Thursday, April 11, 2013

ነብር… መንግስ… ይለናል አቤ ቶክቻው


ሰሞኑን “ከሀገራችን ውጡ” ተብለው  ከሀገራቸው እና ከቤታቸው የተባረሩ ሰዎችን ጉዳይ ሳስብ፤ መንግስታችን አስሮ የሚያንገላታቸውን ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞች ጉዳይ ሳስብ፤ በየቀኑ ባህር አቋርጠው የሚሰደዱ ወግኖቻችንን ሳስብ… ሳስብ ሳስብ ሳስብ… በዛን ሰሞን ወዳጃችን ሰለሞን ሞገስ ያወጋን ጨዋታ ትዝ አለችኝ፤ እንደሚከተለው ትቀርባለች፤
በአንድ ወቅት በቻይና ውስጥ እንዲህ ሆነ አሉ፤
ሴትዮዋ በአንድ ጫካ ጥጋት ላይ ከሁለት ጨቅላ ልጆቿ ጋር ቁጭ ብላ እየዬ እያለች ታለቅሳለች፡፡ በአካባቢዋ አንድም ሰው አልነበረም፡፡ ልቅሶዋ እጅግ በበረታ ጊዜ ግን አገር አቋርጦ የሚያልፍ አንድ መኪና ድንገት አጠገቧ  ቆመ እና ከውስጡ ሰዎች ወረዱ፡፡ እዚህ ቦታ ሰው ይኖራል ብለው አላሰቡም ነበርና ሰው ማየታቸው ሲያስገርማቸው፤ የእናቲቱ ለቅሶዋ ደግሞ እጅግ አስጨነቃቸው፡፡
“ምን ሆነሽ ነው እዚህ ብቻሽን ተኮራምተሸ የምታለቅሺው…” አሏት፡፡
ጭራሽ ሀዘኗ በረታ! የሆነችውንም ዘርዝራ ስትነግራቸው እየተንሰቀሰቀች ነበር፡፡
“የጫካ ነብር ባሌን በላብኝ፤ የእርሱ ሀዘን ከልቤ ሳይወጣ ትልቁ ልጄን አሁን ነጠቀኝ አሁንም ትንሽ ቆይቶ መምጣቱ አይቀርም…” ስትል ተንሰቀሰቀች፡፡
ነገሩ በጣም ያስጨነቃቸው መንገደኞች፤ “ታድያ እዚህ ቁጭ ብላችሁ ሞታችሁን ከምትጠባበቁ ለምን ወደ ከተማ አትወጡም…?” አሏት፡፡
እርሷም፤ “ከተማማ መንግስት አለ!” አለቻቸው፡፡
ከነብር ይበልጥ ተናካሽ እና ተንኳሽ ከሆነ መንግስት ይሰውረን፡፡


Ethiopia Ranked Last in Social Progress Index


by Astrid Zweynert
Source: alertnet
ethiopian flagOXFORD, England (AlertNet) – Social progress is a powerful driver of economic prosperity, according to an index launched on Thursday, with Sweden and the United Kingdom ranked first and second and Ethiopia last.


