቸውን፣ የመማር ማስተማር ሒደት መስተጓጎሉን …ወዘተ ዘርዝራ አስረዳችኝ፡፡
እኔም እኛ (የመጽሔቱ አዘጋጆች እና ባልደረቦች) ኢትዮጵያን አንድ የሚያደርግ እንጂ ዘርን ከዘር የሚከፋፍል ሥራ አለለመስራታችንን፣ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 29 መሰረት ሕግን በማክበር ጽሑፎችን መጻፋችንን እና የተለያዩ ግለሰቦችን ሐሳቦች ማስተናገዳችንን፣ ይህንንም መመልከት እንደሚቻል ከጠቀስኩላት በኋላ የተባለው ጽሑፍ የመጽሔቱ ሳይሆን የግለሰቡ የግል ግለ-ሀሳብ መሆኑን አሰረግጬ ነግሬያት ነበር፡፡
መርማሪዬም ‹‹ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በሕገ-መንግሥቱ ተደንግጓል ብላችሁ የመጣላችሁን ጽሑፍ በሙሉ ታትማላችሁ ማለት ነው?›› በማለት ቆጣ በማለት ለመናገር ሞከረች፡፡ የመጡልን ጽሑፎች ሁሉ እንደማይታተሙ፣ እንደዋና አዘጋጅነቴ መስተካከል ወይም መታረም ያለባቸውን ጽሑፎች በአግባቡ እንደምመለከት፣ ሌሎች የመጽሔቱ አዘጋቾችም መሰል ሥራዎችን ተጋግዘን እንደምንሰራ ረጋ ብዬ አስረዳኋት፡፡
በክፍሉ ውስጥ ያሉት ሶስቱም የፌዴራል ፖሊስ ባልደረቦች በጽሑፉ ምክንያት የጠፋ ንብረት እና የአካል ጉዳት መኖሩን አጽንኦት በመስጠት ‹‹አጥፍታችኋል›› በሚል ተቆጥተው ሊናገሩኝ ሞከሩ፡፡ የእኔም ስሜት በተወሰነ ደረጃ መቀየር ጀመረ፡፡ እመን አትመን ክርክር ውስጥ ለአፍታም ቢሆን ገባን፡፡ ‹‹እነዚህ ሰዎች የፍርድ ቤትንም ሥራ ደርበው ይሰራሉ ወይ?›› ስል ታዘብኩ፡፡
ንግግሬን ቀጥያለሁ፡፡ በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተፈጠረ ለተባለው ነገር መጽሔታችን መነሻ መሆኑን ለመቀበል እንደምቸገር፣ መጋቢት ወር ላይ የወጣ ጽሁፍ አደረሰ የተባለውን ችግር ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት እዚህ ምርመራ ክፍል ውስጥ መሆኑን፣ በጽሑፉ የተቆጡ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለዝግጅት ክፍላችን አለመግለጻቸውን፣ ተማሪዎቹ ያቀረቡትን ቅሬታ ዩኒቨርስቲው መደበኛ በመሆነ መልኩ ለመጽሔታችን ዝግጅት ክፍል ምንም ነገር አለማቅረቡን፣ ቅሬታ ቀርቦ ቢሆን ኖሮ ተፈጠረ የተባለውን ችግር ለመፍታት እኛም የራሳችንን ሥራ መስራት እንችል እንደነበረ፣ ማስተባበያ ጽሁፍ ወይም ጽሑፉን የሚተች ሌላ ጽሑፍ ቢመጣ ኖሮ በተመሳሳይ ገጽ እና ይዘት እንደምናስተናግድ፣ ለዚህም ኃላፊነት እና ግዴታ እንዳለብን ተናገርኩ፡፡
በዚህም ብቻ አቆምኩም፣ በዚሁ መጽሔት ላይ የፖለቲካ አቀንቃኑ እና የኦሮሞ ጉዳዮች ዋነኛ ተማጋች መሆኑ የሚታወቀው ጃዋር መሐመድ የኦሮሞን ሕዝብ ጥያቄዎች ከነመፍትሄዎቹ በተመለከተ የሰጠንን ሰፊ ቃለ ምልልስ ማስተናገዳችንን፣ አቶ ኦባማ አንሰርሙ የተባሉ ጸሐፊም ስለኦሮሞ ሕዝብ ታሪክ ሰፊ ጽሁፍ አቅርበው በመጽሔታችን ላይ ማስተናገዳችንን ዋቢ በማድረግ አስረዳኋቸው፡፡ እኔም ብሆን በግሌ የትኛውም ዘር ከየትኛውም ዘር እንደማይበልጥ እና እንደማያንስ፣ የኦሮሞ ሕዝብ ረዥም ታሪክ ያለው ትልቅ ህዝብ መሆኑንና ከገዳ ሥርዓትም ዓለም ዴሞክራሲን እንደተማረ የግል ዕምነት እንዳለኝ ሀሳቤን ሰነዘርኩ፡፡
በቢሮው ውስጥ የፖሊስ ልብስ ለብሳ ኮምፒውተር ላይ ጽሑፍ በመተየብ ላይ ያለች አንዷ የተቋሙ ባልደረባ ጽሑፉ ግጭት ማስነሳቱን እና ጉዳት ማድረሱን ደጋግማ በመናገር ጥፋተኛ መሆናችንን ለመናገር ጥረት አድርጋ ነበር፡፡
እዚህ ጋር ለፖሊሷ ምሳሌ አነሳሁላት፣ አቶ መለስ ዜናዊ ‹‹የኢትዮጵያ ታሪክ የ100 ዓመት ነው›› ብለው ተናግረዋል በሚል በአንድ ወቅት መስማቴን በመጥቀስ ይህ የግላቸው ዕምነት መሆኑን፣ እኔ ደግሞ ኢትዮጵያ ከ3000 ዓመታት በላይ ታሪክ እንዳላት እንደማምን እና የሳቸውን ሀሳብ መቃወም ካለብኝ መስታወት በመስበር እና ብጥብት በማስነሳት ሳይሆን በሀሳብ ሞግት ብቻ መሆን እንዳለበት አስረዳኋት፡፡ ምሳሌዬ ባይወጥላትም ዝም አለች – ሌላም ምሳሌ አንስቼላት ነበር፡፡ አቶ መለስ ‹‹የአክሱም ሐውልት ለወላይታው ምኑ ነው›› ብለው ነበር፡፡ ስላት፡፡ ‹‹አዎን፣ ምኑ ነው›› ብላ በፈጥነት መለሰችልኝ፡፡ ግን ትሰማኛለች እንጂ አታዳምጠኝም፡፡ ምናልባት እርሷንም ያስከስሳት ይሆን ማድመጧ!
…ሰዓቱ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ሆነ፡፡ መርማሪዬ ወደቤቷ ለመሄድ የቸኮለች መሰለኝ፡፡ ቃሌን ለመስጠት በነጋታው ከእሷ ጋር ተቃጣጠርን፡፡ በዋስ መውጣት እንደማልችል አረዳችኝ፡፡ እኔም በክፍሉ ውስጥ ካደረግነው ንግግር እና ፊታቸውን በማንበብ ቀድሜ ተረድቼ ነበር፡፡ ባልደረባዬ ፍቃዱን አስጠራሁት፡፡ ዋስትና መከልከሌንም ነገርኩት፡፡ ለእናቴ ስለጉዳዩ ነግሮ እንዲያረጋጋት ስልኳን በወረቀት ላይ ጽፌ ሰጠሁት፡፡ የቤቴን ቁልፍ ለአናንያ ሶሪ እንዲሰጥልኝ ነግሬም ቻው ተባብለን ተሰናበትኩት፡፡ እንግዲህ እንዲህ ነው እስር፣ በስልክ ጠርቶ ቡና ከበጋበዝ ይቀላል – ለመንግሥታችን፡፡
…ይቀጥላል!

