Thursday, November 21, 2013

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝ ከቁራና ከዳዊት የቱን ይመርጣሉ?


አልፎ አልፎ ጠዋት የማገኛቸው የማኪያቶ ቡድን አለ፡፡ በፓርላማ ሰለነበረው ውሎ መሠረት አድርገው የግል አሰተያየት ይሰጣሉ በዚህ መሃል አንዱ ምሳሌያዊ ንግግር አደረገ ወደድኩትና ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡ ቁራ ታውቃላችሁ በተለይ መሬት ላይ በእግሯ ስትሄድ አታምርም ይህ ችግር እንዳለባት ታውቃለች፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የእርግብ አካሄድ ይማርካታል፡፡ አካሄዷን ለማሳመር እንደ እርግብ መሄድ ይኖርብኛል ብላ ወሰነችና ልምምድ ጀመረች፡፡ አስር ዓመት ሙሉ ቤት ዘግታ ስትለማመድ ቆይታ ሳይሳካላት ይቀርና ተስፋ በመቁረጥ አንድ ውሣኔ ላይ ትደርሳለች ቢያስጠላም በራሷ በቀድሞ አካሄድ እንደ ቁራ ለመሄድት ወስናለች፡፡የሚያሳዝነው ነገር ግን የእርግብንም ሳትለምድ የራሷም የቁራ አካሄድ ጠፋባት፡፡

የዚህ ምሳሌ መነሻ የሆኑት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝ ናቸው፡፡ በምክር ቤት ውስጥ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ለመምሰል ሲያደርጉ የነበረውን ሙከራ የትዝብቱ አንድ አካል ነው፡፡ በዚህ ዕይታ ሙሉ በሙሉ ባልስማማም ፍፁም ውሽት ነው ራሳቸውን ነበር የነበሩት ብዬ ልከራከር አልችልም፡፡ እኔም የሆነ ነገር ታይቶኛል፡፡ ስለዚህ ይህ ማሳሰቢያው አቶ ሀይለማሪያም መለስን ላይሆኑ ሀይለማሪያምን እንዳያጡት የተሰጠ ምክር በመሆኑ በበጎ ወስጀዋለሁ፡፡
የተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝ በደንብ በሚያውቁት አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ላስረዳ፡፡ መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ 17 ዝርዝሩን ማየት ይቻላል በአጭሩ ታሪኩ የጎሊያድና የዳዊት ነው፡፡ ንጉስ ሳኦል ዳዊት ጎልያድን ለመግጠም ይመረጥና ይልከዋል ወደ ፍልሚያው ሊገባ ሲል፤ ሳኦል ለዳዊት እንዲጠቅመው በሚል የንጉሱን ካባና ንጉሱ በጦርነት ጊዜ የሚጠቀምበትን ዋነኛ መዋጊያ የሆነ የናስ ቁር ደፋለት፤ ጥሩርም አለበ ሰው፡፡ የንጉሱን ልብስ ለብሶ መንገድ ሲጀምር አልተመቸውም አውልቁልኝ ብሎ አወለቀው፤ በማስከተልም የተሰጠውን ትጥቅ ይቅርብኝ ብሎ ወንጭፌን አምጡ አለ፡፡ ከዚያም ብዙዎቹ በዚህ አለባበስና በወንጭፍ እንዴት ጎልያድን የሚያክል ግዙፍ ሰው ለማሸነፍ እንደሚችል ሲጠየቅ ጎልያድ እንደምታዩት ትልቅ ነው (የጎልያድ ቁመት ከስድስት ክንድ በላይ ነው) ለኔ ጎልያድን መምታት ሳይሆን መሳት ነው ከባድ ይላቸዋል፡፡ ግጥሚያው ሲጀመርም ዳዊት ጎልያድን በወንጭፍ ግንባሩን ብሎ ጣለው፡፡ እንዳለውም ጎልያድን መምታት ሳይሆን ከባድ መሳት ከባድ መሆኑን አስመሰከረ፡፡ ዳዊት ያደረገው ከንጉሱ ካባ ይልቅ የራሱ ደበሎ፤ ከንጉሱ ዘመናዊ መሳሪያ ይልቅ የራሱ የሚያውቀው ወንጭፍ እንደሚሻል አሰመሰከረ፡፡ እዚህ ጋ ለአቶ ሀይለማሪያም የተላለፈው መልዕክት የንጉሱ ሌጋሲ ማስጠበቅ በሚል ሳይሆን በራሳቸው ደበሎና ወንጭፍ እንዲጠቀሙ ለማሳሰብ ነው፡፡
እነዚህ ሁለት ምሳሌዎች ለአቶ ሀይለማሪያም በጣም ጥሩምሳሌዎች ናቸው፡፡ ምርጫው እንደ ቁራዋ ሌላ ለመሆን ሞክሮ እራሳቸውንም መሆን አቅቶዋቸው ሳይሳከላቸው መቅረት ወይም እንደ ዳዊት የንጉሱን ትተው እራሳቸውን መሆን ነው፡፡ ምርጫው የግል ነው የኛ ጉዳይ መምከር ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እራሳቸውን እንዲሆኑ የምፈልግበት አንድ ሁለት ነጥብ ላንሳላችሁ አንድ የፕሬስ ህግ የመናገርና ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት የንግድ ህግ መሆኑን አናውቅም ነበር፡፡ እነዚህ ድንጋጌዎች በንግድ ህግ ብቻ የሚጠቀሱ ቢሆን ኖሮ በፍትሕ ብሔር ህግ እንጂ በህገመንግስት ውስጥ የሚጠቀሱ አይሆኑም ነበር፡፡ የህገ መንግሰቱን አንቀፅ 29/2 እና ሌሎችም ድንጋጌዎች እንዳይሸራረፉ መጠየቅ በንግድ ህግ እንዲታይ ማለት ተገቢ አይደለም፡፡
ነጋዴዎች የያዙትን የንግድ ቤት በሽያጭ ይተላለፍ የሚል አስተያየት ሲሰጥ ይህ ዓላማው ድሃው እንዲኖርበት ነው ማለት የእውቀት ሳይሆን ጉዳዩ ሌላ ነው ፣ ድሃው የሚኖርበት ቤትም ቢሆን ለድሃ በይዞታነት ይተላለፍ ማለት ይቻላል፡፡ በጥያቄ የቀረበላቸው ግን ነጋዴዎች እየነገዱ ያሉበትን ቤት ባለቤትነት አዛውሩና ገንዘብ ተቀበሉ፡፡ የተቀበላችሁን ገንዘብ ደግሞ ለኢንቨስትመንት አውሉት ማለት ለወዳጅ የተሰጠ ምክር ነው፡፡ ልብ ብለው ያድምጡኝ ይህ ምክር ከተቀናቃኝም ቢሆን ሊታሰብበት የሚገባ ነው፡፡ ለነገሩ ዓላማው እራሱን ችሎ የሚኖር ነጋዴንም ቢሆን በጭሰኝነት መያዝ እንደሆነ ያስታውቃል፡፡ ለነፃነት ስንል ጫካ ገባን የሚል ቡድን የዜጎቸን ነፃነትን ለመገደብ ምንም መንገድ እንደሚጠቀም ማሳያነው፡፡ ይህ ደግሞ ጫካ የመግባታቸው ሚስጥር ለነፃነት ነበር የሚለው ነጭ ውሽት እንደሆነ መረዳት ከበድ አይሆንም፡፡ ነፃነትን የሚያከብር ቡድን በምንም ዓይነት የሌሎችን ነፃነት በቁሳዊ ጉደይ ለመያዝ አይጥርም፡፡ ነፃነት የማያውቅ ነፃ አውጭ የሚለው የሚገልፃችሁ ይመስለኛል፡፡
 ግርማ ሰይፉ
girmaseifu32@yahoo.com