The Social Progress Index (SPI), a new measure of human wellbeing, uses original research and data from the World Bank, the World Health Organisation and other sources to rank 50 countries on 52 indicators, including nutrition, sanitation, ecosystem sustainability and personal freedom.
“In both economic and business development, our understanding of success has been incomplete,” Michael Porter, professor at Harvard Business School, told delegates at the Skoll World Forum on Social Entrepreneurship, where the index was launched.
“Previous efforts to go beyond economic measurement alone have laid important groundwork, but we need a more holistic, comprehensive, and rigorous approach,” said Porter, a leading authority on competitive strategy who helped design the index. “The Social Progress Index is an attempt to address these gaps and opportunities.”
The global debate about development has been focused on gross domestic product (GDP), an approach that had proved insufficient, said Porter, as it provides little information about the wellbeing of a nation but focuses on economic output instead.
Some of the biggest opportunities for business are in tackling social issues and social challenges, Porter said, and the SPI could be a powerful tool in helping government, business and civil society leaders to decide which social issues to prioritise.
The Arab Spring uprisings of 2011 have illustrated the “shortcomings of economic growth as a proxy for social progress,” said Porter.
“We’ve long understood that while economic development is beneficial for social progress, generally, it’s not sufficient,” said Porter. “Separating business and competition from social progress and social issues was a big mistake.”
No country scored in the top half for all 12 components of the index, which are: nutrition and basic medical care; air, water and sanitation; shelter; personal safety; access to basic knowledge; access to information and communication; health and wellness; ecosystem sustainability; personal rights; access to higher education; personal freedom and choice; and equity and inclusion.
Germany ranked fifth, the United States sixth, and Japan eighth, enjoying nearly double the score of the countries at the bottom of the table, which – apart from Ethiopia – include Nigeria and Uganda.
A low ranking on environmental sustainability (48) pulled down the United States’ overall ranking in the index. Other resource-rich countries, such as Australia and Canada were also poorly placed for environmental sustainability (46 and 47 respectively).
The index showed that it is possible to achieve a high level of social progress at a relatively modest income level, provided that effective policies are in place to tackle social issues.
Costa Rica, ranked 12 overall, delivered the highest social progress at the lowest average income level. China, at 31, fell down on opportunity, while Russia, at 32, got low marks on meeting basic needs. Low marks on safety hit the ratings of countries such as Mexico and South Africa.
Ghana and Nigeria are similar in size, but Ghana is shown to be more effective in terms of achieving progress.
Other indices used to measure a nation’s wealth and wellbeing include the United Nations Human Development Index, the Legatum Prosperity Index and the OECD’s Better Life Index.
In comparison, the SPI separates economic growth from human wellbeing, treating prosperity as a means to social progress, not an end in itself. It counts only social outcomes, or results, rather than inputs, such as health care spending or public policy.
Health spending does not have a strong correlation with health outcomes, according to the index. The United States, which has the highest per capita spending on health care, ranked only 11th on health and wellness, behind Canada, which ranked 4th overall.
Rwanda ranked 46th overall but was ninth in primary school enrolment. Mozambique, in 47th place overall, ranked 14th in equality and inclusion. India ranked the lowest (43) of all Asian countries.
A new organisation, the Social Progress Imperative, has been created to support the development of the SPI and help to integrate it into corporate and governmental thinking. The Social Progress Imperative is backed by the Skoll Foundation, Cisco, Deloitte, Compartamos Banco, and Fundación Avina.

Wednesday, April 10, 2013

Attack on Ethiopian diaspora planned

LONDON - A 52-page document secretly prepared by the Directorate of the Diaspora of the Foreign Ministry in Addis Ababa details step-by-step instructions of how to control Ethiopian Diaspora through the instrumentalities of embassies and consulates. The document is signed by one called Wubshet Demissie, an ambassador. A few of duties of the Directorate of the Diaspora are
"Amnesty International considers these defendants (who are leaders of the opposition Kinijit) -- arrested in connection with demonstrations in November 2005 -- prisoners of conscience who have not used or advocated violence and calls on the Ethiopian government to release them immediately and unconditionally." - Amnesty International: May 16, 2006

  1. To weaken the extremist opposition camp of the Diaspora; leaders of that group should be carefully studied and their names be forwarded to the Head Office
  2. Depending on the instruction from the Head office, a lawsuit should be filed against the extremists for crimes of genocide, treason, corruption and embezzlement at the time of their living in Ethiopia.
  3. Each and every member of the mission should make sure those accused of treason, genocide and embezzlement be presented before court, after gathering enough evidences.
  4. A strong tie should be forged with the governments of those countries where the extremists live in order to secure their deportation to face the court of law. It is also vital that government agencies be told their continues granting of residence to the extremists would spoil the diplomatic relationship between their country and Ethiopia.
  5. If the extremists have taken citizenship of that country of their domicile, make sure to convince the government agencies of that country to stop their citizens from meddling in the internal affairs of Ethiopia.
  6. Systematically [report] to authorities that the those who live in the country and instigate violence in Ethiopia were contravening the international law.
  7. Make sure that radio programmes run by the tax-payers' money of the country where the extremists reside should not be used to destabilise Ethiopia.
  8. Those who had applied for asylum and living in the country should be confined in one city, therefore the Mission should make every effort that this be achieved. through diplomatic means.

June 13, 2006


በጉዲፈቻ ስም ህጻናትን መሸጥ እንደቀጠለ ነው

Adoptions from the the Enat Alem orphanage in Ethiopia.

