Saturday, June 29, 2013

የስምንት ሚኒስትሮች ሹመት ሰሞኑን ይፀድቃል


 የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ዛሬ ግምገማ ያካሂዳል
የኢህአዴግ 36 ከፍተኛ መሪዎችን ያካተተው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አመታዊ ግምገማ ለማካሄድ ዛሬ የሚሰበሰብ ሲሆን የስምንት ሚኒስትሮች ሹም ሽርና ሽግሽግ በሚቀጥለው ሳምንት ለፓርላማ ቀርቦ እንደሚፀድቅ ይጠበቃል፡፡ ለሹመት የሚቀርቡት ባለስልጣናት፤ የፍትህ ሚኒስትር፣ የከተማና ኮንስትራክሽን ልማት ሚኒስትር፣ የግብርና ሚኒስትር፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር፣ የገቢዎች ሚኒስትር የደህንነትና መረጃ ሚኒስትር፣ የደንና አካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር እንዲሁም በፓርላማ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ናቸው ተብሏል፡፡ አንዳንዶቹ ሹምሽር እርምጃዎች ሲሆኑ፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ወደ አዲስ አበባ አስተዳደር እንዲዛወሩ በተደረጉ ባለስልጣናት ምትክ የሚካሄድ ሽግሽግ ነው፡፡

ይሁን እንጂ የእጩ ተሿሚዎችን ማንነት ለማወቅ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም፡፡ ዛሬ የሚካሄደው የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ ከሹምሽሩ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ቢታሰብም፣ የሰብስባው ዋና ርዕሰ ጉዳይ አመታዊ ግምገማና አመታዊ እቅድ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት አስፈፃሚ አካል የመቆጣጠር ስልጣን ያለው የአገሪቱ ፓርላማ ጠንካራ የቁጥጥር ሃላፊነቱን በተግባር ማሳየት እንደጀመረ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጭምር ቢናገሩም፤ በሚኒስትሮች ሹመት ዙሪያ ግን የቀድሞው አሰራር አልተሻሻለም፡፡ በተለያዩ ዲሞክራሲያዊ አገራት ውስጥ የእጩ ሚኒስትሮች ማንነት በይፋ ታውቆ ለበርካታ ሳምንታት በፓርላማና በዜጐች ዘንድ ውይይት የሚካሄድበት ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ ግን የተሿሚዎች ማንነት የሚገለፀው ሹመታቸው በሚፀድቅበት እለት ነው፡፡

የስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ ዛሬ ስብሰባ እንደሚያካሂድ የገለፁት የኢህአዴግ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን፤ የስብሰባው ዓላማ የዓመቱን የስራ አፈፃፀም በመገምገም ድርጅቱ በኪራይ ሰብሳቢነት ላይ የሚያካሂደውን ትግል አጠናክሮ ለመቀጠል በእቅዶች ላይ መወያየት ነው ብለዋል፡፡ የህዝቡን ተጠቃሚነትና ተሳትፎ በማጐልበት የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትን፤ የህዝብ፣ የመንግስትና የድርጅት አቋሞች እንዲጠናከሩ፣ ችግሮች ያሉባቸውን ደግሞ አንጥሮ ለማውጣት ያለመ ስብሰባ ነው ብለዋል፡፡ በነባር ፖሊሲዎችና አሰራሮች ላይ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው መክሮባቸው አቋም ከወሰደባቸው በኋላ፤ የማስፋት፣ የማጠናከርና የማጐልበት እንዲሁም ተጨማሪና አዳዲስ ዝርዝር የአሰራር አቅጣጫዎችን በመተለም በመጪው አመት እቅድ ላይ ውሳኔ ያሳልፋል ብለዋል - አቶ ሬድዋን፡፡

Friday, June 28, 2013

ስብሃት ነጋ “እውነት” ሲያዳልጣቸው

June 28, 2013
ከኢየሩሳሌም አርአያ
ሽማግሌው ስብሃት ነጋ ከጥቂት ቀናት በፊት በሰጡት ቃለ-ምልልስ አስበውት ይሁን ሳያስቡት “እውነት” አምልጧቸዋል። አጥብቀው ያነሷቸው የሙስና ጉዳዮች ራሱን የቻለ “አላማና ግብ” አላቸው። የመጀመሪያው በፓርቲያቸው ውስጥ ያለው ክፍፍል (የጥቅም) እንደተዳፈነ እሳት ውስጥ ለውስጥ እየተብላላ መሆኑን በግልፅ ያሳያል። ከተናገሩት የሚከተለውን እንመልከት፤ “በጤናማ ሁኔታ የሚገኙ ሰዎችን እንቆርጣለን፣ እናስራለን ወዘተ እያሉ ሲያስፈራሩ የነበሩ የፖለቲካ፣ የመንግስት ሰዎች ነን የሚሉ የፀጥታና የስነ አእምሮ ሁከት ፈጥረዋል። መቶ ሚሊዮን የሰረቁና ያስዘረፉ፣ 10ሺህ ብር የሰረቀውን ሲያገላብጡት ያታያሉ።” ብለዋል። « እንቆርጣለን » ያሉት መለስ ዜናዊ ናቸው፤ መለስ በአደባባይ ይህን ከመናገር አልፈው ሲያስፈራሩም እንደነበር እናስታውሳለን። መለስ ያንን ያሉት በ10ሺዎች የሚገመት ቡና ከመጋዘን ጠፋ በተባለበት ወቅት ነው። ያንን ቡና የሰረቁትና ባህር ማዶ ሸጠው ገንዙቡን ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጭ ተጠቅሶ ይፋ ተደርጓል። እናም ስብሃት “መቶ ሚሊዮን የሰረቁ..» ያሉት አዜብ መስፍንን ሲሆን፣ « ያስዘረፉ» ያሉት ደግሞ ባለቤታቸው አቶ መለስን ነው። « 10ሺህ የሰረቁ..» የተባሉት በቅርቡ የታሰሩት የጉምሩክ ሰዎችን ሲሆን..እነዚህን በንፅፅር ያስቀመጡት የአዜብ (ተላላኪዎች) ስርቆት መጠነሰፊ መሆኑን ለማመላከት ነው። ስብሃት እስካሁን አድፍጠው ቆይተው በዚህ ሰሞን ይህን መናገራቸው ..« አዜብ የከተማዋ ም/ል ከንቲባ ይሆናሉ» የሚባለውን በመስማታቸው ሆን ብለው ያደረጉት ነው፥ ይላሉ ታዛቢዎች። በተለይ ሽማግሌውን በቅርብ የሚያውቋቸው የፓርቲው ሰዎች « ስብሃት ከበረሃ ጀምሮ በቀለኛ ነው። ጥርሱ ውስጥ የገባን ሰው ካላስወገደ እንቅልፍ አይወስደውም፤ ብዙ ሰው አጥፍቶዋል። አሁንም አዜብን እግር በእግር የሚከታተለው ለዚሁ ነው» ይላሉ። በማስከተልም ፥ « ሙስና ከተነሳ ስብሃትም እስከአንገቱ ተነክሮበታል። በገርጂና ሳር ቤት የሚገኘው <ሉሲ አካዳሚ > በአሜሪካ በሚኖሩ ስጋ ዘመዶቹ ስም እንዲሁም በቀድሞ የአየር ሃይል ጄ/ል ሰሎሞን ስም የሚንቀሳቀስ ግን የስብሃት የግል ንብረት መሆኑን የማይታወቅ መስሎት ነው?….ጎንደር -ሑመራ ያለው የሰሊጥ እርሻ የስብሃት አይደለም?…በ10ሚሊዮን ብር በሚገመት በመቀሌ (አፓርታይድ መንደር) ስብሃት ዘመናዊ ቪላ እንደሚገነባ አይታወቅም ብሎ ይሆን?…» ሲሉ እነዚህ ወገኖች የስብሃትን ሙስና በከፊል ይጠቅሳሉ።