Wednesday, June 4, 2014

አባ ዱላና ከንቲባ ድሪባ የቁም እስረኛ ሆኑ፣ ፓስፖርታቸው ተቀማ

“የኢህአዴግ በርዕዮተዓለም መበላላት ይፋ እየሆነ ነው”

abadulla and deriba
አባ ዱላ ገመዳና የአዲስ አበባ ከንቲባ ድሪባ ኩማ ፓስፖርታቸውን ተነጥቀው የቁም እስረኞች መሆናቸው ከተለያዩ ምንጮች እየወጡ ያሉ መረጃዎች አመልከተዋል። የጎልጉል ምንጮች ግን ኦህዴድ ውስጥ በከፍተኛ አመራሮች ደረጃ እየተካሄደ ያለው ግምገማ ሲጠናቀቅ በርካታ ባለስልጣኖች ክስ እንደሚመሰርትባቸው ተናግረዋል።
በቀድሞው የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት አባ ዱላ ገመዳና በአቶ ድሪባ ላይ ይህ ውሳኔ የተላለፈው አገር ጥለው እንዳይወጡ በሚል ነው። ጎልጉል በቅርቡ ካገር መውጣት የማይችሉ ባለሥልጣኖች እንዳሉ ጠቅሶ መዘገቡ ይታወሳል። ውሳኔው የተላለፈው ሰሞኑን የአዲስ አበባን አዲስ ማስተር ፕላን ለመተግበር የኦሮሚያ ክልል ከተሞች መካተታቸው ይፋ መሆኑን ተከትሎ ከተነሳው ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ነው። ከሁለቱ ባለስልጣናት በተጨማሪ ከፍተኛ የክልልና የዞን የኦህዴድ አመራሮችም በደህንነት ቅርብ ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑ ተሰምቷል። ካገር መውጣት የማይችሉም አሉ።
አባ ዱላ /ጃርሳው/
ሙክታር
ሙክታር
አባ ዱላ ኦሮሚያን ሲረከቡ በማክረር አካሄድ የሚታወቁት አቶ ጁነዲን ያዋቀሩትን ካቢኔ በመበተን ሥራቸውን አንድ ብለው ጀመሩ። አዲስ ካቢኔ ሲገነቡ የመረጡት አዲስ የዩኒቨርስቲ ተመራቂዎችንና በክልሉ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተቀናቃኝ (የተቃዋሚ) ፓርቲ አባላትን በማስኮብለል ነበር። ህወሃት ለሁለት በተበረገደበት ወቅት ለአቶ መለስ ቡድን ድጋፍ በመስጠት ቅድሚያ የያዙት አባ ዱላ ባስቀመጡት ውለታ መሰረት ኦሮሚያ ላይ ያሻቸውን እንዲያደርጉ የሟቹ መለስ ድጋፍ ነበራቸው። በዚህም ድጋፍ ሳቢያ ኦሮሚያ ላይ የሚፈልጉትን ሲያደርጉ ከተባረሩት መካከል የአሁኑ ፕሬዚዳንት ሙክታር ከዲር ይገኙበታል።
“አትደግፉን ነገር ግን የክልሉን ልማት አታደናቅፉ” በማለት አዲስ የመለመሏቸው የተለያየ አመለካከት ያላቸው አዳዲስ የኦህአዴድ አባላት ኦሮሚያን ከአባ ዱላ እጅ ተረከቡ። አባ ዱላ ፍጹም ነጻነት ይሰጡ ስለነበር ካድሬው ወደዳቸው። ስማቸው ተቀይሮ መለያ ተሰጣቸው፤ “ብራንድ” ሆኑ – “ጃርሳው” ተባሉ። በካቢኔያቸውና በሳቸው መካከል የነበረው ፍቅር በነደደበት ወቅት አባ ዱላ ክልሉን እንደሚለቁ ተሰማ። ባለፈው ምርጫ አባ ዱላ ለፌዴራል እንጂ ለክልል እንደማይወዳደሩ ይፋ ሲደረግ ካድሬው ገነፈለ። “የኢህአዴግ ምክር ቤትን ውሳኔ አንቀበልም” በማለት ተቃወመ። ከአንዴም ሁለት ጊዜ ስብሰባ ቢካሄድም ከስምምነት ላይ ሊደረስ ባለመቻሉ ተበተነ። በመጨረሻም ራሳቸው አባ ዱላ በመሩት ስብሳባ ካድሬውን ተማጽነው ነገሩ ረገበ። ይሁን እንጂ ቅርሾ ግን ነበር። ይህንኑ አስመልክቶ “ኦህዴድ/ኢህአዴግ በመደብ ትግል መተላለቅ ጀመረ” በማለት ዘግበን ነበር።
አባ ዱላ ኦሮሚያን ሲመሩ ቆይተው ሲመሻሸ “ይህንን ቤት ይዤ ለመታገል አይመቸኝም” በማለት ቦሌ ያስገነቡትን አስገራሚ ህንጻ ለኦህዴድ አስረከቡ። በከፍተኛ ሙስና ይታሙ ስለነበር ተናዘውና ገብረው ታለፉ። ለፌዴራል ተወዳድረው አፈ ጉባኤ ለመሆን በቁ። በወቅቱ የወ/ሮ አዜብ ድጋፍ ቢኖራቸውም የሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲን የቀኝ እጅ የሆኑ ባለስልጣኖች ግን ጠምደዋቸው ነበር። ሙክታር አህመድ አንዱና ዋናው ነበሩ። ከላይ በረከት ስምዖንና አዲሱ ለገሰ አባ ዱላን ከሚቃወሙ መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚቀመጡ ናቸው።
