Friday, May 2, 2014

ሰበር ዜና- የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ፕሬዝደንት ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ተሰደደ


Journalist Betre Yakob
ከሳምንት በፊት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት በአፍሪካ ህብረት ጋባዥነት የኢትዮጵያን ችግርና አፈና በተለይ በሚዲያው ላይ ያለውን ጫና እና ጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰውን አፈና ለመግለጽ ወደ አንጎላ አቅንተው ነበር፡፡ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ለአፍካ ህብረትም የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረቡና ለሰብአዊ መብት ኮሚሽነሩም መልስ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ስብሰባው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ አገሩ ለመመለስ በሚዘጋጅበት ወቅት የዓለም አቀፍ የጋዜጠኛ ማህበራትን ጨምሮ ሌሎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ እሱን ለማሰር የተደረገው ዝግጅት በተጨባጭ ማስረጃ ስላቀረቡለት መሰደዱን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች በታሰሩበት ወቅት ፖሊስ የበትረ ያቆብን ቤት በመፈተሸ ያገኘውን ወረቀት ሁሉ እንደወሰደም ምንጮቻችን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አንጎላ በተደረገው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ኮሚሽነሩን በግል እንዳገኛቸውና ኮሚሽነሩም በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ በመግለጽ እንዲሚያገኙት ቃል ገብተውለት እንደነበር ተገልጿል፡፡ በተጨማም ከበርካታ የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና በሚዲያው ላይ ስለሚደረገው ጫና የተወያዩ ሲሆን አብዛኛዎቹ በተለያዩ መንገዶች እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተውለት እንደነበር ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በስብሰባው ወቅት ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጹ ጽሁፎች ለተሰብሰብሳቢዎቹ ተበትነዋል፡፡
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ መቋቋም ያስፈራቸው ሌሎች የጋዜጠኞች ማህበራት በትረ ያቆብን ለሂውማን ራይትስ ዎች፣ ለሲፒጄ፣ ለአርቲክል 19ና ሌሎች የጋዜጠኞች ማህበራት ይሰራል፣ ይሰልላል፣ የእነዚህ ድርጅቶች ተላላኪ ነው፣ ሪፖርት ይጽፋል በሚል በመግለጫቸውና ‹‹የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ›› በተባለው ፕሮግራም ይከሱት እንደነበር ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አገር ውስጥ በነበረበት ወቅት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻል፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

Thursday, May 1, 2014

ሰበር ዜና፣ በጎንደር ተኩሱ ቀጥሏል፣ በግጭቱ 6 ሰው ሞቷል

May 1, 2014

Update:

ፖሊስ በነዋሪዎቹ ላይ የወሰደው እርምጃ ያስቆጣው የጎንደር ህዝብ በቁጣ የአጸፋ እርምጃ እየወሰደ እንደሆነ ከጎንደር የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በፖሊስ እርምጃ የተቆጡ ወጣቶች የፖሊስ መኪና በመሰባበር ላይ ናቸው ተብሏል፡፡ ህዝቡ በነቂስ እየወጣ ግጭቱ እየተባባሰ መሆኑንም ምንጫችን ጠቅሷል (ነገር-ኢትዮጵያ)
——————————
ነገረ-ኢትዮጵያ – ጎንደር ከተማ ውስጥ ቀበሌ 18 ልዩ ቦታ አርምጭሆ ሰፈር፣ ገንፎ ቁጭና ህዳሴ የተባሉ ሰፈሮች የከተማው አስተዳደር ‹‹ህገ ወጥ ሰፈራ ነው፡፡›› በሚል ቤቶችን ለማፍረስ መዘጋጀቱን ተከትሎ አፍራሾቹ ከህዝብ ጋር በፈጠሩት ግጭት ከ6 በላይ ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸውንና መታሰራቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ግጭቱ ከሶስት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት ተኩል ድረስ ቀጥሎ የነበር ሲሆን ምንጫችን ደውሎ በሚነግረን ወቅት (ከቀኑ 6፡ 43) ተኩስ እንደነበር ለመረዳት ችለናል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎቹ ሚያዝያ 7/2006 ዓ.ም ቤታቸውን እንዲያፈርሱ ትዕዛዝ በተላለፈበት ወቅት ህገ ወጥ አለመሆናቸውን፣ ካልሆነም መንግስት ቅያሬ ቦታና ጊዜ መስጠት እንዳለበት በመግለጽ አንለቅም ብለው እንደነበር ይታወቃል፡፡ በዛሬው ቀን ግጭቱ የተነሳውም አፍራሾቹ እንዲፈርሱ የተወሰነባቸውን ቤቶች ቀለም በመቀባታቸውና ህዝቡም እንዳይቀቡ በመከልከሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
በግጭቱ ፖሊስ፣ ፌደራልና ልዩ ኃይል የተሳተፈበት ሲሆን ከተገደሉትና ከቆሰሉት በተጨማሪ የአካባቢው ወጣቶች ላይ ድብደባና እስራት እየፈጸሙባቸው እንደሆነ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ‹‹ወጣቶችን እንደ እንሰሳ በአንድ ገመድ አስረው እየደበደቧቸው ነው፡፡ ህዝብ በጅምላ እየታሰረ ይገኛል፡፡ ግጭቱ ቢያቆምም በአሁኑ ወቅት በሶስቱም ሰፈሮች ጥይት እየተተኮሰ ነው›› ያሉት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች የተወሰደው እርምጃ የጎንደርን ህዝብ በማስቆጣቱ ከዚህ የባሰ ግጭት እንዳይፈጠር ያሰጋል ሲሉም ገልጸውልናል፡፡ በግጭቱ ወቅት የመጀመሪያዋ የሞት ሰለባ የሆነችው ልዩ ኃይል ቤቷ እንዲፈርስ ቀለም ሲቀባ የተቃወመች የልጆች እናት እንደሆነችም ታውቋ፡፡

Wednesday, April 30, 2014

ሴቶችን አብዝቶ የሚፈራው መንግሥት

April 29, 2014

ቹቸቤ
Jailed Ethiopian female bloggers, activists and journalists
መነሻቸው ግልብ ጎጠኛነት መድረሻቸው መንደረተኛነት በመሆኑ በዘረፋ እየከበሩ በመለስ ራዕይ እያጨናበሩ ከመኖር ያለፈ ከእውነት ጋር ፊት ለፊት ተያይተው መኖር ያልቻሉት የትግራይ ጉጅሌዎች በወጣቶች ላይ የሚፈጽሙት ሰቆቃ አሳፋሪ ነው። በህጻናትና በሴቶች ላይ የሚበረቱ የማስተዋል ድርቅ የመታቸው፣ የእውቀት ረሀብ ያደነዛቸው ፍርሃት እንቅልፍ የነሳቸው ናቸውና ድፍረት ያላቸው ህጻናት ያስፈሯቸዋል እውነት የያዙ ሴቶች ያስደነግጧቸዋል። ለዚህ ነው የወጣቶችን ግንባር በምንደኛ ጦር ሲነድሉ ወጣት ሴቶችን ሲደፍሩ ሲያስደፍሩና ሲያዋርዱ ደስታን የሚያገኙት።