sebehat nega one of the founders of TPLFስብሃት በዚህ አላበቁም፤ « ..እስካሁን ከፍተኛ ሙሰኞች ትንሹን ሙሰኛ ከሰው አሳስረው ያስፈርዱና ያሰቃዩ ነበር ይባላል። ከፍተኛ ሙሰኞች ከመርማሪው ጀምረው አቃቤ ሕጉም ዳኛው፣ ምስክሩም ይቆጣጠራሉ። ትንሽ የሰረቀም ምንም ያልሰረቀም ሲሰቃዩና ሲያደኸዩ የነበሩም፤ አሉም ይባላል። ስልክ እየደወሉም ይፈርዱ ነበር ይባላል።» ብለው አረፉት ስብሃት። ትክክል ናቸው!! ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ « ይህን ካልፈረድሽ በመኪና ገጭተን ነው የምንገድልሽ » ተብላለች። ያውም ከቤተ መንግስት ተደውሎ። አባተ ኪሾ ከደቡብ ባጀት ተመላሽ የሆነ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000) ለመንግስት ተመላሽ ሊያደርጉ ሲሉ …« ወዲህ በል..የምን መንግስት ነው?» በማለት ተቀብለው ኪሳቸው የከተቱት አዜብ መሆናቸውን አባተ ፍ/ቤት ጭምር ያጋለጡት ነው። ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ደግሞ ታምራት ላይኔ በውሸት እንዲመሰክር አምስት ጊዜ አግባብተውት እንቢ ሲል ከማስደብደባቸው በተጨማሪ ሌላ ክስ እንዲመሰረትበት አድርገዋል። አቃቤ ሕግ የነበረው ዮሃንስ ወ/ገብርኤል የነስብሃትን የውሸት ክስ ተቀብዬ ተግባራዊ አላደርግም፤ ህሊናዬ አይቀበለውም .. በማለቱ ብቻ ለአምስት አመት እንዲታሰር አላደረጋችሁም?…ብዙ ማስረጃና መረጃ መደርደር ይቻላል።..
አሁን ስብሃት ተናገሩት እንጂ…ህዝቡ ብሎ-ብሎ የታከተው ነገር ነው!! እነ እስክንድር፣መሃመድ አቡበከር፣ አንዷለም አራጌ፣ ርእዮት አለሙ….ወዘተ በርሶ ጓደኞች በስልክ ትእዛዝ የተፈረደባቸው ናቸው!!… «ፍትሃዊ ስርአትና መንግስት አለ..» እያሉ ህዝብን የሚያደነቁሩት እነበረከትና የጋሪ ፈረስ የሆኑት ሃ/ማሪያም እርቃናቸውን የሚያስቀር ነገር ነው በስብሃት የተቀመጠው።

የአብዬን ወደ እምዬ


ወያኔና ከወያኔ አፍ የሰሙትን ሁሉ እንደበቀቀን እየደጋገሙ የሚያነበንቡ ሎሌዎች የራሳቸውን መልክ የሚያዩበት መስታወት የተቸገሩ ይመስላል። ወየኔና ሎሌዎቹ እራሳቸውን ማየት ስለተሳናቸው ህዝብም ልክ እንደ እነሱ ኣራሱን የማያይና እነሱንና እኩይ ስራቸዉን የማያዉቅ እየመሰላቸው ሄዷል፡፡ ለዚህም ነዉ በግፈኛ አገዛዛቸው ተንገፍግፎ የሚቃወማቸውን ሁሉ ጥላሸት ለመቀባትና በራሳቸው ስም ለመጥራት ሲንጠራሩ የሚታዩት።