ECADF News– ኢትዮጵያ ዉስጥ ህጻናትን በጉዲፈቻ ስም ለፈረንጆች አዘጋጅተው ከሚያቀብሉት የንግድ ድርጅቶች አንዱ “እናት አለም ወላጅ አልባ ህጻናት” ወይም “Enat Alem orphanage” ቀደም ሲል ድርጅቱ ህጻናቱን ምግብ በመከልከል፣ ሲታመሙ ተገቢውን ህክምና ባለመስጠትና በአጠቃላይ ለህጻናቶቹ እንክብካቤ ባለማድረግ ስሙ የተነሳ ሲሆን… አሁን ደግሞ የተገኙት መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ድርጅቱ ድሀ እናቶችን እያፈላለገ ልጆቻቸውን “በእናት አለም ወላጅ አልባ ህጻናት” በኩል ጉዲፈቻ እንዲሰጡ እንደሚያግባባ ተደርሶበታል።

ከድርጅቱ ሰራተኞች አንዱ ግርማ ቀበለ በ“እናት አለም ወላጅ አልባ ህጻናት” የጥበቃ ሰራተኛ ሲሆን ለሲውዲን ጋዜጠኞች እንደተናገረው… ሌሊቱን በየመንደሩ እየተዘዋወረ ደሀ እናቶች ልጆቻቸውን ለፈረንጆች ጉዲፈቻ እንዲሰጡ እንደሚያግባባና እስካሁን በ145 ጉዲፈቻዎች ውስጥ እጁ እንዳለበት ተናግሯል።

የወያኔ ባለስልጣናት ተሯሩጠው የተጋለጠውን ድርጅት ዘግተውታል፣ ይሁንና አብዛኞቹ በጉዲፈቻ ስም ህጻናትን ከድሀ እናቶች ላይ ወስደው በመሸጥ ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች ስውር የወያኔ ባለስልጣናት እጅ እንዳለባቸው ይጠረጠራል።

በርካታ የመብት ተሟጋች ኢትዮጵያውያን ድርጊቱን አምርረው ያወግዙታል። ነዋሪነቱ በኖርዌይ የሆነው ሀያሲ (blogger) ጌታባለው በቀለ፣ ሰሞኑን “ከኮለኔል መንግስቱ እና ከአቶ መለስ ለኢትዮጵያ ሕፃናት አባት በመሆን ፋውንዴሽን ሊመሰረትለት የሚገባው ማነው?” በሚል ርዕስ ባስነበበው ጦማሩ እንዲህ ብሎ ይጠይቃል “ሕፃናት አሳዳጊ የሚያጡት ባብዛኛው የርስበርስ ጦርነት ሲኖር ወይንም ሰላም በተናጋበት ጊዜ ነው። ኢትዮጵያ ግን ጎዳና የወጡት ሕፃናቶቿ የበዙት በአንፃሩም ቢሆን ጦርነቱ ከቆመ ጊዜ ጀምሮ ነው ለምን?”።

ከዚህ ቀደም የአውስትራሊያው “ABC News” ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ቅጥ ያጣ ጉዲፈቻ ባጋለጠበት ወቅት ድረ-ገጻችን ጉዳዩን ዘግቦ ነበር። ከጥቂት ወራቶች በሗላ በዋሽንግተን ዲሲ በሚኖሩ የወያኔ አባላት በኩል የተቀጠረ ጠበቃ “የጉዲፈቻ ድርጅቱን ስም በማጉደፍ” ድረ-ገጻችንን ለመክሰስ እየተሰናዳ መሆኑን አሳወቀን። ከጠበቃው ጋር በተነጋገርንበት ወቅት “ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ስላለው በጉዲፈቻ ስም ህጻናትን የመሸጥ ጉዳይ” በአሜሪካ ፍርድ ቤቶች መነሳቱን እንደምንፈልገውና እንዲያውም የኢትዮጵያ ባለስልጣናትን የበለጠ ለማጋለጥ እንደሚረዳን አሳወቅነው ነበር። ይሁንና ጠበቃው በጉዳዩ ዙሪያ ተመልሶ አላነጋገረንም።


Friday, April 5, 2013

ጥልያን በመድፍ በመትረየስ በአውሮፕላን ሊገድለው ያልቻለውን ጀግና በቅናት የተነሳሱ መቀኞች የሸረቡት ገመድ ገደለው


በላይ ዘለቀ ጀግና ብቻ አልነበረም፡፡ ባንዳነትን አድረባይነትን ሎሌነትን አጥብቆ ይጠላም እንደነበር ከዚህ ታሪኩ መረዳት እንችላለን፡፡ “….በላይ ዘለቀ ተኩሶ አይስትም ::ፍጥነቱ ደሞ ሲደግንና ሲተኩስ እኩል ነው ::ውጊያ ሊጀምር ሲል “እኔ ሳልተኩስ እንዳትተኩሱ ” ብሎ ያዛል ::አንዳንድ ጊዜ በውጊያ ሰአት “እርስዎ እዚህ ይቆዩን ” ሲሉት “ምን ?” ይላል ቁጣ እየጀመረው ::”እርስዎ ከወደቁ መሪ የለንም ” ሲሉት “ወይድ ! እኔ አሮጌ ነፍጠኛ ነኝ ::”ይልና ግንባር ይጋፈጣል :: በላይ ዘለቀ እራሱ ሲዋጋ “ገምባው ” ይተበባለው ጥሩንባው ይነፋል ::”ገምባው “ባንዳን ያስበረግጋል ::ጥልያንን ያብረከርካል ::