አብዛኞቹ በዚህ ጎጠኛ ቡድን የሚንገላቱት ወጣቶች ወያኔ በገባበት ዘመን የተወለዱ ወይም ገና ድክድክ የሚሉ ህጻናት ነበሩ። ሲነገራቸው የኖረውና ህይወታቸውን ሙሉ የተመለከቱት ኢትዮጵያ ስትዋረድ የሀገሪቱ ጀግኖች ሲሰደቡና ዘር በዘር ላይ ሀይማኖት በሀይማኖት ላይ የሚያነሳሳ ታሪክ ሲማሩ ነበር ያደጉት። ሬድዮ፣ ቴሌቭዥን ጋዜጣና መጽሄቱ ሁሉ የሰሩት የወያኔን ፕሮፓጋንዳ ነበር። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያዊነት ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ እየገነነ፣ ለነፃነት የሚደረገው ትግል እየጠነከረ መምጣቱ ይልቁንም አፍራሹ ፕሮፓጋንዳና ድርጊት ጠንካራ ወጣት ወንዶችና ወይዛዝርቶችን ቁርጠኛ ታጋይ እንዲሆኑ አደረገ እንጂ ኢትዮጵያዊነት ሲሞት አላየንም።
ከዚህ መማርና መለወጥ የሚቻል ቢሆንም ኢትዮጵያዊነትን ያሟጠጠ አእምሮው በጥላቻ የሰከረን መመለስ እንደማይቻል መመልከት አሳዛኝ ነው። “የሚያድግ ልጅ አይጥላህ” የሚባለው ተረት የሚያስተምር ቢሆን በወጣቶች ላይ የሚሰራውን ግፍ ቀነስ ማድረግ በተቻለ ነበር። እኒህ ወጣቶች ይቅር ባይ እንጂ ቂመኛ እንዳይሆኑ ግን ምኞቴ ነው።
እነዚህ ክፉዎች በየቀኑ የሚተክሉት የጥላቻ ችግኝና የእልቂት ድግስ የመቶ አመቱን በደል አስታውሶ ከሚያጫርሰው በላይ ዛሬ የሚደርሰውን ግፍና በደል አጉልቶ የሚያሳይ በመሆኑ የታች አምናውን ሳይሆን የትናንቱን የወያኔን ሕዝብ ከመኖርያ ማፈናቀል፣ ገበሬዎችን መበተን፣ የሀገር ድንበር መቁረስን፣ በአማራና ኦሮሞ ላይ እየተኪያሄደ ያለውን የዘር ማጥፋት እያስታወሰ የሕዝብ ሃይል መልሶ ጠራርጎ እንደሚያጠፋቸው አለማወቅ የግብዝነትና የድንቁርና ምልክቱ ነው። በዘመነ ደርግና በንጉሳውያኑ ዘመን ከሆነው ሁሉ የበለጠ ግፍና በደል የተፈጸመው በነዚህ ጎጠኞችና የሀገር ጠላቶች እንደሆነ ለመናገር እዚያው ትግራይ ያለውን ተቃውሞ ምሳሌ ማድረግ ይበቃል። ጎጠኞቹ ልብ ያላሉት የታቀፉት የእባብ እንቁላል እነሱኑ ቀድሞ እንደሚነድፍ ነው። ይህ እንደሚሆን ለማወቅ በሀገሪቱ ከተበተኑት ሰላዮች መስማት የሚፈልጉትን ብቻ ሳይሆን እውነት እንዲናገሩ ብቻ ቢፈቅዱላቸው እንኳ ያንዣበባቸውን አደጋ ባወቁት ነበር።