የወያኔ ዘረኞች የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ኃይሎች በሙሉ በፀረ-ኢትዮጵያዊነትና የአገርን ጥቅም ለባዕድ አሳልፎ በመሸጥ ሲከስሱ ስንሰማ አይናቸዉንና ፊታቸዉን ታጥበዉ አይነ ደረቅ ለመመሰል ስንት ኪሎ ጨው እንደፈጀባቸዉ መገመት ያዳግታል።
በአገራችን ታሪክ ውስጥ እንደወያኔ በኢትዮጵያ ህልውናና በወሳኝና ዘላቂ ጥቅሞቿ ላይ የዘመተ ኃይል ኖሮም ተፈጥሮም አያውቅም። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጀግኖች አባቶቻችን አጽም ያረፈበትን መሬት በስጦታ ለጎረቤት አገር እናካችሁ ብሎ የሰጠ ማነዉ? ማነው በሽፍትነት ዘመኑ ለተደረገለት ውለታና ተቀናቃኞቹን እንዲጠብቁለት በማሰብ የኢትዮጵያን ድንበር እንደ ዳቦ እየገመሰ ለባዕዳን የሸጠው?
ማነው የገዛ ወገኑን ከአያት ቅድመ አያት አጽመ ርስቱ ላይ እያፈናቀለ አንድ ሲኒ ቡና በማይገዛ ገንዛብ ለምለም መሬታችንን ለባእዳን የሚያቀራምተው? ማነው በህዝብ ስም በልመናና በችሮታ የተገኘን ገንዘብ እየዘረፈ ከአገርና ከህዝብ ደብቆ የባእድ አገር ባንኮችን የሚያደልበው? ኢትዮጵያ በሶማሊያ በተወረረችበት በ1970ዎቹ አመታት የሞቃዲሾን ፓስፖርት ተሸክመው ይንጎማለሉ የነበሩት የዛሬዎቹ የወያኔ አለቆች መሆናቸውን የኢትዮጵያ ህዝብ ገና አልረሳዉምኮ!
የዛሬዎቹ የወያኔ መሪዎች ትናንት የኢትዮጵያን ሰላምና አንድነት ማየት ከማይፈልጉ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ጋር እጅና ጓንት ሆነዉ የኛን የጎሳ ድርጅት እስከረዳችሁ ድረስ ኢትዮጵያን እናደክምላችኋለን የሚሉ ጸረ አገርና ጸረ ህዝቦች ነበሩ።እነዚህ የለየላቸዉ ከሀዲዎች ዛሬ አይናቸዉን በጨው አጥበዉ እራሳቸዉን የኢትዮጵያ ጥቅም አስከባሪ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነትና ለአገር አንድነት መከበር የሚታገሉትን ዉድ የኢትዮጵያ ልጆች የአገር ጠላት ብሎ ለመጥራት የሚያበቃ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያክል የሞራል ብቃት የላቸውም።
ወያኔዎች ስልጣን በያዙ ማግስት በጻፉትና እነሱን ሲጠቅም በሚጠቅሱት አገርንና ህዝብን ሲጠቅም ግን እየዳጡ በሚያልፉት ህገመንግስት ዉስጥ ደደቢት በረሃ የወሰዳቸዉን ዋነኛ አላማ መገነጣጠልን እንደ አገር ጥቅም በጹሁፍ ካልሰፈረ ብለው ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ የነበሩበትን ጊዜ እኛ የኢትዮጵያ ነገር የሚቆረቁረን ወገኖች አልረሳነውም። ለመሆኑ ሌሎችን በጸረ-ኢትዮጵያዊነት የሚከሰው ወያኔ እውነት ኢትዮጵያን ከወደደ መገነጣጠልን ለምን ተመኘላት? መገነጣጠልን የመሰለ አደጋ እንደ ብሔራዊ የአገር ጥቅም አይቶ የራሱን ምኞት በህግመንግስት ደረጃ ያጸደቀዉ ወያኔ እንዴት ሆኖ ነው ለኢትዮጵያ አንድነትና ክብር የሚጋደሉና የሚታገሉ ልጆቿን በሀገር ጠላትነት የሚከስሰው? የኢትዮጵያ ህዝብ ከወያኔ ጋር የሚደረገዉን ትግል ከመብትና ከነጻነት ትግል ባሻገር እንደ አገር አድን ትግል አድርጎ የሚመለከተዉ ይህንኑ ወያኔ በአገራችን ብሄራዊ ጥቅሞች ላይ በተደጋጋሚ ያሳየዉን ጠላትነት በመገንዘብ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ ተቃዋሚ ኃይሎችን በጅምላ የአገር ጠላት ለማስመሰል በሚቆጣጠራቸዉ የመገናኛ አዉታሮችና በታማኝ ሎሌዎቹ በኩል የጀመረዉን የስም ማጥፋት ዘመቻ ከወዲሁ ተረድቶ “የአብዬን ወደ እምዬ” ብሎ ትግሉን ከቀጠለ ዉሎ አድሯል። ወያኔና ለሆዳቸው ያደሩ ሎሌዎች ሁለመናቸውን የወረሰውን የፀረ-ህዝብና ጸረ ኢትዮጵያዊነት እከክ ማንም ላይ ማራገፍ አይችሉም። ድፍን ኢትዮጵያ ማንነታቸውን አሳምሮ ያውቃልና።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Biography: Nelson Mandela (video)


Biography: Nelson Mandela (video)

Nelson Rolihlahla Mandela (Xhosa pronunciation: [xoˈliːɬaɬa manˈdeːla]; born 18 July 1918) is a South African anti-apartheid activist, revolutionary and politician who served as President of South Africa from 1994 to 1999, the first to be elected in a fully representative, multiracial election. His administration focused on dismantling apartheid’s legacy, and cutting racism, poverty and inequality. Politically a democratic socialist, he served as president of the African National Congress (ANC) political party from 1990 to 1999.
A Xhosa born to the Thembu royal family, Mandela attended Fort Hare University and the University of Witwatersrand, studying law. Living in Johannesburg townships and becoming involved in anti-colonial politics, he joined the ANC, becoming a founding member of its Youth League. When the National Party government implemented apartheid in 1948, he rose to prominence in the ANC’s 1952 Defiance Campaign, being elected president of the Transvaal ANC branch and overseeing the 1955 Congress of the People. Working as a lawyer, he was repeatedly arrested for seditious activities and with the ANC leadership stood on the Treason Trial from 1956 to 1961. Although initially committed to non-violent protest, in association with the South African Communist Party he co-founded the militant Umkhonto we Sizwe (MK) in 1961, leading a bombing campaign against government targets. In 1962 he was arrested and convicted of sabotage and conspiracy to overthrow the government, being sentenced to life imprisonment.
Mandela served in Robben Island and then Pollsmoor Prison, while an international campaign lobbied for his release, which was granted after 27 years in 1990. Becoming ANC president, Mandela wrote his autobiography, and led negotiations with President F.W. de Klerk to abolish apartheid and establish multi-racial elections in 1994, in which he led the ANC to a landslide victory. As president, he created a new constitution and initiated the Truth and Reconciliation Commission to investigate past human rights abuses, while introducing policies aimed at land reform, combating poverty and expanding healthcare. Internationally, he acted as mediator between Libya and the United Kingdom in the Pan Am Flight 103 bombing trial, and oversaw a military intervention in Lesotho. Refusing to run for a second term and succeeded by his deputy Thabo Mbeki, Mandela became an elder statesman focusing on charitable work in combating poverty and HIV/AIDS.
Mandela has received international acclaim for his anti-colonial and anti-apartheid stance, having received over 250 awards, including the 1993 Nobel Peace Prize, the U.S. Presidential Medal of Freedom and the Soviet Order of Lenin. He is held in deep respect within South Africa as the “Father of the Nation”, where he is often known under his Xhosa clan name of Madiba. Controversial for much of his life, critics denounced him as a terrorist and communist sympathiser.

በረከት ስምኦን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየዶለቱ ነው


June 26 2013
Bereket Simon is the Ethiopian Communications Ministerዶር ብርሃኑ ነጋ ሊቀመንበርንት ከሚመራው ግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ በረከት ስምኦን የሚመሩት የመንግስት አካል በምስጢር እየዶለተ መሆኑን ምንጮች ጠቆሙ። በቅርቡ በአንድ ድረገፅ ላይ የወጣውን የዶ/ር ብርሃኑን ንግግር በማስረጃነት ይዘው እየተንቀሳቀሱ ያሉት አቶ በረከትና ተከታዮቻቸው በአገር ውስጥ እየተንቀሳቅሰ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ « ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለው፤ ከግንቦት ሰባት የገንዘብ ድጋፍ ይደረግለታል» በሚል እነበረከት ድምዳሜ ላይ መድረሳቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ የፓርቲውን አመራሮች «ከሽብረተኛ ቡድን ጋር በመገናኘት» ብለው ለመክሰስ ሴራ እያበጃጁ መሆኑን አስውታውቀዋል።