Wednesday, November 20, 2013

HOW LONG DOES THE ETHIOPIAN SOCIETY TREAT JUST SYMPTOMS AND NOT THE ROOT CAUSE?


November 19, 2013
by Kibru Demeke
Extremely Upsetting!
These past few days we Ethiopian people have been screaming our lungs out en mass all around the world in almost all continents – even in Saudi Arabia itself and Beirut -  protesting the inhumane acts being deliberated on our fellow citizens. Needless to say, the only country that crashed the attempts to protest against this crime on humanity is Ethiopia herself.
In my half a decade years stay in the U.S. I have never seen or heard a gathering this big and a movement this large all over the world. Only the May 2005 election massacre protest might beat or equal it.
Clearly we are extremely angry to our nerves. And we should be.
What is Causing This?
However, how many of us took time to think what actually caused this – the intentional targeted brutal attacks on Ethiopians in Saudi Arabia (and elsewhere)? In other words, what is the CAUSE of this shame brought on our nation? I heard several people from different spectrum of life say “poverty is the cause.” I would say NO! Poverty, backwardness, etc are all the SYMPTOMS. In fact what has been happening to Ethiopians in Saudi Arabia is a SYMPTOM. A symptom of what? What is the cause then!? Good question to ask really.
Now it is of high importance to ask oneself “WHY HAVE WE ALWAYS BEEN TREATING THE SYMPTOMS AND NOT THE CAUSE?” This question always challenges me. By the way the only difference between this current mishap on Ethiopians in Saudi Arabia and what has been going on since the mass migration has began 22 years ago is that, on the former, the Saudi government took a wide-ranging campaign of rounding up migrant workers as a national program and the maltreatment affected all migrant workers largely targeting Ethiopians.
Symptoms
For over two decades every single day, several Ethiopian migrant workers have been beaten, tortured, killed and driven into mental disorder in Arab countries. Former Ethiopian Airlines flight crew told me they do not like to operate the Arab bound flights due to its horrific scene in-flight. Sometimes they transport a full plane half of the passengers that went mental and screaming for the whole duration of the flight. This is to say that this SYMPTOM has been there and will be there unless the CAUSE is treated and taken care of.
So these horrendous crimes on Ethiopians have been happening for over two decades especially in Arab countries. It is happening as we speak.
Going back to what I initially was saying, the persistence, massiveness, and globalization of the organized protests are bringing attention to prominent media, human rights institutions, influential governments and entities. It is also exposing the Saudis’ serious crimes against humanity to the open world and that might give our fellow compatriots some relief when Saudi tries to save its face. However it may not completely deter them from continually tormenting our citizens.
Therefore, it is necessary and of utmost urgency that the sub-human conditions on fellow citizens suffering in Saudi Arabia stops and measures taken to transport them to safety either back home or accommodating countries through refugee and/or asylum as appropriate. Most agree that this should not be a campaign but a movement until all our citizens are rescued to safety.
Cause!
The cause has always been BAD GOVERNANCE in general and the TPLF/EPRDF led “government” in particular. Here we are not even going to try to state the obvious that there is a “government” that has completely gone wrong in Ethiopia – unless we are in a complete delusional state and self denial crisis. In fact, I’d love to be off the conventional term “Bad Governance” for the Ethiopian case and call it “Nasty Governance” since that is what it is. Not out of hatred but sincerity.
Whom to Battle?
But there is no guarantee whatsoever that this won’t happen again in Saudi Arabia, Yemen, United Arab Emirates, Kuwait, Lebanon etc. Well in fact there are unheard voices of Ethiopians under extreme inhumane condition in those countries I just mentioned and beyond. Are we going to go out for demonstration all year round all over the globe? We all know that is not possible. But we can do what is possible – to address THE MOTHER OF ALL THE SYMPTOMS – THE CAUSE!
Again no wasting time stating the obvious fact that the TPLF led absolute dictatorship that is ruling our country by gun point for the past 22 years is the root cause for citizens to fall in despair and leave their country to seek domestic work in brutal Arab states. Not to mention all other turmoil, in all aspects of the nation and the society caused by this illegitimate regime that is leading Ethiopia and its people to the demise of catastrophe.
The battle on the frontline must be to end the cause by any means possible. The mother cause of all catastrophes to our nation’s and people is the TPLF/EPRDF led regime. The system must be dismantled, the regime fallen, and the perpetrators face justice.
Whose Problem?
It is evident that majority of the Ethiopian peoples’ lives both at home and abroad has been severely affected by the current state of our country. Our sovereignty as a nation, our unity as people, and our pride as Ethiopians is going down the drain. Our citizenship is in question. Every single one of us, as citizens, has responsibility of getting ourselves out of this disaster.
And there’s only one way of doing that – by treating the root cause. And that, in plain language is, ending the TPLF led rogue regime.
My most favorite verse from William Shakespeare’s Hamlet play goes as:
To be or not to be, that is the question:
Whether ‘tis Nobler in the mind to suffer
The Slings and Arrows of outrageous Fortune,
Or to take Arms against a Sea of troubles,
And by opposing end them

ነፃነት ያለ ደም …. ክብርስ ያለ መስዋዕትነት እንዴት ሊገኝ ይችላል?


የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል በሰሜን አሜሪካ፣ ነፃነት ያለ ደም …. ክብርስ ያለ መስዋዕትነት እንዴት ሊገኝ ይችላል?