ርዕዮት አለሙ ጽንፈኛና አሸባሪ ልትባል የምትችልበት ምንም መረጃ የለም። ወያኔዎችን ያስፈራው እውነትን መያዝዋና ድፈረቷ ብቻ ነው። ርዕዮትን ማሸማቀቅ ሌሎችን ለማስፈራራት የተወሰደ እርምጃ ነበር ግን ውጤቱ በተቃራኒው ሆነ። እናም አነሆ ወይዛዝርቶቹ ተነሱ! ስለወያኔ ክፋት ሳይሆን ስለሕዝባችን ብርታትና መነሳሳት የምናወጋውም በኩራት የሚሆነው ለዚህ ነው።
ሴቶች ትግሉን አልተቀላቀሉም፣ ብዙዎቹ ወደሁዋላ ይላሉ እንላለን ጥቂት ግን በጣም ጥቂቶቹ ደፍረው ሲወጡ ከጎናቸው ልንቆምና በየአቅጣጫው ልንታገልላቸው ይገባል። ርዕዮት እድሜዋ ገና ሰላሳዎቹ ውስጥ ያለች ወጣት ትዳር ያልመሰረተችና ልጅ የሌላት ብዕረኛ ናት። ትዳሩ ይቅር ልጅም አይኑራት ነገር ግን ለህይወትዋ አስጊ በሆነ የጤና ችግር ላይ መሆንዋ እየታወቀ ህክምና እንዳታገኝ ማድረጉ አሰቃይቶ የመግደል እኩሌታ ነው። ይህ የግፍ ጽዋ ሞልቷል። ወጣቱ ቆርጦ ተነስቷል።
ምስላቸው ከዚህ ጽሁፍ ጋር የሚታየው ወጣቶች የእስርቤት ሰለባ ይሆናሉ ብሎ ማሰብ በጣም ያሳዝናል። ይሁን እንጂ ሁላቸንንም የሚያበረታቱ የጣይቱ የዘር ግንድ የጀግኖች የዜግነት ውርስ በዚህ ትውልድ ደም ውስጥ መፍሰሱን ስለሚያመለክቱ ተስፋ ይሰጡናል ብርታትም ይሆኑናል። እኒህ ወጣቶች ከታሰረው ከሰፊው ሕዝብ ጋር ተቀላቅለው ለነጻነት ለሚደረገው ትግል አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ተባብረን እንነሳ! ከትንሹ እስር ቤት ወደ ትልቁ ይመጡ ዘንድ ድምጻችንን እናሰማ። አብረንም ሆነን የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልስ። ኢትዮጵያችንንም ነፃ እናውጣ!
ኦህ ኢትዮጵያ ባንቺ ተሰፋ አይቆረጥም… ልጆችሽ የነጻነት ዐየርን ይተነፍሱ ዘንድ በጀግንነት እንታገላለን… ሁሌም የመከራ ገፈት የሚቀምሱትና የበደል ጫና አንገት ያስደፋቸው የሀገራችን ሴቶች በሀገራቸው ኮርተው አንገታቸውን ቀና አድርገው እንዲሄዱ የድርሻችንን ሁሉ እናበርክታለን።
ምንጭ፦ ኢካዲፍ