በላይ ዘለቀ የዘመኑን አስተሳሰብ በማወቁ ህዝቡን ለማስተባበር “ትልቅ ሰው ” ማስፈለጉን በመገንዘቡ እሱ እራሱ ግን ተራ ሰው በመሆኑ የንጉስ ተክለሀይማኖት ሀረግ ለሆኑት ለልጅ ሀይሉ በለው ደብዳቤ ጻፈላቸው :: የደብዳቤው ሀሳብ ባጭሩ “ህዝቡን ለማስተባበር እርስዎ የበላይ ሆነው እነን የጎበዝ አለቃ ይሹሙኝና ጠላትን እንቋቋመው ::እኔም እዋጋለሁ ::እርስዎ ወደጦር ግንባር መድረስ አይኖርብዎትም ::” የሚል ነበር ::ደጋግሞ ደብዳቤ ጻፈላቸው ::ገጸበረከትም ላከላቸው ::…ጠመንጃ ሽጉጥ ዝናር ከነጥይቱ ሶስት መቶ ብርና ካባ :: ልጅ ሀይሉ በለው ለደብዳቤዎቹ አንድም መልስ ሳይሰቱ አንድ ቀን አንድ የትእዛዝ ደብዳቤ ላኩበት ::”ደብረወርቅ ገበያችንን ያለአግባብ ቀረጡብን ብለዋልና ከንግዲህ ቆቅ የሰገረ ወፍ የበረረ እንዳይደርስባቸው ::የተወሰደባቸውም ቀረጥ እንዲመለስላቸው ::”

በላይ ዘለቀ ተናደደ ::አብረውት የነበሩትን “ጎበዝ እግዚአብሄር የወለደው ሰው አለ ?” ሲል ጠየቀ :: “እግዚአብሄር ይፈጥራል እንጂ አይወልድም ” አሉት :: “ንጉስስ ?” “ንጉስም እግዚአብሄር ይቀባዋል እንጂ አይወልድም ::ይፈጥረዋል እንደሌላሰው ” “እኔንም ፈጥሮኛል ::ሊቀባኝ አይችልም ?” “የሱ ሀይል ካደረብዎ የፈለጉትን ማድረግ ይችላሉ ::” “እንግዲህ ከዛሬ ጀምሮ ለማንም አልታጠቅም ::” ተመስገን ፈንታ የበላይ ዘለቀ የቅርብ ጉዋደኛው ነበር ::አንድ ቀን ከጠላት በፊት ተመስገን ፈንታ በላይ ዘለቀን “ሸዋ ሄደን ለትልቅ ሰው እንደር ::እንሾማለን ;እንሸለማለን “አለው :: “እኔ ሰው ሆኜ ለሰው አላድርም “አለ በላይ ዘለቀ :: “ባንተ ተኩስ ;ባንተ ወኔ ;ባንዳፍታ ትሾማለኽ :: “ጀግንነት እደጃችን ድረስ ይመጣ እንደሆነ ማን ያውቃል ?” አለው በላይ ዘለቀ ::አመታት አለፉ ::

ሞረድ እጀ ጠባብ ካስመራ እሚመጣ አፈ ሾሌ ሱሪና ተመሳሳይ ኮኮት ጥንግ ድርብ ጥበብ ኩታ በቅሎ እንደተጫነች ጠመንጃ ከነሙሉ ዝናር ጥይት …በላይ ዘለቀ ይህንን ሁሉ አዘጋጀና ተመስገን ፈንታን ጠርቶ ; “ያ የጌታ አዳር ሄደን እንሸለማለን ያልከው ይኸውና “ብሎ ሸለመው ::በአርበኝነት ዘመን ጉዋደኛሞቹ አልተለያዩም :: በላይ ዘለቀ መጀመርያ “ራስ ” ብሎ የሾመው ተመስገን ፈንታን ነበር :: “እኔንስ ራስ አልከኝ ::አንተ ማን ልትባል ነው ?” አለው ተመስገን ፈንታ :: “እኔንማ እናቴ አንደዜ በላይ ብላኛለች ” አለ በላይ ዘለቀ ::” ……….