November 20, 2013

የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል በሰሜን አሜሪካ

በሳውዲት አረቢያ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ እየተካሄደ ያለውን አሰቃቂ ግድያና ሰቆቃ አጥብቆ ያወግዛል !
አድዋ ላይ የፈሰሰው ደም ፣ በማይጨው የተከሰከሰው አጥንት ፣ በመተማ ግንባር ላይ የተቀላው አንገት ፣ በዶጋሊ በደም የተፃፈው ጀግንነት …… ለግል ታሪክ ማዳመቂያ ሳይሆን እኛ ኢትዮጵያኖች በገዛ አገራችን በባርነት ቀንበር ስር እንዳንማቅቅና በነፃነት ተከብረንና ኰርተን እንድንኖር አድርጐናል ።
ዘርዓይ ደረስ ለአገሩ ባንዲራ የከፈለው መስዋዕትነት …. አብዲሳ አጋ ያስመዘገበው ወደር ያልተገኘለት ጀግንነት …. አብረሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በየካቲት አስራ ሁለት ጀነራል ግራዚያኒ ላይ የቃጡት ጥቃት ፣ አቡነ ጴጥሮስ ለህዝባቸውና ለአገራቸው ክብር ሲሉ ነፍሳቸውን መስጠታቸው እኛ ልጆቻቸው ፣ የልጅ ልጆቻቸው ባለ አገርና ያልተገደበ ነፃነት እንዲኖረን ነበር ።
የኦጋዴንን ድንበር ሰብሮ በመግባት …… ልጆቻችንን ፣ ሚስቶቻችንና እናቶቻችንን እፊታችን ስር ሊደፍርና ሊያዋርድ የመጣውን እብሪተኛ ጦር እውነተኛው ኢትዮጵያዊው ሰራዊት በሰማይ ፣ በባህርና በምድር ተሞ ድባቅ መምታቱ ባንዲራችንን የሰንደቆች ሁሉ አውራ አድርጓት ኖሯል ።
ታዲያ ዛሬ ያ ! ሁሉ የዜግነት ክብር እንዴት ተናደ ? ዜጐቻችን ባባህር ሲያቋርጡ የአሳ ነባሪ እራት ለምን ይሆናሉ? እህቶቻችን የፈላ ዘይትና ውሃ በአካላቸው ለምንስ ተቸለሰባቸው ? ከፎቅ ላይ እራሳቸውን እያምዘገዘጉ ለምን ጣሉ ? በጠራራ ፀሃይ በመሃል ከተማ ውስጥ የድረሱልኝ እሪታ እያሰሙ እንደ በግ መሬት ለመሬት ሲጐተቱና በመኪና መስኰት እንደወረቀት እያጣጠፉ በግድ ሲጭኗቸው በገሃዱ አለም ለምን አየን ? ሳውዲት አረቢያ ለዜጐቻችን የምድር ሲዖል ለምን ሆነች ? ወንድሞቻችን እንደ ረከሰ ውሻ ያለርህራሄ ተቀጥቅጠው ሲሞቱ በዓይናችን በብረቱ አየን ። ሰንደቅ ዓላማችንን በአናቱ ላይ ያሰረው ወንድማችን እንዲሁ ምህረትን እንደተማፀነ ነፍሱ ከስጋው ስትለይ በሰቀቀን ተመለከትን …… ገዳዮቹ ውሻው አበሻ (ኢትዮጵያዊ) ሞቷል እያሉ ሲሳለቁበት እርር ድብን እያልን ተከታተልን ።
እህቶቻችን አይናችን ፊት በጐዳና ላይ ለአምስትና ለአሥር ሆነው ሲደፍሯቸው ተጐልተን እያየን በቁጭት አነባን ።
አባችቶቻችን ያቆዩልንን አኩሪ ነፃነት መጠበቅ አቅቶን በባርነት በተሸጥንበት አገር የውሻ ስም ተሰጥቶን የውሻ ሞት ሞትን። ከዜጐች ሁሉ መጨረሻ የተናቅንና የተዋረድን ሆንን ።
እነሆ የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል በሰሜን አሜሪካ ይህንን በህዝባችን ላይ እየተፈፀመ ያለውን አሰቃቂ ፍጅት አጥብቆ እያወገዘ ፤ ለዚህ ሁሉ ውርደትና ሥቃይ የዳረገንን ዘረኛ መንግስት ተጠያቂ ያደርጋል ።
የኢትዮጵያ ሰራዊት ሆይ ስማ ! አገርህ ኢትዮጵያ ናት ፣ ህዝብህ ኢትዮጵያውያን ናቸው ።
የኢትዮጵያ ሰራዊት እንጂ የዘረኞች የግል ዘበኛ አይደለህም ።
ህዝብህ ተዋርዷል ! ዜግነትህ ከእንስሳ ባነሰ በቁሻሻ ላይ ተጥሏል ። እናትህ ፣ አባትህ ፣ ወንድምህና እህትህ ከለላና መከታ አጥተው ደማቸው በየጐዳናው እየፈሰሰ ይገኛል። የህዝብህን ዋይታ ስማ !
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል በሰሜን አሜሪካ
Source, ECADF