Tuesday, April 29, 2014

በዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና በጋዜጠኞች ላይ የተወሰደው የእስር እርምጃ እንዳሣሰበው ሲ.ፒ.ጄ ገለጸ።

ዓለማቀፉ የጋሴጠኞች ተንከባካቢ ድርጅት(ሲፒጄ)  ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ሰሞኑን በ9 ጸሀፍያን ላይ የወሰደው የእስር እርምጃ፤ ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ላይ ከተቃጡ የከፉ እርምጃዎች አንዱ ነው ብሏል።
“የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በሰላማዊ መንገድ ሀሳብን መግለጽን እንደወንጀል እየቆጠሩት ነው” በማለት ነው -የሲፒጄ የምስራቅ አፍሪቃ ወኪል-ቶም ሩድስ-እርምጃውን የኮነኑት።
እሁድ ዕለት የመንግስት አቃቤ ህግ በ አዲስ ጉዳይ ዋና አዘጋጅ በ አስማማው ሀይለጊዮርጊስ፣ በፍሪላንስ ጋዜጠኞቹ በተስፋለም ወልደየስ እና በ ኤዶም ካሣዬ፣ እንዲሁም በጦማርያኑ በ አቤል ዋቤላ፣በ አጥናፍ ብርሀኔ፣በማህሌት ፋንታሁን፣ በዘላለም ክብረት እና በበፈቃዱ ሀይሉ ላይ  ከውጪ ድርጅቶች ጋር ይሠራሉ፣ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀምም በሀገሪቱ አለመረጋጋት እንዲፈጠር ይንቀሳቀሳሉ.. የሚል ክስ እንደመሰረተባቸው ሲፒጄ አውስቷል።
ተስፋለም፣አስማማውና ዘላለም ለፊታችን ሚያዚያ 28 ቀሪዎቹ ደግሞ ለሚያዚያ 29 እንደተቀጠሩ ከሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች የደረሰውን መረጃ ዋቢ አድርጎ የጠቀሰው ሲፒጄ፤ በታሳሪዎቹ ላይ እስካሁን መደበኛ ክስ እንዳልተመሰረተ ጠቁሟል።
ሲፒጄ በመግለጫው-ፀሀፊዎቹ ዞን ዘጠኝ ተብሎ የሚጠራ የገለልተኛ አክቲቪስቶች ስብስብ አባል ሆነው የተለያዩ ዜናዎችንና ጽሑፎችን ይጽፉ እንደነበር  አመልክቷል።
“ዞን ሰጠኝ የተሰኘው ስያሜ ከቃሊቲ የተገኘ  መሆኑና  የጸሐፊዎቹ  መሪ ቃል፦”ስለሚያገባን እንጦምራለን” የሚል  መሆኑ በሲፒጄ መግለጫ ተመልክቷል።
ጦማርያኑና ጋዜጠኞቹ የታሰሩት ከደህንነቶች በሚደርስባቸው ወከባ ምክንያት ላለፉት ሰባት ወራት ዘግተውት የቆዩትን የፌስቡክ ገፃቸውን ዳግም በከፈቱ ማግስት መሆኑን እንደተረዳም የጋዜጠኞች መብት ተንከባካቢ ተቋሙ ገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ አማካሪ የሆኑት ጌታቸው ረዳ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ፦”የታሰሩት ጋዜጠኞች አይደሉም፤ እስሩ ከጋዜጠኝነት ሥራቸው ጋር የተገናኘ አይደለም። ከከባድ ወንጀል ጋር የተገናኘ ነው” ማለታቸውን ሲ.ፒ.ጄ ጠቁሟል።
“በጋዜጠኝነት ወይም ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ላይ የቃጣነው በትር የለም። ሆኖም ማንም ቢሆን ሙያውን ሽፋን በማድረግ ወንጀል ለመፈፀም ሲሞክር በህግ ይጠየቃል” ሲሉም አክለዋል-አቶ ጌታቸው ረዳ።
“የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ወደለየለት ፈላጪ ቆራጭ አገዛዝ  ማዘንበላቸውን እንዲገቱና በሀገሪቱ  ነፃ ሀሳቦች ይንሸራሸሩ ዘንድ እንዲፈቅዱ ጥሪ እናቀርባለን” ብለዋል-ሚስተር ቶም ሩድስ።
የታሰሩት 9ኙም ጸሀፊዎች በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል ሲሉም ጠይቀዋል። ዓለማቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቋም ሂውማን ራይትስ ዎችና ሌሎች ድርጅቶችም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በጦማርያኑ እና በጋዜጠኞቹ ላይ የወሰዱትን እርምጃ በማውገዝ ፤ ኢትዮጵያን ለመጎብኘት ዛሬ አዲስ አበባ የሚገቡት የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ  እስረኞቹን እንዲፈታ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል።
የተለያዩ ዓለማቀፍ የሚዲያ ተቋማትም ሰሞኑን የኢትዮጵያ መንግስት በ9ኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ የወሰደውን የማሰር እርምጃ ሽፋን ሰጥተውታል።
ከሚዲያ ተቋማቱ መካከል ኤ.ቢ.ሲ ኒውስ፣ ሲ ኤን.ኤን፣ ዋሽንግተን ፖስት፣ ሬውተርስ፣ እና አልጀዚራ ይገኙበታል።
እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ በጉብኝታቸው ስለታሰሩት ጦማርያን እና ጋዜጠኞች አጠንክረው እንደተናገሩ  የኒውዮርክ ታይምሱ ታዋቂ አምደኛ  ኒኮላስ ክሪስቶች ለሰጣቸው አስተያዬት፤ “ በጣም  ጠቃሚ ጉዳይ ነው። ዩናይትድስቴትስ  በመላው ዓለም ላይ የፕሬስ ነፃነትን በመደገፍና ከጥቃት በመከላከል ባላት ጠንካራ አቋም ትቆያለች” በማለት ምላሽ ሰጥተውታል።
ምንጭ፦ ኢሳት

Saturday, April 26, 2014

Nine Bloggers and journalist Tesfalem Woldey arrested in Addis Ababa /Meakelawi/


Zone9 has confirmed that Six Zone9 bloggers and journalist Tesfalem Woldeyes are in Addis Ababa central investigation center (meakelawi) since their arrest last night. during the arrest their house was searched and police took laptops, Newspapers and books from their home. Families were not allowed to meet them.We believe members and friends of Zone Nine have nothing to do with any illegal activities and we again request the government to release them immediately.