የፓርቲው አመራሮችን ከማሰር ባለፈ «ሰማያዊ ፓርቲ በሽብርተኛ ድርጅት የሚረዳ ነው» በሚል በአገር ውስጥ የሚኖረውን የፓርቲው ቀጣይ ህልውና ለማክሰም ጭምር እየዶለቱ መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል። ከበረከት በተጨማሪ ደብረፂዮን ይህንን ሴራ በበላይነት እየመከሩበት እንደሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ አሜሪካ ለሚገኝ አንድ ጋዜጠኛ ከገዢው ባለስልጣናት ዳጎስ ያለ ገንዘብ እንደተላከለት የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። መጀመሪያ 250.000 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) ፣ በማስከተል 50.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ሃዋላ እንደተደረገለትና ባጠቃላይ 300.000 (ሶስት መቶ ሺህ ብር) በዶላር ተመንዝሮ በእጁ እንደደረሰው ምንጮቹ ጠቁመዋል። ገንዘቡ ከነበረከት በኩል በምስጢር የተላከ መሆኑን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚሁ መሰረት ጋዜጠኛው ለሕወሐት/ኢህአዴግ ማገልገል መቀጠሉንና በተለይ አሁን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየተሸረበ ያለው ሴራ መነሻው ይህ ሰው እንደሆነ አያይዘው ገልፀዋል።
ከኢየሩሳሌም ኣርአያ

Monday, June 24, 2013

የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአፍጋኒስታን ገበያ አገኘ እንዴ?

June 24, 2013

ሐቅ! የአየር መንገዳችን የጭነት ጥያራዎች በግንቦት እና በያዝነው ሰኔ ወራት ወደ አፍጋኒስታን ደፋ ቀና ሲሉ ታይተዋል። (Flight Radar24.com ድረ-ገጽን ይመልከቱ)
ሐቅ! አየር መንገዱ ስድስት የጭነት ጥያራዎችን አሰማርቶ በቋሚ መልክ ወደ አውሮፓ፤ መካከለኛው ምሥራቅ እና እስያ ሸቀጣ ሸቀጥ ያመላልሳል። ኾኖም አፍጋኒስታን በቋሚነት ከሚበርባቸው አገሮች መኻል ያልተመዘገበች ከመሆኗም ባሻገር በጦርነት ከተዘፈቀች አገር ጋር ምን ዓይነት ንግድ ተጀመሮ ይሆን የሚያስብሉ ሰባት በረራዎች ቀልቤን ሊስቡት ችለዋል።
ሐቅ! አፍጋኖቹ ያለፉትን ሦስት-አሥርት ያህል ዓመታት ያሳለፉት እርስ በርስ በመፋጀት፤ በመፈራረቅ አገራቸውን የያዙባቸውን የሁለቱን ኃያላን መንግሥታት ወራሪ ሠራዊቶች በመከላከል እና በመኻሉም አክራሪ-ሃይማኖተኝነትን መርኅ በማድረግ ነው። የአገራቸው መልክዓ-ምድር እንደ ኢትዮጵያ ተራራማ ከመኾኑም ባሻገር የገጠሩ ዜጋ አኗኗር የኛውኑ ገጠሬ ጋር ይመሳሰላል። በጎቻቸው እንኳ በላት ምትክ ቂጣሞች ይሁኑ እንጂ የኛውኑ የአዳል ሙክት ነው የሚመስሉት። ግን ከኋላቸው ሲያስጠሉሉሉሉሉሉ!
afghanistan sheeps and Ethiopia
እንግዲህ ለዚህ መጣጥፍ መነሻ የሆነኝ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዩ የጭነት በረራዎች በግንቦት ወር አራት (የመጀመሪያው በረራ ግንቦት 14 ቀን 2005 ዓ/ም ነበር) ጊዜ
እና በያዝነው የሰኔ ወር ደግሞ ሦስት ተመሳሳይ በረራዎች (ወሩ ገና ስላላለቀ ሌሎችም ሊኖሩ ይችላሉ!) የአሜሪካ ሠራዊት የሚጠቀምበትን የካንዳሃር ጥያራ ጣቢያ ሲጠቀሙ መገንዘቤ ነው። ለአሜሪካ ሠራዊት የቀንድ ከብት ጭነው ይኾን እንዴ? አይ ግዴላችሁም አበባ መሆን አለበት! ግን አንዱ በረራ ከሊዬዥ ቤልጂግ ተነስቶ ካንዳሃር ካረፈ በኋላ መልሱን በሆንግ ኮንግ በኩል ሲያደርግ ነዋ የታየው። ስለዚህ ጭነቱ አበባ ቢሆን ኖሮ ከአዲስ አበባ፣ ሊዬዥ፤ ከሊዬዥ ዱባይ፤ ከዱባይ ካንዳሃር እስከሚገባ አበባው የሚጠወልግ እና የኪሣራ ኪሣራ ነው የሚሆነው።

ወይ ከአፍጋኒስታን እነኛን የአዳል ሙክት የሚመስሉትን በጎች መንግሥታችን ሸምቶልን ይሆናላ! አይ፣ ወይ የሁዳዴ ወይ የረመዳን ጾም መፍቻ ወቅት ቢሆን ኖሮ በግ ተሸምቶልን ነው ለማለት ይቻል ይሆን ነበር። በግንቦትና በሰኔ ወራት ግን አይመስልም። እሺ! አየር መንገዳችን ሰራተኞቹን በጭነት አውሮፕላን እያጓጓዘ የዓመት እረፍታችውን በራሱ ወጭ አፍጋኒስታን ወስዶ ማዝናናት ጀመረ እንዴ ? እንደዚያ ከሆነ ጎረቤት አገር ኬንያ እየወሰደ ቢያዝናናቸው ወጭው አይቀልለትም ኖሯል ? ደግሞስ ጦርነት እሚካሄድበት አገር ወስዶ ለአደጋ ቢያጋልጣቸው የዋስትና ሽፋኑ አይከሽፍበትም ? አይ ምክንያቱ ይኼም ሊሆን አይችልም። በነገራችን ላይ ምንም ጭኖ ወይም ለመጫን ይሁን አፍጋኒስታን የሄደው በሽብር መኻል ጥያራው የተንኮል አደጋ ቢደርስበት የአየር መንገዱ ዋስትና ይሸፍነው ይኾን?
Ethiopian Airlines, cargo planes in Afghanistan
ታዲያ በስድስት ጠብድያ የጭነት ጥያራዎች የተጓጓዘው ምንድነው እንበል ? ምነው ዴሞክራሲ እና ግልጽነት በሰፈነበት አገር ተወልደን በሆነ ኖሮ? አየር መንገዳችን በየአንዳንዱ በረራው ከየት ተነስቶ ወዴት፤ ምን ጭኖ እንደሚንቀሳቀስ፤ በጥያራው ግዥ ያባከንነው ገንዘባችን ለኛው ትርፍ እየተሰራበት መሆን አለመሆኑን እና የመሳሰሉትን ጥያቄዎቻችንን የመጠየቅ ብቻ ሳይሆን አጥጋቢ መልስ የማግኘት መብትም ይኖረን ነበር።