የበላይ መጨረሻም ይህ ሆነ፡፡ ንጉስ ሹም ሽር አደረጉ ::በላይ ዘለቀ ከወንድሞቹ ጋር ሆኖ በሁዋላም ከአገሬው ጋር ሆኖ ጠላትን ተዋግቶ ነጻ ያወጣው ጠቅላይ ግዛት ለራስ ሀይሉ ተሰጠ :: በላይ ዘለቀ ወዳዲሳባ ተጠርቶ ደጃዝማች ተብሎ የቢቸና አውራጃ ገዥ ሆኖ ተሾመ :: የቢቸና አውራዣ ገዥ ሆኖም ሊሰራ አልቻለም ::ከደብረ ማርቆስ ትእዛዝ እየመጣ ወረዳዎቹ ሁሉ ቀድሞ ባንዳ የነበሩ ሰዎች ተሾሙባቸው ::ብስጭት በዛበት በላይ ዘለቀ :: “ሊወጋን ነው ….እምቢ አለ …”እያሉ ማስወራት ጀመሩ :: በቂ ካስወሩ በሁዋላ ከራያና አዘቦ ጦር አስዘመቱበት :: (ጎጃመማ በላይ ዘለቀን ወይ ይወደዋል ወይ ይፈራዋል :: ) በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ ከጥቂት ታማኝ ተከታዮቹ ጋር ሆነው ወደ ሳማ አምባ ሸሹ ::በላይ ዘለቀ ሸፈተ ተባለ :: ሳማ አምባ ያለ ሁለት በር የላትም ሁለቱንም በር ይዘው ሀያ አምስት ቀን ሌትና ቀን ተዋጉ :: “ምረነዋል ልቀቁት ይምጣ “የሚል መልእክት ከንጉሱ መጣ :: ከሳማ አምባ ከወረዱ በሁዋላ ተከበቡና መሳሪያቸውን ተነጥቀው እንደ እስረኞች ወደ አዲስ አበባ ተወሰዱ :: በላይ ዘለቀ ሞት ተፈረደበት ::ንጉሱ “ምህረት ” አደረጉለትና ቅጣቱ ወደ እስራት ተለወጠለት ::

መስከረም 1936 አ .ም በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ በያገሩ ተበትነው ታሰሩ :: በላይ ዘለቀና ወንድሙ እጅጉ ዘለቀ ወሊሶ በበቀለ ወያ ጠባቂነት ታሰሩ :: የበላይ ዘለቀ ምቀኖች አሁንም አላረፉለትም ::በላይ ዘለቀ ከዳ ;አመለጠ ጠፋ እየተባለ ይወራ ጀመር ::በቀለ ወያ ተያዘና “ምን ቢሰጥህ ነው የለቀከው ?”ተባለ ::”እረ እኔ አልለቀኩትም አለ :::: በላይ ዘለቀና እጅጉ ዘለቀን ወደ አዲስ አበባ አመጡዋቸውና ከአንድ ሌላ ሰው ጋር አሰሩዋቸው :.ያ ሰው እናምልጥ እያለ እነ በላይ ዘለቀን ይጎተጉታቸው ጀመር :: አንድ ቀን “ጠባቂዎቻችንን የኛ ወዳጆች ገዝተዋቸዋልና እናምልጥ ::በንዲህ ያለ ስፍራ እነ እገሌ መኪና ይዘው እየጠበቁን ናቸው ::”አል :: “ወንድሞቸ በየቦታው ተበታትነው ታስረው እኔ ማምለጥ ምን ያረግልኛል ?” አለ በላይ ዘለቀ :: “ፈራህ እንዴ በላይ ዘለቀ ?”አለው :: “እኔ የዘለቀ ልጅ !” በላይ ዘለቀ ወንድሙን ላከው መኪናው እተባለበት ስፍራ መኖሩን ለማረጋገጥ ::ወንድምየው በተባለበት ስፍራ መኪና አየ ::እስረኞቹና ጠባቂዎቻቸው አብረው አመለጡ ::እመኪናው ቦታ ሲደርሱ መኪናው የለም ::እንግሊዝም የለም :: ጠባቂዎቻቸው ከዚያ ሮጠው አጠገባቸው ከነበረው ጫካ ገቡና ደጋግመው ተኮሱ ::ምልክት ነው :: በላይ ዘለቀ እጠላቶቹ ወጥመድ ውስጥ መግባቱን አወቀ :: በላይ ዘለቀና እጅጉ ዘለቀ ከዚያ እሮጠው አመለጡ :: ሰላሌ ደርሰው በቅሎ ለመከራየት ሲነጋገሩ ተከበቡ :: በላይ ዘለቀ በጦር ፍርድ ቤት ሞት ተፈረደበት ::ንጉሱ ፍርዱን አጸደቁት :: ጥር 1937:.በላይ ዘለቀ በስቅላት ሞተ ::እድሜው ሰላሳ አምስት አመት ነበር ::