#FreeZone9bloggers #FreeTesfalem #Ethiopia

1. TESFALEM WELDEYES @tesfalemw.
Journalist, Former addis neger ,
Founder of Habeshawi Kana.Worked @ A.Standard & A Fortune.
Arrested Apr25
2. BEFEKADUHAILU @befeqe
was a MIS Expert at St. Mary's U/College.
Blogger & Activist @ #Zone9.
Arrested Apr25. 3
3. . NATNAIL FELEKE @EthioLiberty
HR Mgmt Officer at C and B Bank S.C.
Blogger & Activist @ #Zone9.
Arrested Apr25.
4. . MAHLET FANTAHUN @faantish a Data Officer at PMU.
Blogger & Activist @ #Zone9.
Arrested Apr25
5. . ATNAF BERHANE @Atnaf1
an IT and Services professional.
Blogger & Activist @ #Zone9.
Arrested Apr25.
6. . ZELALEM KIBRET, @zelalemkibret
Studied Law.
Lecturer at Ambo Unv..
Blogger & Activist @ #Zone9. Arrested on Apr25.
7. . ABEL WABELLA @abelpoly,
a Tooling Engineer at Ethiopian Airlines.
Blogger & Activist @ #Zone9
Arrested Apr25


Friday, April 25, 2014

የሚታደስ ቃል ኪዳን


አጼ ዮሃንስ (1837-1889)
(ጸጋዬ ገብረ መድኅን አርአያ)
“መኳንንቶቼ፣ ልጆቼና ሕዝቦቼ ሆይ! እኔ ስለ እናቴ ኢትዮጵያ ሕይወቴን ልሰዋላት ሙሉ ፈቃድ አለኝ። በእኔ ልብ ያለው አሳብ በትክክል በእናንተም ልብ በመታሰቡ በጣም ደስ ብሎኛል። እንግዲህ አሳባችን አንድ ከሆነ ጠንክሩ እንጂ አትፍሩ። ለዘመቻውም አዋጅ አናግራለሁና አይዞአችሁ አትፍሩ! አገሬ ሆይ ስሚ! መኳንንቶቼ፣ ወታደሮቼ፣ ሕዝቦቼ ስሙ…..ወደፊት ገስግሱ እንጂ ወደኋላ አትቅሩ! የኢትዮጵያ ልጅ ሆይ! ልብ አድርገህ ተመልከት ኢትዮጵያ የተባለችው አንደኛ እናትህ ናት! ሁለተኛ ዘውድህ ናት! ሦስተኛ ሚስትህ ናት! አራተኛ ልጅህ ናት! አምስተኛ መቃብርህ ናት! እንግዲህ የእናት ፍቅር፣ የዘውድ ክብር፣ የሚስት ደግነት፣ የልጅ ደስታ፣
የመቃብር ከባቲነት እንደዚህ መሆኑን አውቀኸው ተነሳ!”



- አንበሳው አጼ ዮሐንስ- ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ

ለእናታቸው፣ ለሚስታቸው፣ ለልጃቸው፣ ለዘውዳቸውና ለመቃብራቸው የተሰውትና በሕይወት ዘመናቸው “አንበሳው አጤ ዮሐንስ” እየተባሉ ይጠሩ የነበሩት ሰማዕት ከሞቱ 125 ዓመት ሆናቸው። አንድ አሜሪካዊ ታጋይ በ1775 በአንድ የፊላደልፊያ ፍርድ ቤት ቀርቦ የታላቁን የእንግሊዝ መንግሥት አመራር በመቃወም በፈፀመው ወንጀል እንዲሰቀል ሲፈረድበት የተናገረው ተጠቃሽ ቃል ነበር። “አዝናለሁ እግዚአብሔር አንድ ነፍስ ብቻ ስለሰጠኝ” ነበር ያለው። አጤ ዮሐንስን በዚያ ታሪካዊ ብጽአት የምለካቸው፣ በዚያው ራሳቸው በመደቡት የወርቅ ሚዛን የምመዝናቸውና ለኢትዮጵያ ተከታታይ ትውልዶች ሁሉ ዘላለማዊ ብሔራዊ ቃል ኪዳን ቀርጸው ያለፉ ታላቅ መሪ ስለሆኑ ነው። በዚህ መስፈርት የኖሩም ናቸው። ደርቡሽ ጀግናውን መሪ ገድያለሁ፣ አንገቱንም ቆርጨ ወስጄ ተጫውቸበታለሁ ሊል ይችላል። ዮሐንስ ተገድሎ የኢትዮጵያ መሬት በደርቡሽ ተወስዶ ቢሆን ቁጭቱ ባነደደን ነበር። እስከማዕዜኑ። ቢያንስ 125 ዓመት የዚያ አካባቢ ኢትዮጵያዊ መሬትነት ተጠብቆ ቆይቶአል። ደርቡሽ የደፈረንስ አሁን ነው። አገር ሲያረጅ እሾህና አሜከላ ያበቅላልና! አጤ ዮሐንስ - ራሳቸው ባሰፈሩት መዳልው መሠረት ለእናታቸው፣ ለሚስታቸው፣ ለልጃቸው፣ ለዘውዳቸውና ለመቃብራቸው ሕይወታቸውን “ለመሰዋት ሙሉ ፈቃድ አለኝ” እንዳሉት ጽዋውን ተጐንጭተው አለፉ። ልቅሶ መቀመጥ የሚገባቸው “እናታቸው፣ ልጃቸው፣ ሚስታቸው፣ ዘውዳቸውና መቃብራቸው” ደግሞ እንደ ዘመኑ ባህል ቅቤ መቀባት የነበረባቸው ይመስለኛል። በደስታ የሚሞትላቸው መሪ መታደል እንደ ቀላል ነገር የሚታይ አይደለማ። እኔስ በእኔው ደረጃና አጋጣሚውን አውቀዋለሁ። ከጉራና ከአጉል መንጠራራት ጋር ካላያችሁብኝ።