በዚህ አጣብቂኝ ውስጥ አልፈው እዚህ የደረሱት አባ ዱላ ሰፊ ቁጥር ያላቸውን ተማሪዎች ህይወት የቀጠፈውን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን አስመልክቶ አምቦ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ተማሪዎችን ከወ/ሮ አስቴር ማሞ ጋር በመሆን አነጋግረው ነበር። በወቅቱ የተማሪዎቹ ጥያቄ ፍትሃዊ እንደሆነ ሲመሰክሩ፣ ይህንኑ ምስክርነታቸውን ለተለያዩ የአገር ውስጥና የውጪ አገር ሚዲያዎች አሳውቀውም ነበር። አያይዘውም ነፍስ ያለ አግባብ ያጠፉ እንደሚጠየቁ ቃል ገቡ።abadulla
የጎልጉል ምንጮች እንዳሉት አባ ዱላ ይህንን ከተናገሩ በኋላ ከፍተኛ ወቀሳ ተሰንዝሮባቸዋል። “ረብሻውን ያስነሱት ራሳቸው የኦህዴድ ካድሬዎች ናቸው” ከሚል ድምዳሜ የደረሰው ኢህአዴግ ችግሩ ከተፈጠረ በኋላ ሰፊ የስለላ ስራ አከናውኗል። “ጥፋተኞቹን ለህግ እናቀርባለን” በማለት መግለጫ ያወጣው ኢህአዴግ በቀጣይ የሚያስራቸውና የሚከሳቸው ባለስልጣኖች አሉ። ምንጮቹ በተለይ አባዱላና የአዲስ አበባ ከንቲባ የሆኑት አቶ ድሪባ ኩማ ላይ ስለሚወሰደው ርምጃ ያሉት ነገር ግን የለም። ክስ ከተመሰረተባቸውና ምርመራው በሰንሰለት ታች ድረስ ከዘለቀ የኦህአዴድ የታችኛው መዋቅር ሊናጋ እንደሚችል ግን ግምታቸውን አኑረዋል። ለምሳሌ ያነሱት ሽፈራው ሽጉጤን ነው። ሽፈራው ሽጉጤ በሙስና እንዲከሰሱ ከተወሰነ በኋላ የታለፉት “የሲዳማ ብሔረሰብ ይነሳል” በሚል እንደሆነ ያወሱት ምንጮች “ክስ ተመስርቶ ምርመራው ቢካሄድባቸው ወ/ሮ አዜብም አሉበት ሲሉ አስቀድመው በምክር ቤት ይፋ በማድረጋቸው ዝምታ ተመርጧል”።
ኦህዴድን ወደ ታች ማዘዝ እንደ ቀድሞው አይቀልም
አዲስ አበባን የሚያሰፋው አዲሱ ማስተር ፕላን ተግባራዊ እንዲሆን ሀሳብ ሲቀርብ ድፍን የኦህዴድ ምክር ቤትና ካቢኔ ተቃውሞ አሰምቷል። በክልሉ ምክር ቤት ደረጃም የተያዘው አቋም ተመሳሳይ ነው። ይህንን እውነት የሚያነሱ ክፍሎች ኢህአዴግ/ህወሃት ስንቱን አስሮና ለፍርድ አቅርቦ ይችለዋል ሲሉ ጥያቄ ይሰነዝራሉ” ቀደም ሲል በምርኮኞች ስብስብ የተቋቋመው ኦህዴድና አሁን ያለው ኦህዴድ የተለያዩ መሆናቸውን ኢህዴግ ችግር ሊገጥመው እንደሚችልም ግምታቸውን ያስቀድማሉ።
አሁን ያለው ኦህአዴድ ከምርኮ አስተሳሰብ የተላቀቀ። አዲስ ትውልድ የተካተተበት፣ በጎሳ አስተሳሰብ የተቃኙ፣ ህወሃት በሚፈልገው መጠን ከመታዘዝ በላይ ወደ ራሳቸው ደምና ጎሳ የተሳቡ፣ ይህንኑ አስተሳሰብ እስከ ቀበሌ መዋቅር ድረስ የተከሉ በመሆናቸው የተወሰኑ የበላይ አመራሮችን በማሰር ችገሩ ሊፈታ እንደማይችል ሰፊ አስተያየት እየተሰጠ ነው። ለዚህም ይመስላል ኢህአዴግ በመደብ መተላላቅ መጀመሩ ይፋ እየሆነ የመጣው።
የመጨረሻው መጀመሪያ
ለጊዜው ይፋ ሆኑ መረጃዎች እንደሚያመክቱት አባዱላና አቶ ድሪባ ኩማ ካገር መውጣት አይችሉም። የተጀመረው ግምገማ ተጠናቆ የሚሆነው ሳይታወቅ በቅርብ ክትትል ስር ናቸው። የጎልጉል ምንጮች እንደጠቆሙት የዞንና ወረዳ መዋቅሮች ላይ ርምጃ ለመውሰድ  ስጋት አለ። ካድሬው ዘንድም መደናገጥ ተፈጥሯል። ህወሃት ውስጥም የአቋም መለያየት ተከስቷል፡፡ በአንድ ወገን ካድሬው እንዳይሸፍትና በቀጣዩ ምርጫ ኢህአዴግን አሳልፎ እንዳይሰጠው ርምጃው የተለሳለሰ መሆን አለበት እየተባለ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ግለ ሂስ በማካሄድ ነገሩን የማርገብና ምርጫውን የማለፍ ስልታዊ አካሄድ አለ። ይሁን እንጂ ኦህዴድ እየተለማመደ ያለው አካሄድ ሌሎችን ትምህርት በሚሰጥ መልኩ ካልታረመ ወደ ፊት ችግሩን ያገዝፈዋል የሚል አቋም የሚያራምዱ መኖራቸው ታውቋል። ህወሃት በዚህ ደረጃ አቋም ለመያዝ አለመቻሉና በርዕዮተ ዓለም መከፋፈል መጀመሩ ለዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ የዘራው መርዝ መልሶ ራሱን ሊያጠፋው አፉን መክፈቱ የሚጠቁም ነው፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ወቅት “ኢህአዴግ በርዕዮተ ዓለም መበላላት መጀመሩ ይፋ እየሆነ ነው” የሚለው ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚነሳ ዓቢይ ጉዳይ ሆኗል፡፡