Sunday, November 17, 2013

ይድረስ ለኢትዮጵያ ፖሊሶችና የመከላከያ ሰራዊት አባላት


November 16, 2013

በየቦታው ተበትናችሁ ለአገር የሚበጅ ስራ እየሰራን ነው ለምትሉ የፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሙሉ። እንዴት ከርማችሁልኛል? እንደ አገር ልጅ ብናፍቃችሁም እንኳ የናንተ እንጀራና የኔ ኑሮ አልገጥም ብሎ ካጠገባችሁ ከራቅሁ አመታት አልፈዋል። ብዙ ሰዎች የሰው ልብ ያላችሁ፣ አዛኝ አንጀት ያላችሁ መሆናችሁን ይጠራጠሩ ይሆናል። እኔ ግን እንደሱ አላስብም ብዙዎቻችሁ ድህነት በግዱ ገፍትሮ እዚህ ውስጥ እንደ ጨመራችሁ አውቃለሁ። ምክንያቱም ብዙ ጓደኞቼ የሚላስ የሚቀመስ ሲያጡ፣ እንደኔ ለመሰደድ መድፈር ሲያቅታችውና ቢፈልጉም እንኳን ሱዳንና ኬንያ የምታደርስ ገንዘብ በማጣታቸው እንጀራ ብለው የገቡ ብዙ እንዳሉ አውቃለሁ። እነዚህ በሙሉ የድሀ ልጆች ቤት ተቀምጦ በረሀብ ከመሞት የምችለውን አድርጌ እኖራለሁ ብለው እንደሚኖሩ አውቃለሁና በተለይ እናንተ ከዚህ የመከራ ማጥ እንድትወጡልኝ አምላኬን መለመን አልተውኩም። ግምገማ ፈርታችሁ የራሳችሁን ወገን በዱላ መጨፍጨፍ እንዴት እንደሚሰማ አውቀዋለሁ። ባዶ እጁን ያለን ሰውማ በጥይት መግደል የባሰ ነው። በተለይ ያልበላን ሆድ ተርቦ የሚያውቅ ሆድ እንዲህ ያለውን ግፍ በደንብ ያውቃል። ዞሮ ዞር የሚመታውም ሆነ የሚገደለው የናንተ ዘመድ እንኳን ባይሆን አንዱ ቦታ ተመድቦ የሚሰራ የባልደረባችሁ ዘመድ መሆኑ መች ይቀራል።
ጫካ የነበራችሁና ለነፃነት ሲባል የተቀላቀላችሁ ወገኖቼም ብትሆኑ ብዙዎቻችሁ የድሀ ገበሬ ልጆች ናችሁ ወይም ነበራችሁ። ድህነት ጣዕሟን ታውቃላችሁ። ወገናችሁ በሰው አገር እንደ ውሻ ሲቀጠቀጥ ወንጀለኛ ነው ወይም ሕገ ወጦች ናቸው ተብሎ ይበሏቸው የሚል አንጀት ይኖራችሃል ብዬ አላስብም። ከተወለደበት ቀዬ ወደማያውቀው አገር ብን ብሎ የሚሄደው የቸገረው ብቻ ነው። እጅና እግር እያለኝ እናትና አባቴ በረሀብ አይሞቱም ያለ ብቻ ነው። የምታጠባው ጡት ደርቆባት ልጆቿን የምታቀምሰው አጥታ ባሏ እጅና እግር እያለው ስራ አጥቶ ሲንከራተት ያየች ነች ጉዱን እያወቀች አረብ አገር የምትሄደው። አንዳንዶቻችሁ ሲከፋችሁ ምናባቱ ብላችሁ ጫካ እንደገባችሁት ባወጣ ያውጣው ብለው ያሉት የተሰደዱት የናንተው ቢጤ ምስኪኖች፣ ሀገራቸውንና ወገናቸውን የሚወዱ ድሆቹ ናቸው። ለነዚህ መከረኞች አለሁ ማለት ካቃታችሁ የትኛውን አገር ነው የምትጠብቁት? የትኛውን ነፃነት ለማምጣት ነው ጫካስ የገባችሁት? ምነው ታውቁት የለም የሱማሌ ስደተኞችን ተቀብለን አላኖርንም? ከ ኤርትራ የመጡ ስደተኞች ኢትዮጵያ ይኖሩ የለም? አረ ምን ስደተኞች ባለስልጣኖቹስ ቢሆኑ እነማን ሆነው ነው? ደግሞስ ከሀገራችን ይውጡ ካሉ አሳፍሮ መላክ ነው እንጂ እንደ አይጥ መንጋ መጨፍጨፉንስ ምን አመጣው? ምናልባት ጥፋት ስለሰሩ ነው ብለው ነግረዋችሁ ከሆነ ውሸት ነው። ሲብስባቸው የሚደርስላቸው ሲያጡ ባንዲራ ለብሶ መታረድ ቢሰለቻቸው ነው መቆጣት የጀመሩት። እውነት ቢኖራቸው ኖሮ መረጃውን ሁሉ አይከለክሏችሁም ነበር። አይናችሁን ሸፍነው ጆሮአችሁን ደፍነው ከሰውነት ወደ አውሬነት ለመቀየር ስለሚፈልጉ ነው። አረቦቹ ኢትዮጵያውያኑን በስፋት መግደል የጀመሩት የሀገራችሁ መንግስት ውሰዱልን ብንል እምቢ ስላሉ ነው እያሉ ነው።
ወገኖቼ ያለባችሁን ችግር አውቃለሁ ብዙ ብጽፍ ለማንበብም እድል አታገኙ ይሆናል። ግን ትንሽም ቢሆን የተሰማኝን ስሜት ላካፍላችሁ ብዬ ነው። አይምሰላችሁ የናንተን ችግር ሕዝቡም ያውቀዋል። እናንተ የእንጀራ ጉዳይ ሆኖባችሁ እንጂ አንጀታችሁ እርር እንደሚል አውቃለሁ። ከዚያም በላይ ደግሞ ብዙዎቻችሁ እህቶቻችሁ የወንድም የእህቶቻችሁ ልጆች ሁሉ አረብ አገር እንዳሉ አውቃለሁ። አንዳንዶቻችሁ እጮዎቻችሁ ጭምር ትንሽ ገንዘብ ሰርተው ኑሮ ለማሳመር ሲሉ አረብ አገር እንደሄዱባችሁ ሁሉ አውቃለሁ። ያው ነና የኔም ዘመዶች እኔኑ እያስቸገሩ እዚህ ተቀምጠን የማይሆን ነገር ውስጥ ከመግባት ሲሉ ስቅቅ እያልኩ ገንዘብ እልክላቸው ነበር። ካልሆነልን በዝሙት መተዳደር ነው እድላችን ያሉኝም አሉ። እቤት ተቀምጨ ረሀብ በሶስት ቀን ከሚገድለኝ ትንሽ ፋታ የሚሰጠው ኤድስ ይሻላል የሚሉ ሁሉ እንዳሉ አውቃለሁ፣ እናንተም ይህን በደንብ ታውቃላችሁ። ይህን እየሰማ አልጨክን የሚል ሆድ ያለው ግማሹ ገንዘቡን ልኮ ሌላውም ጥሪቱን ሽጦ ወይም ተበድሮ ነወ የላከው። ይህ ወገኑን የአረብ መጫወቻ ሲሆን እንባ አይደለም ለምን ደም አያስለቅስም። እናንተ ከዚህ የባሰ ሀዘን ውስጥ እንደምትሆኑ አውቃለሁ። ለመነጋገር ቀርቶ ለማሰብም እንደምትፈሩ ይገባኛል። ጥርነፋው የሚያወላዳ አይደለም። ግን ከእሳት የሚያወጣ ሀይል ያለው አምላክ አለላችሁ። የወገን ግፍ በቃ በሉ። ስለወገናችሁ መዋረድ ተቆርቆሩ። ይህን ሰርቶ እንጀራ ከመብላት ታግሎ መውደቅ ይመረጣል በእውነት ክፉ እንዲነካችሁ አልፈልግም ነገር ግን በዚህ ከቀጠልን ለናንተም እየፈራሁ ነው።
እናንተ እኮ የሀገር መከላከያ እንጂ የባለስልጣን ዘበኛ አይደላችሁም። ሀገር ስትዋረድ የአስራ አምስትና አስራ ስድስት አመት ልጆች በስድስትና ሰባት ወንድ እየተደፈሩ ደም በደም ሆነው በየሜዳው ሲጣሉ ምን አንጀት ያስጨክናችሁ ይሆን? ወገኖቼ አገራችን ብዙ አምባገነን መንግስታትን አስተናግዳለች። ሰራዊቱና ፖሊስም ለዚህ መሳርያ ሆኖ ያገለገለበት ወቅት ነበር። ነገር ግን የሀገር መከላከያ ሙሉ በሙሉ በጠላት እጅ ወድቆ ለጠላት አድሮ ኢትዮጵያን በዚህ ደረጃ ያዋረደበት ጊዜ ኖሮ አያውቅም። የዚህ የጠላት ጦር አጋር መሆን ወንጀል ነው። ልጆቻችንን አትንኩብን ወንድም እህቶቻችንን አትግደሉብን ብለው ሰልፍ የወጡ ሰዎችን አረቦች ፊት፣ ኤምባሲያቸው ፊት ለፊት በናንተ ዱላ መጨፍጨፍ ወንጀል ነው። ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረች ጊዜ ከጣልያን ጎን በመሰለፍ የሀገራቸውን ሕዝብ ያስጨፈጨፉ ጥቂት ባንዳዎች ነበሩ። የአንድ ሀገር ጦር እንዳለ የባንዳ ሰራዊት ሲሆንና ለእለት እንጀራ ሲባል የዚህ ጦር አባል መሆን ጭካኔ ነው አውሬነትም ነው። አውሬም እንኳ የራሱን ዘር መልሶ አይበላም። ለመሆኑ እናንተ ከማን ተፈጠራችሁ?
ይህ ጭካኔያችሁን የተመለከተ ኢትዮጵያዊ የያዛችሁትን ቆመጥ ተቀብለው ሊያደርጓችሁ የሚችለውንስ ታውቁ ይሆን? ወገናችሁን በመጨፍጨፍስ የደም እንጀራ ስትበሉ እንቅልፍስ እንደምን ትተኛላችሁ? ድህነት ክፉ ነው ሆድ ብዙ ያደርጋል ግን አሁን በቃ ልትሉ ይገባል። ልታምጹ እምቢ ለትሉ ይገባል። ጥያቄው የስልጣን አይደለም፣ የሀይማኖት አይደለም፣ የዘር አይደለም የነጻነት ጥያቄ ነው! የክብር ጥያቄ ነው! የ ኢትዮጵያዊነት ጥያቄ ነው።
ከጠላቶቻችን ጋር ተባብራችሁ የሀገራችሁን ሕዝብ ለመጨፍጨፍ ቁርጠኛ ሆናችሁ ከቀጠላችሁ ይሄ ሕዝብ ሊያደርጋችሁ የሚችለውን አስባችሁ ይሆን? ወገኖቼ ይህ ቀን ሳይጨልም እምቢ በሉ። ዘረኞች፣ የአረብ አሽከር ሆነው ሀገራችሁን መሬታችሁን እየሸጡ፣ ሚስት ልጆቻችሁን ለግርድና እየላኩ ሀብት ሲያጠራቅሙ የነሱ ዘበኛ መሆንና የእንደዚህ አይነት ከሀዲዎች አጋር መሆን ጨካኝነት ብቻ ሳይሆን የሀገር ጠላትነት ነው። በታሪክ የሚያስጠይቅ በክህደትም የሚያስጠይቅ ነው። እምቢ የምትሉበት ጊዜ አሁን ነው። በየሜዳው ላይ እየተደፈሩና እየተገደሉ ያሉ ኢትጵያውያን ደም ይፋረዳችኋል። ይህ መረጃ ለሁሉም ሊደርስ የሚገባው ነው ላልሰማው አሰሙ። ይህ የፍረሀት አጥር ይፈርሳል ያኔ የታጠቃችሁት መሳርያ ዋጋም አይኖረውም። ብዙዎች ወገኖቻቸውን ለመቀላቀል መነሳሳትን አሳይተዋልና እናንተም ተነሱ፣ ቁጣችሁን አሳዩ ወገናዊነታችሁን አስመስክሩ! አገራችሁን ኢትዮጵያንና ሕዝባችሁን ታደጉ። የመገናኛ ብዙሃን በድምጽም ቢሆን መልዕክቴን ያደርሱላችሁ ይሆናል አመጽ በልብ ይጠነሰሳል ሁኔታ ሲፈቅድ ደግሞ ይፈነዳልና ልባችሁ ይሸፍት እምቢታችሁን መግለጫ መንገድ አስቡ። ኢትዮጵያ ከዚህ መዐት ተውጣለችና የመፍትሄው አካል ሁኑ። አምላካችሁ የእውነቱን መንገድ ያሳያችሁ።
ወንድማችሁ ዳኛቸው ቢያድግልኝ
biyadegelegne@hotmail.com