አንድ ጊዜ በጦቢያ ላይ በወጣ ጽሑፍ ምክንያት ከከፍተኛው ፍርድ ቤት እመላለስ ነበር። እንዳጋጣሚ ታላቅ እህቴ ማን እንደነገራት ሳላውቅ በመጨረሻው የፍርድ ዕለት ችሎቱ ሲከፈት ከሕዝቡ መሐል ጉብ ብላለች። እህቴን ሳያት “አርፈህ ብትቀመጥስ? አንተ ታማሚ ነህና ሁሉንም ነገር እርግፍ አድርገህ ተቀመጥ- እኛንም በስጋት ጨረስኸን” ብላ ትጨቀጭቀኛለች ብዬ ጥርሶቼን ሳፉዋጭ ቆየሁ። ወዲያው ተጠራሁና ፍርደ ገምድሉን የእነ ሽመልስ ከማል ውሳኔ ተቀብዬ የተጣለብኝን አሥር ሺህ ብር መቀጮ ጓደኞቼ ከፍለው ወጣሁ። ከመኪናችን ውስጥ ሁለቱ የጦቢያ አርበኞች ደርበውና ጐሹ ነበሩ። እህቴ ዘርትሁን ከእኛው ጋር ትዳበላለች። አሁን ካሁን ጭቅጭቅዋን ትጀምራለች ስል “በሉ ከሰዓት በኋላ ሁለት ላሞች ሸጨ አሥሩን ሺ ብር እሰጣችኋለሁ። በእኔ በኩል ዛሬ የፌስታዬ ቀን ነው። የጀግና እህት ሆኛለሁ። እግዚአብሔር እኔን ጀግና አድርጐ አልፈጠረኝም። ወንድሜ ከወያኔ ጋር ተቋቁሞ…እንዲህ ሲያስከብረኝ ምነዋ አልደሰት! ሁላችንም በዕድሜና በበሽታ ተቀፍድደን ነው እንጂ ኑሮአችን በዱር በሆነ ነበር። አዎን እንደ ደሀ ጨርቅ በመርፌ እየተጠቀጠቅን.. ሽባ ሆነን ጠበቅናቸው” ስትል ሆደ ቡቡ ነኝና እንባዬን ስለቅቀው ሁለቱ ጓደኞቼ ለብዙ ጊዜ የእህቴን ንግግር የመጽናናት መልእክትና የሕዝባችንን ባሮሜትር መለኪያ ያደረጉት ይመስለኛል።( ዛሬ እህቴ ከዘመናት ክስለት በኋላ አርፋለች)