Tuesday, June 3, 2014

ግንቦት 20፡ የኢትዮጵያዊያን ጠላት መሆንን የመረጠ ጉጅሌ ለስልጣን የበቃበት ታሪካዊ ቀን፤






በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ወርሃ ግንቦት የተለየ ሥፍራ አላት።ከወርሃ ግንቦት ግንቦት ሰባትንና ግንቦት ሃያን በተለይ አንረሳቸውም። ግንቦት ሃያ ጎጠኝነት፤ እኔ ብቻ ባይነት፤ አስመሳይነት ፤ስግብግብነት እና ሌብነት ተደምረው የወለዱት ቡድን ብሶት ወለደኝ ብሎ በትረ ስልጣኑን የተቆጣጠረበት ቀን። ብሶት ወለደኝ ብሎ ግንቦት 20 ዕለት በትረ ስልጣኑን የጨበጠው ቡድን ግንቦት ሰባት ዕለት ብዙ ህፃናትን፤ ብዙ ወጣት ሴትና ወንዶችን፤ ብዙ አረጋዊያንን ገድሎና በደም ሰክሮ የዴሞክራሲ ጥያቄዎችን ለማዳፈን የሞከረበት ቀን። አዎን ግንቦት ሃያ የኢትዮጵያ ጠላት መሆንን የመረጠ ጉጅሌ ለስልጣን የበቃበት ታሪካዊ ቀን።