ጥልያንን በመድፍ በመትረየስ በአውሮፕላን ሊገድለው ያልቻለውን ጀግና በቅናት የተነሳሱ መቀኞች የሸረቡት ገመድ ገደለው ::ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ ሰላሳ አምስት አመት ታስረው በለውጡ ተፈቱ::መልኩን ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ እንዲህ ብለው ይገልሱታል :: “አፍንጫው ሰተት ብሎ ወርዶ ቅጠሉ ነፋ ነፋ ይላል ::ከንፈሩ ከበድ ይላል ::ጠጉሩ ክርክም ጎፈሬ ጺሙ ሙሉ ለስላሳ ረጅም ጣቱ መልካም ወተት የተነከረ ነው የሚመስለው ጣቱ ::እግረ ቀጭን ::”…………..”

ዛሬም እንደዚህ ነው…. ስንት አድርባዮችና አሰመሳዮች አለን? ኑሮአችንን በሌሎች ህልውና ላይ የመሰረትን? የአፋኝ ሥርዐት ሎሌ በመሆን የወንድሞቻችንን ደም ከንቱ ያደረግን…..?

ዳምጠው ወያኔ/ኢሕአዴግና አፈና በኢትዮጵያ




በቀልድ ልጀምር፤ አንድ ጮሌ የአስመራ ልጅ የእኔ ተማሪ ነበር፤ አንድ ጊዜ የጂኦግራፊ ክፍል ተማሪዎች አንድ ጃፓናዊ አስተማሪ ለመሸኘት ግብዣ አድርገው ነበር፤ በግብዣው ላይ የጠቀስሁት ነገረኛ የአስመራ ልጅ (የአስመራ ልጅ የምለው ላርቀው ፈልጌ እንዳይመስላችሁ፤) በአስተማሪዎች ላይ ቀልድ ያሰማ ነበረ፤ ስለኔ ሲናገር፤– መስፍን ወልደ ማርያም የቢሮውን በር ሁልጊዜ ክፍት አድርጎ የሚቀመጠው ለምንድን ነው? ይልና እሱው ሲመልስ፣ በሩን የመዝጋት ሌሎች ዘዴዎች ስላሉ ነዋ! ቀልዱ ለእኔ እንደገባኝ ፊቱን ስለሚያኮሳትር ሰዎች በሩን አልፈው እንዲገቡ አይጋብዝም ማለት ነው፤ በዚያን ጊዜ እኔም እየሳቅሁ እንደተናገርሁት የሱን ፈሪነት በእኔ መልከ-ክፉነት መደበቁ ነው፤ ቀልዱን ያመጣሁበት ምክንያት ወያኔ ለነጻነት የቆመ መስሎ ለመታየት ሳንሱር የሚባለውን የሚታተሙ ጽሑፎችን በቅድሚያ የማስፈተሽ ቀንበር በሕግ አነሣ፤ ሰዎች እውነት መስሎአቸው ቅሪታቸውን እያነጠፉ ጋዜጦችና መጽሔቶችን ማሳተም ጀመሩ፤ ጋዜጦች እንደአሸን ፈሉ፤ መጻሕፍት ታተሙ፤ ጥቂት ቲያትሮችም ታዩ፤ ዘፈኖች ተመረቱ! ነገር ግን የግል ራድዮና ቴሌቪዥን እንዲሁ የብዙ ሰዎች ሕልም ሆኖ ቀረ፤ ብዙ ሰዎች ብዙ ገንዘብ ከሰሩ፡፡