Friday, November 15, 2013

Arrests at anti-Saudi protest in Ethiopia


Police crackdown on demonstrations against targeted attacks on Ethiopian migrant workers in Saudi Arabia.
 The government said protesters did not have a permit to demonstrate and confirmed that arrests [AFP]Police in Ethiopia have arrested dozens of people outside the Saudi embassy in the capital Addis Ababa 
Screenshot_2013-11-15-14-50-54-1in a crackdown on demonstrators protesting against targeted attacks on Ethiopians in Saudi Arabia.Police units blocked roads on Friday to prevent the protest at the embassy from growing and forced some journalists to delete photos.”The police came and they beat us… and now more than 100 people are at the police station.Getaneh Balcha, Blue PartyOne protester, Asfaw Michael, who was beaten, said he did not understand why Ethiopia wanted to shield Saudi Arabia from the protest.According to the Ethiopian government, three Ethiopians were killed last week in Saudi Arabia in clashes with police. Saudi authorities are in the process of repatriating at least 23,000 illegal immigrants fromEthiopia.”The police came and they beat us…and now more than 100 people are at the police station,” said Getaneh Balcha, a senior member of the opposition Blue Party movement, adding the party chairman and vice chairman were among those held.The government said protesters did not have a permit to demonstrate and confirmed that arrests had been made, but did not say how many.”It was an illegal demonstration, they had not got a permit from the appropriate office,” Shimeles Kemal, a government spokesman, told the AFP news agency, adding charges could be brought against the organisers.”They were fomenting anti-Arab sentiments here amongEthiopians … the demonstration itself was illicit, so the police took measures and apprehended some,” he said.Many foreign workers in Saudi Arabia are fleeing or are under arrest amid a crackdown on the kingdom’s nine million migrant labourers. Close to 500 Ethiopians have been repatriated.Last weekend, Saudi residents fought with Ethiopians and a video emerged of a crowd dragging an Ethiopian from his house and beating him.The security sweep in Saudi Arabia comes after seven months of warnings by the government, which has created a task force of 1,200 Labour Ministry officials who are combing shops, construction sites, restaurants and businesses in search of foreign workers employed without proper permits.More than 16,000 people have already been rounded up, according to authorities.

Wednesday, November 13, 2013

የኢትዮጵያ መንግስት በሳዑዲ አረቢያ እየተፈጸመ ያለውን ግድያን አስመልክቶ በአ.አ ሰልፍ መውጣትን አልደግፍም አለ


“በዜጎቻችን ጉዳይ ከማንም ጋር አንደራደርም” – ሰማያዊ ፓርቲም

‹ከእናንተ በፊትም ሌሎች ዜጎች ደብዳቤ ይዘው መጥተው ተከልክለዋል ስለዚህ ለእናንተም አይቻልም›አቶ ማርቆስ ብዙነህየሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ደብዳቤውን አቶ ማርቆስ ቢሮ አስቀምጠው ወጥተዋል፡፡