ቆይ ቆይ! የአሜሪካ ሠራዊት ከአፍጋኒስታን የመውጣት ዝግጅቱን እያጧጧፈ ነው የሚል ትንተና አንብቤ የለም እንዴ? አዎ! ሠራዊቱ ቁሳቁሱን አጠቃሎ እ.አ.አ. 1914 መጨረሻ በፊት እንዲወጣ በተወሰነው መሠረት የጊዜ ገደቡ ከመድረሱ በፊት ለማገባደድ ዝግጅቱን እያመቻቸ ይገኛል። የተከማቸውን የጦር መሣሪያ በያይነቱ፤ የመመላለሻ መኪናዎች፤ የተቀበረም ኾነ በሽምጥ የተነጣጠረ ፈንጂ መቋቋም የሚችሉ ተንቀሳቃሾችን (በእንግሊዝኛው Mine-Resistant Ambush Protected (MRAP) vehicles ይሏቸዋል) ማንሳት ይጠይቃል። ታዲያ ዕድሜ ለኅብረ-መረብ (ኢንተርኔት)፤ ሰሞኑን ያነበብኳቸው መጣጥፎች እንደሚገልጹት፣ ከአሜሪካው ዜጋና የሕዝብ ተወካዮች ሸንጎ የተደበቀ መፍትሄ ቢሆንም የሠራዊቱ ዓለቆች ከሃያ በመቶ (በግምት ሰባት ቢሊዮን ዶላር) የሚኾነውን የጦር መሣሪያና ተሽከርካሪዎች፤ የመገናኛ ቁሳ-ቁሶችና ንብረት — አላስፈላጊ ወይም ወደአሜሪካ የማጓጓዣው ወጭ ይከብዳል የሚል ውሳኔ ላይ ደርሰዋል — ከቻሉ ወዳጅ አገራት በራሳቸው ወጭ አስነስተው መውሰድ እንደሚችሉ፤ በዚህ ዓይነት ያልተነሳውን (ብልጫውን) ደግሞ እዚያው አፍጋኒስታን ውስጥ በመሰባበር ማውደም ላይ መኾናቸው ተዘግቧል።
ለምሣሌ የአሜሪካው ሠራዊት በአፍጋኒስታን ካሰማራቸው አሥራ-አንድ ሺ (አሥራ-አንድ ሺ) ኤም. አር. ኤ. ፒ. መኪናዎች (እያንዳንዳቸው አንድ ሚሊዮን ብር ነው ያወጡት!) ሁለት ሺዎቹን መልሶ እንደማይወስድ (ከነኚህም አብዛኛዎቹ ማጓጓዣቸውን አመቻችቶ የሚወስድ ወዳጅ አገር ስለሌለ እዚያው እንደሚሰባበሩ) ቀሪዎቹ ዘጠኝ ሺ መኪናዎች ደግሞ ወደአሜሪካ እና በየአገሩ ወደተሠማሩት የአሜሪካ ሠራዊት እዞች (ይሄም ኢትዮጵያን ሊመለከት ይችላል) እንደሚላኩ የፔንታጎን ቃል አቀባዮች መግለጻቸውን አንብቤያለሁ። ጉድ እኮ ነው!
ታዲያ ወያኔ ምኑ ሞኝ ነው! የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት ጥያራዎችን አሰማርቶ በነፃ የሚገኘውን መሣሪያ እና ኤም. አር. ኤ. ፒ. መኪናዎች ለማንሳት ነዋ ወደካንዳሃር ያዘዛቸው! በርሮበት ወደማያውቀው ጥያራ ጣቢያ፤ የኔ ብጤውን ተከታታይ ለማደናበር ሰባቱንም በረራዎች ከካንዳሃር በቀጥታ ወደሆንግ ኮንግ በማብረር (መሠረታዊ የጭነት በረራ መሥመር ባይሆንም እንኳ ሆንክ ኮንግ ከካንዳሃር የተሻለ ታማኝነት ይኖረዋል) ያለጥርጥር መሣሪያውን በምሥጢር እያጓጓዙ ነው ወደሚለው ድምዳሜ በበኩሌ የደረስኩ መሆኔ ይሰመርልኝ።
መችም “የስጦታ ፈረስ ጥርሱ አይገለጥም” የሚባለው የአባቶች ብሒል አይታዘበኝና፤ ገዢው የወያኔ ኃይል ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት ከመቶውን ወንበር በሚቆጣጠርበት “የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት” (ድንቄም የሕዝብ ውከላ እቴ!) ያሉት አንድዬው ተቃዋሚ አቶ ግርማ ሰይፉ እውነታውን ተገንዝበው ጥያቄ ቢያቀርቡም እንኳን ምናልባት ከአቶ መለስ የለመድነውን የትዕቢት ዘለፋ ከማትረፍ በቀር እውነት ያለበትን ጎራ እንኳ አቅጣጫ ይጠቆማሉ ብሎ ማሰብ ከንቱ ነው። እንኳን የአሜሪካኖቹ ትርፍራፊ በኛው ላይ ሊነጣጠር የታሰበ ሊሆን እንደሚችል ሊነገረን ቀርቶ ለምጽዋቱ እንኳን እንደባህላችን “እግዚአብሔር ይስጥልን” ለማለት አይፈቀድልንም። ታዲያ አቶ ኦባንግ ሐሙስ ዕለት በአሜሪካው ኮንግረስ ላይ “እራሳችንን እኛው ነፃ እናወጣለን። እናንተ ግን የመንገድ እንቅፋት አትሁኑብን!” ያሉዋቸውን በአንድ ፊት እናዳምጣለን የሚሉን አሜሪካኖች በጎን ወያኔን በምስጢር እስከቅንድቡ ድረስ እያስታጠቁት ነው።
እንግዲህ ለተጋለጡት በረራዎች የወያኔ አካላትም ሆኑ ደጋፊዎቻቸው ምክንያት አድርገው ሊያቀርቡ የሚችሏቸውን መልሶች በመንደርደሪያዬ ላይ እንደሸፈንኳቸው ተስፋ እያደርግሁ ያልተለመደ፤ ያልተገለጸ፤ የንግድ ዓላማ ሊኖረው የማይችል እና ማደናበሪያ አቅጣጫዎችን ያካተተ ከካንዳሃር አፍጋኒስታን የሚነሱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት ጥያራ በረራዎች የጦር መሣሪያዎችንና ወታደራዊ ቁሳ-ቁሶችን ለማንሳት ካልሆነ በቀር ሌላ ምክንያት አልታየኝም። ይልቁንስ ተቃዋሚ ቡድኖች ካሁኑ ማንሳት ያለባቸው 1ኛ) አሜሪካኖቹ በነፃ ውሰዱ ያሉትን ከፍ ያለ ዋጋ ከፈልንበት ብለው የለመዱትን ብዝበዛ እንዳያካሂዱ 2ኛ) ምስር ልትወጋን እየተነሳሳች ስለሆነ መከላከያ መሣሪያ ብለን ነው እንዳይሉ ከምስር ጋር እያካሄዱት ያለው የአፍ ጦርነት በሁለቱም በኩል የገዥ አካላቱን ዕድሜ ማራዘሚያ ስልት እንጂ ሌላ ምንም ትርጉም የሌለው መሆኑን 3ኛ) ምዕራባውያን በፊት ለፊት የዴሞክራሲ፣ የሰብአዊ መብት፣ ወዘተ
ደጋፊናተቸውን በመለፈፍ እየሸነገሉ በኋላው በር ግን እኛኑ የሚያስቀጥቀጥ ግፊታቸውን እንደማያቆሙ እንደነቃንባቸው ማሳወቅ ነው።
ይመኩ ታምራት (ከሎንዶን)
ሰኞ ሰኔ 17 ቀን 2005 ዓ/ም
ምንጮች
* http://www.flightradar24.com
*Scrapping equipment key to Afghan drawdown By Ernesto Londoño,June 19, 2013
http://articles.washingtonpost.com/2013-06-19/world/40067061_1_afghanistan-war-mineresistant-