ህወሃትን ስልጣን ይዞ አገርን ሊመራ እንደሚችል የፖለቲካ ተቀናቃኝ ድርጅት አድርጎ ማየት ከስህተት ይጥላል። ስህተቱ ደግሞ ለነፃነት፤ ለእኩልነት እና ለፍትህ የሚደረገውን የትግል አቅጣጫ ያዛባል። የትግሉ አቅጣጫ እንዳይዛባ ህወሃት የህዝብ ጠላት መሆንን የመረጠ ጉጅሌ መሆኑን አጥብቆ መያዝ ያስፈልጋል። ህወሃትን ከህዝብ ጠላትነት ዝቅ አድርጎ ማየት በማንኛውም መለኪያ ስህተት ነው።
በዚህ ወቅት ጉጅሌው ህወሃት የህዝብ ጠላት መሆኑን የሚጠራጠር ኢትዮጵያዊ እውነቱን ለመቀበል የማይፈልግ፤ ለነፃነት የሚከፈለውን ዋጋ ለመክፈል የማይፈልግ ሰነፍ አልባሌ ሰው ነው። እንዲህ ዓይነት ሰነፍ ሰዎች ጉጅሌዎቹ ሠላም ያመጣነው እኛ ነን ሲሉ ያምኗቸዋል። ልማትም ከመቼውም ግዜ በላይ ለኢትዮጵያ ያመጣንላት እኛ ነን ሲሉ እውነት ነው ይላሉ። እኛ ከሌለን ኢትዮጵያ ትበታተናለች ብለው ሲደነፉም ይደነግጣሉ።እንዲያውም ህወሃቶች ከሌሉ ማን አገሪቷን ሊመራት ይችላል ብለው ለመከራከር ይዳዳቸዋል።
ህወሃቶች በማንኛውም መስፈርት አገር ለመምራት ብቃት ያላቸው ቡድኖች አይደሉም። አገር የሚመራ ኃይል ኢትዮጵያዊ ብሄረተኝነትን ለማጥፋት ሳይታክት አይሠራም። ጉጅሌዎቹ ከተመሸጉባቸው የጎሳ ፖለቲካ ክበብ ውስጥ ሁነው ኢትዮጵያዊ ብሄረተኝነትን ለማጥፋት ያልፈነቀሉት ድንጋይ፤ያልቧጠጡት ዳገት የለም። ጉጅሌዎቹ የማያውቁት አንድ እውነት ግን ኢትዮጵያዊ ማንነት በፀና መሠረት ላይ የቆመ ተሸርሽሮ የማያልቅ ፅኑ ዓለት መሆኑን ነው። ግንቦት ሃያ ዕለት ስልጣኑን የጨበጠው ጎጠኛው ነፃ አውጪ ቡድን ከሃያ ዓመት በኋላም ሥሙን እንኳን ሳይቀይር “እኔ ካልገዛኋችሁ ኢትዮጵያ ትበታተናለች” እያለ ያሟርታል። ህወሃትን የህዝብና የአገር ጠላት የሚያሰኘው አንዱ አንጓም ይሄው ነው።”እኔ ያልኩት ካልሆነ አገሪቷን አፈርሳታለሁ፤ የጎሳ ግጭት ተነስቶ ህዝቡ እርስ በርሱ እንዲተላለቅ አደርጋለሁ” እያለ መዛቱ። እንግዲህ “እኔ ከሌለው አገሪቷን አፈርሳታለሁ” የሚል ቡድን በምን መሥፈርት አገርንና ህዝብን መርቶ ወደ ተሻለ ደረጃ ሊያደርሳት እንደሚችል “ህወሃቶች ከሌሉ አገሪቷን ማን ይመራታል” ብለው የሚጨነቁ ሰዎች መልሰው መልሰው ራሳቸውን እንዲጠይቁ እንመክራቸዋለን። ለማንኛውም ከግንቦት ሃያ መራራ ፍሬዎች መካከል አንዱ “እኔ ያልኩት ካልሆነ አገሪቷን እበትናታለሁ” የሚል ክፉና ጎጠኛ ጉጅሌ በአገራችን ጫንቃ ላይ መጫኑ ነው።
ጉጅሌዎቹ ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ ልማት አመጣንም እያሉ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ይጮኻሉ።የህወሃቶች ድንቁርና ልማትን ከሰው ልጅ ሠላምና ደስታ ይልቅ ዛሬ ታይቶ ነገ በሚጠፋ ግዑዝ ቁስ መለካታቸው ነው። ይህ ግዑዙ ቁስ ለሠው ልጆች ሠላም፤ ደስታና እፎይታ ካላስገኘ ልማት ሊባል አይቻልም። ጉጅሌዎቹ ልማትን የሚለኩት ከህዝቡ ደስታ፤ ሠላም እና የእለት ጉርሳቸውን ያለጭንቀት አግኝተው ማደር ከመቻላቸው አንፃር ሳይሆን ራሳቸው ዘርፈው ካካበቱት ሃብት አንፃር ነው። እነርሱ ዘርፈው ብዙ ሃብት ስላከማቹና ስም አጠራሩን እንኳ የማያውቁትን መጠጥ በብዙ ሺህ ብር ገዝተው መጠጣት ስለቻሉ አገሪቷ ያደገች ይመስላቸዋል። ጉጅሌዎቹ እንደሚሉት አገሪቷ በልማት ጎዳና ላይ እየተጓዘች ቢሆን ኑሮ ወጣቱ ትውልድ በአገሩ ተስፋ ቆርጦ የባእድ አሸከርና ገረድ ለመሆን ስደትን የሚመርጥ ባልሆነ ነበር።ጉጅሌዎቹ አገሪቷን ከተቆጣጠሩ ከግንቦት ሃያ 1983 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ መሰደድን የማይመኝ ዜጋ አይገኝም። መንኩሴ፤ ሼኽ፤ ፓስተር፤ ገበሬ፤ ምሁር፤ ተማሪ ሁሉም የሚሰደድባት አገር ኢትዮጵያ ነች። ግንቦት ሃያ ካተረፈልን ፍሬዎች መካከል ሊጠቀስ የሚችለው የዜጎች ያለገደብ መሰደድ ነው። ልማታዊ ነን ብለው ራሳቸውን የሚጠሩት ጉጅሌዎቹ ዜጎች እጅግ አደገኛ በሆነ በርሃና ባህር ውስጥ አልፈው ከቀናቸው አሽከርና ገረድ መሆንን ለምን እንደሚመርጡ መልስ የላቸውም።
“የኢኮኖሚ ልማት … በሰው ልጅ ሁለንተናዊ እድገት፣ በዋና ዋና መሠረተ ልማት አቅርቦቶች፣ በአካባቢው ገበያ በሚኖር ተወዳዳሪነት፣ በምቹ የተፈጥሮ አካባቢ (ኢንቫይሮመንት)፣ በማኅበራዊ መስተጋብር፣ በጤና፣ በደህንነት፣ በትምህርት እና በመሳሰሉ ነገሮች እድገት ማምጣትን ያካትታል።ብለው ልማትን የሚተረጉሙ ሊሂቃን አሉ።”
የጉጅሌዎቹ ልማት በእነዚህ መሥፈርቶች ቢለካ ተስፋ በሚያስቆርጥ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አገራቸውን ጥለው የሚሰደዱ ዜጎች ብዛትና ዓይነት ደህና ምስክር ነው። የጉጅሌዎችን የህዝብ ጠላትነት ከሚያሳዩ እውነታዎች መካከል ሌላው ገፅ ይሄው ዜጎችን በሙሉ ተስፋ አስቆርጦ ለስደት የሚዳርግ ሥርዓት በአገሪቷ ውስጥ እንዲዘረጋ ማድረጋቸው ነው።
ህወሃቶች የህዝብ ጠላት መሆንን የመረጡ ጉጅሌዎች ናቸው ስንል ሌላው መገለጫቸው ህዝቡን ሠላም ማሳጣታቸው ነው። ጉጅሌዎቹ እኛ ከመጣን በኋላ አገሪቷ ሠላም ወረደላት፤ የህዝቡም አንድነት ከመቸውም ግዜ በላይ ተጠናከረ እያሉ ያላዝናሉ።
በእውኑ ኢትዮጵያችን ውስጥ ሠላም አለን? ህዝቦቿስ ከመቸውም ግዜ በላይ በኢትዮጵያዊነት ስሜት አብሮ የመኖር ዝንባሌ እያሳዩ ነውን ? መልሱ ግልፅ ነው። ሠላም የለም፤ ኢትዮጵያም የዜጎቿ አገር አልሆነችም።
ከግንቦት ሃያ መራራ ፍሬዎች መካከልም ዜጎች ለዘመናት ከኖሩበት እና እትብታቸው ከተቀበረበት መንደር ውጡና ወደ አገራችሁ ሂዱ ተብለው ከነ ቤተሰቦቻቸው ሜዳ ላይ ተበትነው ማየታችን ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ቁም ነገር ነው። ጉራፋርዳ አማራ ተብሎ ለሚጠራው ዘውጌ ማህበረሰብ አገሩ ካልሆነ የአማራ አገሩ የት ነው? ከቤንሻንጉል አማሮች ውጡ ሲባሉ ኢትዮጵያዊነት ከወደየት አለ? በአዲስ አበባ አካባቢ የሚኖሩ የኦሮሞ ገበሬዎች ተፈናቅለው የትም ተጥለው የጉጅሌው አባላት እና ደጋፊዎች መሬታቸውን ሲቀራመቱ ህግ የት ደረሰ? እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች የግንቦት ሃያ ፍሬዎች መሆናቸውን መርሳት አይገባም።
እንግዲህ ጉጅሌዎቹ ነጋ ጠባ “ሰላማችን፤ ሰላማችን” እያሉ የሚያላዝኑት፤
  • ዘረኝነት የፓለቲካ ሥርዓቱ መታወቂያ ሆኖ እያለ፤
  • ኢፍትሃዊ የሀብትና የሥልጣን ክፍፍል እና ሙስና የሥርዓቱ መለያ ሆነው እያሉ፤