ሰማያዊ ፓርቲ አርብ ከ5.30 ጀምሮ በሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ በር ላይ የሚደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ ለሚመለከተው አካል ለማሳወቅ ዛሬ ጠዋት 4 የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ወደ አዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ደብዳቤ ለማስገባት የሄዱ ቢሆንም ደብዳቤውን የተቀበሏቸው የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ኦፊሰር አቶ ማርቆስ ብዙነህ ‹ከእናንተ በፊትም ሌሎች ዜጎች ደብዳቤ ይዘው መጥተው ተከልክለዋል ስለዚህ ለእናንተም አይቻልም›በማለት ላለመቀበል ቢያንገራገሩም አመራሮቹ በቁርጠኝነት ደብዳቤውን አቶ ማርቆስ ቢሮ አስቀምጠው ወጥተዋል፡፡ አቶ ማርቆስ ብዙነህም ከንቲባው ከሰአት ስለሚገቡ እሳቸው ካልፈቀዱ ቀሪ ደብዳቤ ላይ አልፈርምም ቢሉም ሰማያዊ ፓርቲ አዋጁ በሚያዘው መሰረት ከ48 ሰአት በፊት የማሳወቅ ስራውን ጨርሶ በፅ/ቤቱ ለተቃውሞ እንቅስቃሴው ዝግጅቶችን እያደረገ ይገኛል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ)በሳውዲ አረቢያ በዜጎች ላይየሚፈጸመው ኢሰብአዊ ድርጊት አውግዞ በቅርቡ በሚጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ሕዝቡ በነቂስ በመውጣት በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና በደል በመቃወም ድምፁን እንደዲያሰማና ወገናዊ አጋርነቱን እንዲያሳይ መድረክ ጥሪ አቀረበ።
source . zehabesha

Tuesday, November 12, 2013

ትግሉ መሯል፤ እኛም ዝግጁዎች ነን


በንቅናቄዓችን ፀሐፊ እና በግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አመራር አባላት ላይ የተቃጣው ረዥም ጊዜ የወሰደ የግድያ ሴራ መክሸፉ አስደስቶናል። ይህ ሴራ የወያኔ የስለላና የግድያ ኃላፊዎች በሆኑት ጌታቸው አሰፋ እና ጸጋየ በርሄ የቅርብ ክትትል የተመራ፤ የአሻንጉሊቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እውቅናና ይሁንታ የተሰጠው፤ ወያኔ ከፍ ያለ ተስፋ የጣለበት ሴራ ነበር።

“ወያኔ-ኦ-ሚሊኒየም” የተሰኘው ይህ በወያኔ የመጨረሻ ከፍተኛው አመራር የተመራው ሴራ ስለወያኔ ውስጣዊ አደረጃጀት ጠቃሚ መረጃዎችን ሰጥቶናል። ከዚህም በተጨማሪ የወያኔ ሹማምንት ስለ ኢትዮጵያ ሕዝብ ያላቸውን ንቀት፤ ከአመት በኋላ ስለሚደረገው ምርጫ ውጤት፤ ለሰላዮቻቸው ስለሚሰጡት ጉርሻ መጠን፤ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ተስፋ ከጣሉበት ቅጥረኛ ነብሰ ገዳያቸው ጋር ካደረጉት የስልክ ንግግሮች ማድመጥ ይቻላል። ይህ ለበርካታ ጥናቶች በግብዓትነት ሊውል የሚችለውን በድምሩ ከስምንት ሰዓታት በላይ የሚፈጀው የስልክ ንግግር ቅጂ በሕዝባዊ ኃይሉ የመረጃ ክፍል አማካይነት ለሕዝብ በኢንተርኔት በነፃ ተለቋል። በአጋጣሚውም የወያኔ ገበና ተጋልጧል።

በአንፃሩ ደግሞ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የተደራጀው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቢሆንም ምን ያህል ወያኔን እንቅልፍ እንደነሳ ተጨባጭ ማስረጃ ሆኗል። ይህ ለነፃነት ታጋዮች ከፍተኛ የስነልቦና ብርታት የሚሰጥ ነገር ሆኖ ተገኝቷል።
በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የተቃጣበትን ጥቃት ከማክሸፍ በተጨማሪ የወያኔን ገበና ማጋለጥ በመቻሉ የመጀመሪያው ሁነኛ ድል ተቀዳጅቷል።

ግንቦት 7 : የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ “ወያኔ ኦ ሚሊኒየም” አፕሬሽንን ላከሸፉ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አመራርና አባላት ያለውን አድናቆት ይገልፃል። ለወደፊቱም ተመሳሳይ ጥቃቶች ሊደርሱ የሚችሉ መሆኑን በመገንዘብ የመከላከል ብሎም የማጥቃት ኃይሉን እንዲያጠናክር ይመክራል።

የንቅናቀዓችን እና የሕዝባዊ ኃይሉ አመራርና አባላት ለመስዋዕትነት የተዘጋጁ ናቸው። “ወያኔ ኦ ሚሊኒየም” ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ትግላችን ይገታ ነበር ማለት አይደለም። ትግላችን መስዋዕትነትን የሚጠይቅ መሆኑን እናውቃለን። ጓዶች ሲወድቁ ሌሎች ሺዎች አርማቸውን አንስተው ትግሉን ይቀጥላሉ።

ትግሉ የሚጠይቀንን መስዋትነት ከፍለን ወያኔን ከሥልጣን አስወግደን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት የሆነባት ኢትዮጵያ እንደምትኖረን እርግጠኞች ነኝ።

ትግሉ መሯል፤ እኛም ዝግጁዎች ነን።
ድል ለግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!