አሜሪካ አቋማን የምትፈትሽበት ወቅት ላይ ናት” ክሪስ ስሚዝ



"አሸባሪነትን መዋጋት የግፍ ማከናወኛ ሽፋን አይሆንም"
gear 1
ኢህአዴግ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ስም ከአሜሪካ ጋር የመሰረተውን ግንኙነት አስታክኮ የሚፈጽመው ኢሰብዓዊ ድርጊት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ተገለጸ። አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምትከተለውን ፖሊሲ የምትመረምርበት ወቅት ላይ ትገኛለች ተባለ። ኢህአዴግ ጸረሽብርተኝነትን ለአፈናና ለበጀት ማሟያ እየተጠቀመበት እንደማይቀጥል ተመለከተ።
አሜሪካና ሌሎች ለሰብአዊ መብት መከበር ዋጋ የሚሰጡ አገሮች በሙሉ በ”አዲስ አበባው” አገዛዝ ላይ ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ያለ አንዳች ማወላወል ማሳየት እንደሚገባቸው እንደራሴ (ኮንግረስማን) ክሪስ ስሚዝ ያስታወቁት ሽብርተኛነትን አስመልክቶ ጠንካራ ማሳሰቢያ በማስቀመጥ ነው።
እንደራሴ ስሚዝ የኢትዮጵያ ጉዳይ የተደመጠበትን የምክክር ሸንጎ ከዘጉ በኋላ በተለይ ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት “አሜሪካ በኢህአዴግ ላይ ያላትን አቋም የምትመረምርበት ወቅት ላይ ትገኛለች” ብለዋል።
አሜሪካ ከሰብአዊ ርዳታ ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግና በተለይም ኢትዮጵያና አሜሪካ አሸባሪነትን በመዋጋት በኩል አብረው እንደሚሰሩ ያመለከቱት እንደራሴው፣ “ሽብርንና ሽብርተኛነትን የመታገል ትብብር ግን የዜጎችን ሰብአዊ መብት ለመርገጥ ፍቃድ ማግኛ አይደለም። የመብት ረገጣ ሽፋን ሊሆን አይገባም” በማለት የኢህአዴግና የመሪዎቹን ተግባር ኮንነዋል።
“አንድ አገር ገና ለገና ሽብርተኛነትን ለመዋጋት ከአሜሪካ ጎን ስለቆመ ብቻ የህዝብ ሰብአዊ መብቶችና የዴሞክራሲ አተገባበር ላይ ዝም ሊባል አይገባም” በማለት አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት ስሚዝ፣ ሽብርን መዋጋት የኢትዮጵያ የራስዋም ፍላጎት አንደሆነ አመልክተዋል።
“ስለዚህ” አሉ ክሪስ ስሚዝ፣ “ስለዚህ የአሜሪካ መንግስትም ሆነ ሌሎች የምራብ አገራት፣ ኢህአዴግ ኢትዮጵያዊያን ላይ እየፈጸመ ያለውን ተግባር በመረዳት አቋማቸውን በግልጽ ማስቀመጥ ይገባቸዋል”
“ለሰብአዊ መብት መከበር ዋጋ የሚሰጡ አገሮች በአዲስ አበባው መንግስት ላይ የማያወላውል ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ማሳየት አለባቸው” ሲሉ የተደመጡት ክሪስ ስሚዝ “ከዚህ ቀደም አርቅቄ፣ አስተዋውቄ፣ ለውይይት አቅርቤው የነበረውን ኤች አር 2003 ህግ እንደገና በማሻሻል ለድምጽ አቀርበዋለሁ” ብለዋል።
“የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ህገደንብ” የሚል ስያሜ ያለው ህግ፣ ኢትዮጵያን የሚመራው ኢህአዴግ ከአሜሪካ መንግስት ለሚፈልገው ማናቸውም ድጋፍ መሟላት የሚገባቸውን የሰብአዊና የዴሞክራሲ መብት ግብአቶችን በቅድመ ሁኔታ የሚያስቀምጥ ነው። እንደራሴ ክሪስ እንደገና ለድምጽ እንደሚያቀርቡት ደጋግመው የገለጹት ይህ ህግ ኢህአዴግ በከፍተኛ ደረጃ ገንዘብ አፍስሶ በአሜሪካን ጎትጓቾች (ሎቢዪስቶች) ዘመቻ ያካሄደበት ነው።
መለስን ”አሮጋንት/ዕብሪተኛ/“ በመለት የገለጹት ክሪስ ስሚዝ “ከመለስ ሞት በኋላ ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ አቅጣጫ ታመራለች” የሚል እምነት እንደነበራቸው በመናገር “የሰማሁት ምስክርነት ከዚህ የተለየ፣ ተስፋ ከተደረገው ተቃራኒ ነው” ብለዋል። እሳቸው ብቻ ሳይሆኑ “ብዙዎች” ሲሉ በጥንቃቄ የገለጹዋቸው አካላት ከመለስ ሞት በኋላ በተመሳሳይ ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ መንግድ ታመራለች የሚል እምነት እንደነበራቸው ሳይሸሽጉ ተናግረዋል። በውል የተየው ነገር ኢትዮጵያዊያን ወደ ባሰበት ችግርና የመብት ረገጣ የመዘዋወራቸው ጉዳይ እንደሆነ አመልክተዋል። ይህም አሳሳቢ እንደሆነ ጠቁመዋል።
በማብቂያቸውም “አሁን ፖሊሲያችንን ዳግም የመፈተሽያ ጊዜ ላይ ነን። ቁም ነገሩ ከተጨቆኑት ወገኖች ጋር መቆሙ ላይ ነው። ከተጨቆኑት ወገኖች ጋር እንቆማለን” የሚል ከተለመደው የአሜሪካ አቋም የተለየ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አቶ ኦባንግ ሜቶና ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የተገኙበትን የምክክር ሸንጎ ተከትሎ እስካሁን ድረስ የኢህአዴግ አቋምና ምላሽ አልታወቀም። ይሁን እንጂ ቀደምሲል ኤች አር 2003 ህግ ሆኖ እንዳይጸድቅ ኢህአዴግና ወዳጅ ባለሃብቶች ተመሳሳይ ተግባር ለማከናወን ሩጫ መጀመራቸው ተሰምቷል። በተጨማሪም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የዲፕሎማሲ ጅምናስቲክ መጀመሩ ታውቋል።
የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በተለያየ ወቅት መለስ በሽብርተኛ ትግል ሰበብ አሜሪካንንና የምዕራቡን ዓለም እያምታቱ እንደሆነ በተደጋጋሚ መገለጹ ይታወሳል። ሆን ተብሎ በተሽከርካሪዎች ላይ የተቀነባበረ የፈንጂ ማፈንዳት፣ ህዝብን የማሸበር ተግባር እንደሚፈጸም በማመልከት ተቃዋሚዎች ሲጮሁ ሰሚ አልነበራቸውም። የሹልክዓምድ (ዊኪሊክስ) መረጃ ይህንኑ ይፋ ማድረጉና ኢህአዴግ ራሱ ፈንጂ አፈንድቶ “አሸባሪዎች ፈንጂ አፈነዱ” በሚል እንደሚያምታታ ማጋለጡ ይታወሳል።
አቶ መለስ አሜሪካና ምዕራባዊያን ሰብአዊ መብትን፣ ምርጫንና የዲሞክራሲ መብቶችን አስመልክቶ ጥያቄ ሲያቀርቡላቸው “ጦራችንን ከሶማሊያ እናስወጣለን፣ ቀጠናው ቢተራመስ ተጠያቂ አይደለንም” የሚል ምላሽ  እየሰጡ ያስፈራሩ እንደነበር የሚጠቁሙ የጎልጉል ምንጮች “ኢህአዴግ ብር ሲፈልግና ካዝናው ሲጎድል ዘወትር የሚያነሳው የሽብርና አሸባሪዎችን የመታገል ውለታ ድርጎ ነው” ብለዋል። በ1997 ምርጫ ወቅት የተሸነፈው ኢህአዴግ በወቅቱ አሜሪካን ጫና ልታደርግ ስትሞክር “ሰራዊታችንን ይዘን ወደ ክልላችን እንገባለን። ተቃዋሚዎች ጦር የላቸውም። በቀጣናው ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂ አይደለንም” በማለት አቶ መለስ አሜሪካን ጫናዋን አቁማ ከህወሃት ጎን እንድትቆም ማድረጋቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ይናገራሉ። ያም ሆነ ይህ እንደራሴ ክሪስ ስሚዝ ኢህአዴግ የውጪውን ዓለም የሚጋልብበትን የፖለቲካ “ጆከሩን” ወይም “ሽብርን መታገል” መርጠው ” ካሁን በኋላ በዚህ ሂሳብ መጫወት አይቻልም” ማለታቸው ቀጣዩን የፖለቲካ ጨዋታ እንደሚያከረው ተገምቷል።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ  እንወዳለን፡፡