  • ፍትህ ተዋርዳ ፍርድ ቤቶች ገዢዎች የሰጡት ቅጣት ማሳወቂያ በሆኑበት፤
  • በዘርና በፓለቲካ ወገንተኝነት የተዋቀሩት የጦር ሠራዊት፣ የፓሊስና የስለላ ተቋማት ኢትዮጵያዊያንን ማጥቂያ ሆነው እያሉ፤
  • በፓለቲካ እምነታቸውና በሀይማኖቻቸው ምክንያት ታስረው ሰቆቃ እየተፈፀማቸው ያሉ ወገኖቻችን ብዛት በአስደጋጭ ፍጥነት እየጨመረ ባለበት ሁኔታ፤
  • ሚሊዮኖች ድሀ ገበሬዎች ከይዞታቸው እየተፈናቀሉ በገዛ አገራቸው ስደተኛ የሆኑበት ሁኔታ እየተባባሰ መምጣቱን እያየን፤
  • ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ቤተሰቦቻቸውን የሚመግቡት ቁራጭ መሬት አጥተው እያለ ሰፋፊ ለም መሬቶች ለውጭ ባለሀብቶች በገፍ እየተሸጠ ባለበት ሁኔታ፤
  • የወያኔ ሹማምንት በሀብት ላይ ሀብት እየጨመሩ ከተሞችን በሕንፃዎች ሲያሽቆጠቆጡ ዛንጋባ እንኳን አጥተው በረንዳ ላይ የሚያድሩ ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መሆኑን በገዛ ዓይኖቻችን እያየን፤
  • ከፍተኛ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ወጣቶች ለሚጠብቃቸው የሥራ እድል ባይማሩ ኖሮ ይበልጥ ተመራጭ ይሆኑ የነበረበት የመሆኑ አሳዛኝ ሐቅ እያየን፤
  • ወጣቶች በተስፋ እጦት ከአገር ሲሰደዱ በባህር ሰጥመው አሊያም በበረሃ ንዳድ ተቃጥለው እያለቁ ባሉበት በአሁኑ ሰዓት፤
  • አብዛኛው ሰው ቁርስ፣ ምሳና ራቱን ደርቦ “ቁምራ” እየበላ ስለ ተከታታይ ዓመታት 11.6 % ዓመታዊ የኢኮኖሚ እድገት መስማት ግዴታ የሆነበት የጉድ አገር ሆኖ እያለ፤
  • የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪቃና የአረብ አገራት እስር ቤቶች በኢትዮጵያዊያን ወንዶችና ሴቶች ተሞልተው እያለ፤ እና
  • ወያኔ የሚያደርሰው ግፍ ፅዋውን ሞልቶ በፈሰሰበት በአሁኑ ወቅት ነው “ሰላማችን፣ ሰላማችን” እያሉ የሚያደነቁሩን።
ይኸ ሁሉ ኢ-ፍትሃዊነት ባለበት ሊኖር የሚችለው ሰላም አሉታዊ ሰላም ያውም ተቃውሞን በጉልበት በመደፍጠጥ የሚገኘው አደገኛ አሉታዊ ሰላም ብቻ ነው።በጉልበት የሚመጣ አሉታዊ ሰላም ለአገራችን አይበጃትምና የወያኔን ሰላም መቃወም ተገቢ ነው። ከብዙ አገሮች ልምድ እንዳየነው አደገኛው አሉታዊ ሰላም ከመኖሩ አለመኖሩ ይሻላል። የወያኔ ሰላምም ለኢትዮጵያችን የሚበጅ አይደለም።
የግንቦት ሃያ መራራ ፍሬዎች ብዙ ናቸው።ግንቦት ሃያ የህዝብ ጠላት መሆንን የመረጠ ጉጅሌ የአገሪቷን ስልጣን የተቆጣጠረበት ቀን ነው።ከዚህ ቡድን የሚጠበቅ መልካም ፍሬ የለም። ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነት እና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ግንቦት ሃያ ቀን የአገሪቷን ስልጣን የተቆጣጠረው የጉጅሌው ቡድን ከህግ በታች እንዲውል ለማድረግ ትግላችንን አጠናክረን እየቀጠልን ነው። የትግላችን መዳራሻም የህዝብ ጠላት መሆንን የመረጠ ቡድን መሪዎች እጅ ተይዞ ለፍርድ እስከሚቀርብ ድረስ ይዘልቃል። ይሄም ያለምንም ጥርጥር ይሆናል።
እናሸንፋለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