በሕዝቡ ዘንድ የነጻነት ፍቅር እየለመለመ መሄዱን ሲያየው ወያኔ ሆዱ ተንቦጨቦጨ፤ እንቅልፍ እያጣ ሄደ፤ ቀስ በቀስ ግራ እጁን በሕገ መንግሥቱ ላይ ጭኖ በቀኝ እጁ ጎራዴውን መዘዘ፤ ቀስ በቀስ፣ አንድ በአንድ የተለያዩ መብቶችን ለማስከበር የቆሙትን አንቀጾች ሁሉ አስተኛቸው፤ በተገላቢጦሽ መብቶቻቸውን የሚጠይቁ ሰዎችን፣ ስለመብቶች የሚጽፉ ሰዎችን፣ መብቶችን ከጥቃት ለመከላለከል የቆሙ ድርጅቶችን፣ ከወያኔ አመለካከት ውጭ የሆኑ ሰዎችን ሁሉ መንግሥት በመገልበጥ ሴራ፣ ወይም በሽብርተኛነት እየያዘና እያሰረ በመክሰስና በማስፈረድ የማፈን እርምጃዎችን ሁሉ አጠናከረ፤ አንዲህ ያለውን አፈና ማየትና መስማት እየተለመደ መጣ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በሽብር ስም የሚካሄደው ጥቃትና የሰብአዊ መብቶች ረገጣ እንኳን እኛንና በሽብር ላይ ዓለም-አቀፍ ጦርነት ያወጁትን አሜሪካኖችንም እያስደነገጠ ነው፤ የዓለም የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ሁሉ፣ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ በምሬት እየጮሁ ነው፤ ጋዜጠኞች፣ የሠራተኞች ማኅበሮች፣ የፖሊቲካ ቡድኖች ጭጭ እንዲሉና ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ መንገዱ ሁሉ እየተዘጋባቸው ነው፤ በትግራይ አብርሃ ደስታ የሚባል ወጣት የአፈናውን ድቅድቅ ጨለማ ጥሶ በመውጣት ስለጻፈ አፈናና ማስፈራራት ደረሰበት፤ ‹‹ጭቆናን ስላጋለጥሁ የሕዝብ ጠላት ተባልሁ›› ይላል፤ በቅርቡ እንኳን ሰማያዊ ፓርቲ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል የጠራው የራት ግብዣ እንግዶቹ በተጠሩበት ሰዓት ተሰርዞ ተመልሰዋል፤ ለግራዚያኒ ስለሚሠራው ሐውልት የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የሞከሩ ኢትዮጵያውያን ታሰሩ፤ እነዚህን ኢትዮጵያውያንን ያሰሩትን ምን እንላቸዋለን? እንግዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ ምን የማያሳስር ነገር ሊኖር ይችላል?

የአፈናውን ነገር እነእስክንድር ነጋ፣ እነርእዮት ዓለሙ፣ ውብሸት ታየ … ይመሰክራሉ፤ ለመሆኑ ወደዘጠና ሚልዮን የሚሆን ሕዝብ ያላት አገር ስንት ጋዜጣ፣ ስንት የራድዮ ጣቢያ፣ ስንት የቴሌቪዥን ጣቢያ አላት? ኤርትራ ሦስት የራድዮ ጣቢያዎችና ስድስት ጋዜጦች፣ ጂቡቲ ሦስት የራድዮ ጣቢያዎችና አምስት ጋዜጦች፣ ኬንያ አሥራ ስምንት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ ከሠላሳ በላይ የራድዮ ጣቢያዎች፣ ዘጠኝ ጋዜጦች አሉት፤ ትናንት የተፈጠረው ደቡብ ሱዳን እንኳን ሁለት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ አምስት የራድዮ ጣቢያዎች፣ አምስት ጋዜጦች አሉት፤ ኢትዮጵያ ያላትን እናውቃለን፡፡

ሰንጠረጅ አንድ
የኪስ ስልክ (ሞባይል) እድገት
እ.አ.አ.2008200920102011
አገሮች     ሞባይል ለ100 ሰዎች
በደቡብአፍ
91
93
100
127
ኢትዮጵያ
2
5
8
17
ኬንያ
42
49
62
65
ሱዳን
29
36
42
56
ኤርትራ
2
3
4
4
ሶማልያ
7
7
7
7
ጂቡቲ
13
15
19
21