Saturday, June 22, 2013

የናይል ተፋሰስ ሚኒስትሮች ተሰበሰቡ



ደቡብ ሱዳን በናይል ወንዝ ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ለመገንባት 16 ቦታዎችን መምረጧል አስታወቀች፡፡


ከናይል ተፋሰስ ሃገሮች የምክክር ስብሰባዎች አንዱባለ አምስት ቢሊየን ዶላር መዋዕለ-ነዋዩ ኅዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን ጎረቤቶች ቀልብ አነቃቅቶና ውዝግቦችም እየተሰሙ ባሉበት ሁኔታ ውስጥ በአባይ ውኃ አጠቃቀም ላይ ለመምከር የአባይ ተፋሰስ ሃገሮች ድርጅት ስብሰባ ደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ላይ ዛሬ ተሰብስበዋል፡፡


የኅዳሴ ግድብ ወደ ግብፅ የሚወርደውን ውኃ መጠን ይቀንስብናል ሲሉ ግብፃዊኑ ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ሥጋታቸውን በየጊዜው እየገለፁ ነው፡፡ በዚህ ወር መጀመሪያ ደግሞ የግብፅ ፕሬዚዳንት ሞሐመድ ሞርሲ በውኃ ደኅንነታቸው ላይ የሚፈጠርን “ማንኛውንም ሥጋት ለመያዝ ‘ሁሉም አማራጮች ክፍት’ ናቸው” ባሉ ጊዜ በውኃው አቅርቦት ላይ ያላቸውን ፍርሃት ጠቁመው እንደነበርና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ በሰጡት ምላሽ የግብፅ መሪዎች “… ካላበዱ በቀር የጦርነትን አማራጭ ይወስዳሉ ብለን አናምንም …” ብለው ነበር፡፡

በናይል ሃገሮች መካከል የሰፋ ትብብር እንዲፈጠር የአሥር የተፋሰሱ ሃገሮች ሚኒስትሪዎችን መሪዎች የጁባ ስብሰባ በከፈቱ ጊዜ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ተጠሪው ባርናባ ማሪያል ቤንጃሚን ጥሪ አሰምተዋል፡፡

የኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር አቶ አለማየሁ ተገኑም ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ የጀመረችውን ግድብ ግንባታ ሥራ እንደማታቆም አስታውቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የማንንም ሃገር የመሻሻል ዕድል እንደማትቃወም የተናገሩት የግብፅ የውኃ ኃብቶች ምክትል ሚኒስትር አሕመድ ባህ ኤልዴይን ይሁን እንጂ ናይል ወንዝን በተመለከተ ማንኛቸውም ዕቅዶች ከመነደፋቸው በፊት መዘዞች ሁሉ ግምት ውስጥ ሊገቡ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡


ከናይል ተፋሰስ ሃገሮች የምክክር
የናይል ተፋሰስ ሃገሮች

Friday, June 21, 2013

ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ስራቸውን እየሰሩ ነው ማለት ነው!