Monday, June 2, 2014

U.S. Warns of Possible Terror Attack in Ethiopia

Addis Ababa — The US Embassy in Addis Ababa urged American citizens residing or traveling to Ethiopia to exercise caution over a possible attack by a Somali terrorist group.
The safety advisory the embassy said was issued due to threat from Al-Shabaab against Ethiopia and western interests in Ethiopia.
Citing to multiple and ongoing credible threats, the US embassy urged its citizens to take the highest precautions to maintain their personal safety and security.
“The Embassy continues to receive credible threat reports of Al-Shabaab’s intent and capability to attack Ethiopia and western interests in Ethiopia” it said in a statement Sudan Tribune received on Sunday.
The embassy said that there have been a number of incursions along the Ethiopian-Somali border in recent weeks urging its citizens to maintain a high level of vigilance and to take appropriate steps to enhance personal security.
“While there is no known specific information regarding the timing or location of an attack, we would like to remind U.S. citizens to be especially vigilant in areas where large numbers of US and western citizens congregate, including restaurants, hotels, bars, places of worship, supermarkets, and shopping malls” the statement said.
The embassy highly recommended for Americans living in Ethiopia and those travelling to Ethiopia to enrol in the Department of State’s Smart Traveler Enrollment Program (STEP).
“The STEP enrollment gives you the latest security updates, and makes it easier for the U.S. embassy or nearest U.S. consulate to contact you in an emergency. If you don’t have Internet access, enrol directly with the nearest U.S. embassy or consulate” it added.
Ethiopia, which is a regional security partner of the United States government, has a deployed forces in war torn Somalia to help the weak government battle the Al-Qaeda-allied Al-Shabaab group.
In the past Al-Shabaab has repeatedly warned to carryout massive attacks in Ethiopia in retaliation for its military intervention and Addis Ababa takes such threats seriously.
However government officials often disclose that the country’s defence force and intelligence are capable enough to thwart Shabaab’s terror plots and to defend the country from any external enemy.
Addis Ababa says it will remain determined to keep its troops in Somalia till order, peace and security is fully restored in Somalia.
However Ethiopian opposition politicians on the contrary call on government for immediate pull-out arguing keeping the troops longer will increase the risk of retaliation attacks against the horn of Africa’s nation.
Source: SudanTribune

በእነ አቶ መላኩ ፈንታ የክስ መዝገቦች ላይ ብይን ተሰጠ

31 May, 2014
የተከሳሾች መቃወሚያ ውድቅ ሆኗል
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 15ኛ ወ/ችሎት የሙስና ክስ የቀረበባቸውን የቀድሞ ገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታንና በሶስት መዝገቦች የተከሰሱ ሌሎች ተከሳሾችን የክስ መቃወሚያና የአቃቤ ህግን ምላሽ መርምሮ በትናንትናው እለት ብይን ሰጠ፡፡ ፍ/ቤቱ አብዛኛውን የተከሳሾችን መቃወሚያ ውድቅ አድርጓል፡፡


ፍ/ቤቱ ብይኑን ከመስጠቱ በፊት ተከሳሾቹ ያመለከቱትን የክስ መቃወሚያና የአቃቤ ህግን ምላሽ አስታውሷል፡፡
በመዝገቡ 1ኛ ተጠሪ የሆኑት አቶ መላኩ በዚህ መዝገብ በቀረቡባቸው ክሶች፤ የቀረቡብኝ ክሶች በስነ ስርአት ህጉ አንቀፆች መሰረት የተሟሉ አይደሉም፣ ከባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ክስ አንስተሃል ለተባልኩት ኃላፊነት የለብኝም” የሚሉና ሌሎች መቃወሚያዎችን ያስታወሰው ችሎቱ፤ አቶ ገ/ዋህድ በበኩላቸው፤ “በተነሱና በተቋረጡ ክሶች ልጠየቅ አይገባም፤ ክሶችን እንዳነሣ አዋጁም ይፈቅድልኛል፤ ከተፈቀደልኝ ወሰን በላይ ህግ አልጣስኩም” ማለታቸውን ጠቁሟል፡፡



ሌሎች በመዝገቡ የተካተቱ ተከሳሾች “የቀረበው ክስና ማስረጃ ግልፅ አይደለም፣ በተሻረ የህግ አንቀፅ ተከሰናል፣ ኮሚሽኑ በማይመለከተው ስልጣንና በሌለው ውክልና ነው የከሰሰን፣ ክሱ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ነው” የሚሉና ሌሎች በርካታ መቃወሚያዎች እንዳቀረቡም ችሎቱ አስታውሷል፡፡
ለተከሳሾቹ መቃወሚያ ከአቃቤ ህግ ከተሰጡ ምላሾች መካከልም፤ ከማስረጃና ከክስ ጭብጥ ጋር ተያይዞ የቀረቡት መቃወሚያዎች በብይን ሳይሆን በክርክር ሂደት ነው መታየት ያለባቸው የሚለው ይገኝበታል፡፡



እነ አቶ መላኩ በእርግጥም ክስ የማንሳት ስልጣን በአዋጅ እንደተሰጣቸው የጠቀሰው አቃቤ ህግ፤ ነገር ግን ተከሳሾቹ ከተፈቀደላቸው የህግ ወሰን በላይ የተሰጣቸውን መብት ተጠቅመዋል ሲል ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ሁሉም ተከሳሾች ያቀረቡት የክስ መቃወሚያም ሙሉ ለሙሉ ውድቅ እንዲደረግለት አቃቤ ህግ የጠየቁ ሲሆን፡፡


የግራ ቀኙን መከራከሪያ ሲመረምር መቆየቱን ያስታወሰው ፍ/ቤቱም፤ በዚህ መዝገብ ላይ ክሱ መስፈርቱን አሟልቶ መቅረቡን እንዲሁም ገቢዎችና ጉምሩክ ለፀረ-ሙስና ኮሚሽን ውክልና መስጠት እንደሚችል በመግለፅ በመዝገቡ ከተጠቀሱት 93 ክሶች 90ዎቹ ባሉበት እንዲቀጥሉ ሶስቱ ተሻሽለው እንዲቀርቡ በይኗል፡፡


ፍ/ቤቱ ቀጣይ ሂደቱን ለማየት ሁሉንም መዝገቦች ለሰኔ 3 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