ጌቶቼና እመቤቶቼ፣ ወንድሞቼና እህቶቼ- ልጆቼም! አንድ ውለታ ዋሉልኝ። የአጤ ዮሐንስን አዋጅና ኢትዮጵያን በምን እንደመሰሉአት መላልሳችሁ አንብቡልኝ። መለስ ዜናዊና እሱን ለመሆን የሚፈልጉ ፍጡራን ለመሆኑ ይህን መሆን ሳይሆን ለማንበብ እንኳ እንደሚደነግጡ አይሰማችሁም? ኢትዮጵያ እናት፣ ልጅ፣ ሚስት፣ ዘውድ፣ መቃብር..ሁሉንም ናት። አጤ ዮሐንስን ሠራዊታቸው- የጦር አበጋዞቻቸውና ጭፍራው በሙሉ ያደነቃቸው ፊት ለፊት ፈረሳቸውን እየጋለቡና እንደ አንበሳ እየተጐማለሉ የሚመሩ ጀግና በመሆናቸው ነው። በአዋጁ ላይ እንደተመለከተው ሠራዊታቸውን በማሳሳት መልክ እንኳ ከኋላ አልተከተሉም። በመሐል ሆነው አልተደበቁም። ምሽግ አሠርተው፣ እርድ አስቆፍረው ከዚያ መምራትን አልፈለጉም። እንደ ንጉሥ ዳዊትና እንደ ትልቁ እስክንድር - እንደ አቲላና እንደ ጄንጂስካን

Tuesday, April 15, 2014

በኖርዌ ኦስሎ ከተማ የግንቦት 7 አመራር አባል አቶ ብዙነህ ፅጌ በተገኙበት ታላቅ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ

በሁለገብ ትግላችን ወያኔን እናስወግዳለን በሚል መሪ ቃል የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ በአፕሪል 12, 2014 በወቅታዊ የሐገራችን ሁኔታ ላይ ታላቅ ህዝባዊ ውይይት አዘጋጀ። በዝግጅቱ ላይ ተጋባዥ እንግዳ የነበሩት የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ብዙነህ ፅጌ ነበሩ። 

የኦስሎ ነዋሪዎች እና ከኖርዌ የተለያዩ ከተሞች የመጡ በርካታ ታዳሚዎች በዝግጅቱ ላይ የተገኙ ሲሆን በኖርዌጂያን የሰአት አቆጣጠር ከቀኑ 15፡00 የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ የህዝብ ግንኝነት ሃላፊው በወያኔ ስርአት ለተጎዱ ወገኖቻችን እንዲሁም በየእስር ቤቱ ያለወንጀላቸው ለሚሰቃዩና ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን በሙሉ መታሰቢያ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት እንዲያደርግ ታዳሚውን ጋብዘው ፕሮግራሙን አስጀምረዋል። በመቀጠል የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ዋና ሊቀመንበር የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ በተመለከተ አመሰራረቱን እና የቆመለትን አላማ እንዲሁም የትኛውን የፖለቲካ ድርጅት እንደሚደግፍ እንዲሁም ድርጅቶቹን ለምን እንደሚደግፍ እንዲሁም የድርጅቱን አላማ በማስመልከት ለታዳሚው ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ተጋባዥ እንግዳው አቶ ብዙነት ፅጌ በተራቸው ስለ ኢትዮጵያ ያለፉት መንግሰታት ከንጉሱ ጊዜ ጀምሮ የደርግን መንግስት እና አሁን እስከደረስንበት የአፈና አገዛዝ ድረስ ያለውን የኢትዮጵያ መንግስታቶች ታሪክ በዝርዝር ለታዳሚው በሚገባ መልኩ አስረድተው በተለይ አሁን ያለውን የአምባገነን ስርአት ከድሮው መንግስታቶች ጋር በማነፃፀር ምን ያህል አስከፊ እንደሆነ አስረድተዋል። ማብራሪያቸውን ከጨረሱ በኋላ የተለያዩ ታዳሚዎች በተለያዩ የሃገራችን ጉዳዮች እና ግንቦት 7 ትን አስመልክቶ ላቀረቡላቸው ጥያቄች በቂ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዝግቱ ላይ የተለያዩ አዝናኝ ባህላዊ ውዝዋዜዎች እንዲሁም ምግብና መጠጥ የተዘጋጀ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ም/ክትል ሊ/መንበር ሰፋ ያለ ቀስቃሽ የአቋም መግለጫ በመስጠት የማጠቃለያ ንግግር አድርገው ዝግጅቱ ከምሽቱ በ21፡00 በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር
ሄለን ንጉሴ/ኖርዌ