ምንጭ፡- የዓለም ባንክና የዓለም ቴሌኮሚዩኒኬሽን ድርጅት

የአፈናውን ልክ በሁለቱ ሰንጠረጆች ማየት ይቻላል፤ ለንጽጽር የቀረቡት አገሮች የአፍሪካ ቀንድ ጎረቤቶች ናቸው፤ ነገር ግን ላቅ ያለ ግብ ለማመልከት ደቡብ አፍሪካ ተጨምሮአል፤ ለምሳሌ የኪስ ስልኩን ብንወስድ በደቡብ አፍሪካ በመጀመሪያው ዓመት እአአ በ2008 ለአንድ መቶ ሰዎች 91 የኪስ ሰልኮች ነበሩ በ2011 ለመቶ ሰዎች ወደ አንድ መቶ ሃያ ሰባት ደረሱ፤ ይህም አንዳንድ ሰዎች ከአንድ በላይ የኪስ ስልክ አላቸው ማለት ነው፤ከጎረቤቶቻችን መሀል ኬንያ በ42 የኪስ ስልኮች ለአንድ መቶ ሰዎች ጀምሮ በአራተኛው ዓመት ላይ ወደስድሳ አምስት ማደጉ ይታያል፤ ሱዳንም ከሃያ ዘጠኝ ተነሥቶ በአራተኛው ዓመት ወደሃምሳ ስድስት አድጎአል፤ ጂቡቲም ከ13 ጀምራ ወደ 21 ገብታለች፤ ትልቅዋ አገር ኢትዮጵያ በሁለት ጀምራ ከአራት ዓመታት በኋላ ለመቶ ሰዎች አሥራ ሰባት የኪስ ስልኮች አስቆጥራለች፤ በአፍሪካ ቀንድ በኪስ ስልክ የመጨረሻውን ዝቅተኛ ቦታ የያዘች አገር ትልቅዋና በዓመት ከአሥራ አንድ ከመቶ በላይ እድገት ታስመዘግባለች የሚባልላት ኢትዮጵያ ነች፡፡

ሁለተኛው የአፈናው መገለጫ የኢንተርኔት አገልግሎት ነው፤ በኬንያ በ2008 ከአንድ መቶ ሰዎች ውስጥ የኢንተርኔት ተጠቃሚ የነበረው 42 ሲሆን በ2011 ወደ ስድሳ አምስት አደገ፤ በኤርትራ ከ4 ወደ 6 ሲያድግ፣ በኢትዮጵያ አላደገም፡፡

እነዚህ ሁለቱም የመረጃና የእውቀት መተላለፊያ ዘዴዎች ለማናቸውም እድገት ቁልፍ መሆናቸው አያጠራጥርም፤ በተለይም ለነጻነትና ለእውቀት እድገት አስፈላጊዎች በመሆናቸው ለአምባ-ገነኖች እንደጠላት መሣሪያ የሚቆጠሩ ናቸው፤ ችግሩ እውቀት አለነጻነት አይገኝም፤ ነጻነትም አለእውቀት አይገኝም፤ እውቀትና ነጻነት ተነጣጥለው አይገኙም፤ ስለዚህም ነጻነትን ለመግደል የፈለገ እውቀትንም ይገድላል፤ ስለዚህም አምባ-ገነኖች ሞባይልንና (ተንቀሳቃሽ ወይም የኪስ ስልክ) ኢንተርኔትን ማፈን ዋና ተግባራቸው ያደርጉታል፤ በዚህም ምክንያት ሕዝቦቻቸውን በድንቁርና ያዳፍናሉ፤ በደሀነት ያሰቃያሉ፤ በዘመናችን ዋናው የአውቀት መተላለፊያ ኢንተርኔት ነው፡፡

ሰንጠረጅ ሁለት
የኢንተርኔት አገልግሎት እድገት
እ.አ.አ.2008200920102011
አገሮችየኢንተርኔት አገልግሎት ለመቶ ሰዎች
ደቡብአፍ8.510.118.120.9
ኢትዮጵያ0.50.50.81.1
ኬንያ42496265
ሱዳን10.2
ኤርትራ4.14.95.46.2
ሶማልያ1.11.21.3
ጂቡቲ2.34.06.57.0
ደቡብ አፍሪካ የገባው ለንጽጽር ነው፤


ምንጭ፡- የዓለም ባንክና የዓለም የቴሌኮሚዩኒኬሽን ድርጅት

የኢንተርኔት አገልግሎት በቅርቡና በርካሽ ወይም በነጻ ከተገኘ ብዙ ሳይለፉ ምንም ዓይነት እውቀት ሊገኝ ይቻላል፤ በሠለጠኑት አገሮች በአንዳንድ ቡና ቤቶች ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት ይገኛል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በኢንተርኔት ለመጠቀም ደህና ገቢ ያለው መሆን ያስፈልጋል፤ከደሀነት ለመውጣትም ሀብታም መሆን ያስፈልጋል!



መስፍን ወልደማርያም
መጋቢት 2005