(ECADF) – ሰሞኑን የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት በጎንደርና ደሴ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ሲያስተላልፉና ቅስቀሳ ሲያደርጉ ነው የከረሙት። ሂደቱ በራሱ ከፍተኛ ትግል የተካሄደበት ነበር፣ አባላቱ ሲታሰሩ ሲፈቱ ከርመዋል፣ በደሴ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አመራር አባላት በቀን ውስጥ ሁለት ጊዜ ታስረው ተፈተዋል። ኢህአዴግ/ወያኔ ሰልፉን በቀጥታ ለማገድ ከሞሞከር አንስቶ መላ ካድሬዎቹን አሰማርቶ ህዝቡ አንድነት በጠራው ሰልፍ ላይ እንዳይገኝ ሲያግባባና ሲያስፈራራ ሰንብቶ ነው ሰልፉ የተጠራበት ቀን ሀምሌ 7 እንዳይደርስ የለም የደረሰው።
ፖሊሱና የፖለቲካ ካደሬው አንድ አካል ሆነው በሚኖሩበት ኢትዮጵያ ህዝብን ከአደጋ እንዲከላከል ከህዝብ በሚሰበሰብ ገንዘብ ደሞዝ ተቆርጦለት የተሰማራው የፖሊስ ሀይል ያለምንም እፍረት የካድሬ ስራ ያከናውናል።
በጎንደር ሰላማዊ ሰልፈኛው የሚጓዝባቸው ጎዳናዎች መጋቢ መንገዶች በፌደራል ፖሊሶች ተዘግተው ውለዋል፣ አላማቸው በተቻለ መጠን የሰላማዊ ሰልፈኛውን ቁጥር መቀነስ ነበር። ይሁንና የጎንደር ህዝብ መንገዶችን እያሳበረ፣ የሚጥለው ዝናብና መንገድ የዘጋው የፌደራል ፖሊስ ሳይበግረው ሰልፉን ተቀላቅሏል።
No comments:
Post a Comment