June 21, 2013

Bucknell University Professor of Economics Berhanu Nega
ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ የግንቦት ሰባት ሊቀመንበር።
ሰሞኑን ከኢህአዴግ ጋር የስጋ ዝምድና አላቸው እየተባሉ የሚጠረጠሩ ወዳጆቻችን ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ከአንዳች ሀይል ኢህአዴግን ለመገዳደሪያ የሚሆን ገንዘብ እንዳገኙ የሚያሰማ ድምፅ አጋርተውናል፡፡ ችግሩ ግን ይህ ገንዘብ ከየት እንደተገኘ እርስ በርሳቸው ስምምነት ላይ አልደረሱም፡፡ አንዳቸው ከኤርትራ ነው ሲሉ ሌላኛው ደግሞ ከግብፅ ነው ይላሉ፡፡ በደንብ ጆሮ ጣል ብናደርግ ከኢህአዴግ መንግስት ነው የሚልም አይጠፋም፡፡
ወዳጆቻችን ያጋሩን ድምፅ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ከሆነ ቦታ የተገኘውን ብር፤ ለእንትን ይሄን ያህል፣ ለእንትና ይሄን ያህል እያሉ ሲናገሩ ያስደምጣል፡፡ በዚህ ላይ ያስደነቀኝን ልናገር እና እመለሳለሁ ቆይ አዲስ መስመር ላይ እንገናኝ፡፡
ዶክተሩ የሆነውን ብር እዛው ለመከላከያ እና ደህንነቱ የተበጀተ ነው፤ ሲሉ ሰማናቸው፡፡ ይሄኔ በተለይ እንደኔ በኢህአዴግዬ ፍቅር የተለከፈ ሰው ክው!!! ማለቱ አይቀርም፡፡ ደህነነት እና መከላከያችን ከመንግስት ከሚመደብለት በጀት ውጪ በግንቦት 7 ደግሞ ሌላ በጀት አለው ማለት ነው፡፡ ይቺን ነው መፍራት፤ ዶክተሩ ስራቸውን ቀጥ ለጥ አድርገው እየሰሩ ነው ማለት ነው፡፡ 

ታድያ ለዚህ ነዋ የኢህአዴግዬ ገመናዋ ሁሉ ቀድሞ አደባባይ የሚሰጣው!!! እኔ ልሰጣ … ልበል ወይስ አልበል! (በቅንፍም ይቅርብኝ እነ እንትና ሳይሉ እኔ ቀድሜ ልሰጣ… ብል እነሱን ማሳጣት ሆንብኛል!) ከቅንፍ ስንወጣም ለኢሳትም የሆነ ብር ይሰጣል ሲሉ ዶክተሩ መናገራቸውን አዳመጥኩ፡፡ በእውነት ዶክተርዬ የተባረኩ ኖት፡፡ … እንዴ… በአሁኑ ጊዜ ማን እንደዚህ ያደርጋል… የምር እኮ ኢሳትን ሁሉም መርዳት አለበት፡፡ ግንቦት 7 ከረዳው በጣም ጥሩ ጅምር ነው፡፡ እንኳን ሌላ ቀርቶ ግንቦት 20 ም ራሷ ኢሳትን መርዳት አለባት፡፡ እንዴ ኢቲቪ የማይሰራውን በሙሉ የሚሰራው ኢሳት አይደለ እንዴ…! ታድያ እንዲህ እንዲተጋገዙ ሁሉም የአቅሙን ቢያዋጣ ምን ችግር አለበት!
ወደ ዋናው መስመር ስመለስ ወዳጆቻችን “ፈልፍለው” ይፋ ባደረጉት መረጃ ዶክተሩ ለካስ አልተኙም ብለናል፡፡ እና ይበርቱ ልንላቸው ይገባል፡፡
ገንዘቡ ከግብጽ ነው፤
ግብፅ የምር ለኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ገንዘብ የምትረዳ ከሆነ ተጃጅላለች ማለት ነው፡፡ ሌላ ቀርቶ ኢህአዴግ እንኳ ያንን ሁላ አድርጋለት አልተመለሰላትም፡፡ በእውኑ ሌሎቹማ ከኢህአዴግ የበለጠ ለሀገራቸው ተቆርቋሪ አይደሉምን…!
ገንዘቡ ከኤርትራ ነው፤
ወይ…. ኤርትራ….!!! አሁን ማን ይሙት ኤርትራዬ ከራሷ አልፋ ለሌላ ሰው ይሄንን ያክል ብር መስጠት ትችላለች…! ይሄንን ሃሳብ የሰነዘሩ ሰዎች በእርግጠኝነት ኤርትራዊያን ናቸው፡፡ አላማውም የኤርትራም መልካም ገፅታ ለመገንባት ሳይሆን አይቀርም ብለን እኛ ጠርጣሮቹ እንጠረጥራለን!
የትም ፍጪው ኢህአዴግን አስወጪው፤
ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ግንቦት 7 የሚባል ተቃዋሚ ፓርቲ መስርተው ሁለገብ በሆነ ዘዴ ኢህአዴግን ወግድ እለዋለሁ ብለውናል፡፡ ግንቦት 7 ይህ ከሆነለት የዘመናት ብሶት የወለዳቸው ሁሉ ተሰባሰበው ዋንጫ እንደበላ ሰው “የእርግብ አሞራ” እያሉ የሚጨፍሩለት ደስታ የሚሆን ይመስለኛል፡፡ ታድያ ለዚህ አላማ ገንዘብ ከየትስ ቢያመጡ እኛ ምን አገባን…!?
ከአቤ ቶክቻው የፌስቡክ ገጽ የተወሰደ

UDJ calls for national protest


(Reuters) – An Ethiopian opposition party called on Thursday for the government to scrap an anti-terrorism law it says is used to stifle dissent, threatening a repeat of protests that brought thousands onto the streets of Addis Ababa early this month.
The rally on June 2, organized by another opposition group, was the first large-scale protest in the Ethiopian capital since a disputed 2005 election ended in street violence that killed 200 people.
Opposition groups in the Horn of Africa country were vibrant until that vote but have since largely retreated from public view, the result, analysts say, of harassment by the authorities and divisions within their ranks.
They routinely accuse the government of intimidating and imprisoning their members and rigging elections against them. Ethiopia’s 547-seat legislature has only one opposition member.
The anti-terrorism law ratified in 2009 makes anyone caught publishinginformation that could induce readers into acts of terrorism liable to jail terms of 10 to 20 years. Opponents say it is used indiscriminately to target anyone who opposes government policy.
“We shall demand that the anti-terror law be abolished immediately. It contradicts the constitution and violates the rights of people,” Unity for Democracy and Justice (UDJ) party spokesman Daniel Tefera said at a news conference in Addis Ababa.
In a statement, UDJ said the government was doing too little to tackle unemployment and corruption and announced a campaign of nationwide debates and rallies.
“If there is no positive response from the ruling regime, we shall go to court with the millions of signatures in our hands,” it said.
More than 10 journalists have been charged under the anti-terrorism law, according to the Committee to Protect Journalists, which says Ethiopia has the highest number of exiled journalists in the world.
The government dismisses the claims that it is cracking down on dissent and says the law is needed it its fight against separatist rebels and armed groups who it says are backed by arch-foe Eritrea.
Analysts say the opposition may have found renewed vigor since the death last year of Prime Minister Meles Zenawi, who was praised abroad for delivering strong economic growth but criticized for keeping a tight grip on power for 21 years.
Prime Minister Hailemariam Desalegn has for now shown no sign of a major shift in policy away from his predecessor.

Thursday, June 20, 2013

የግንቦት7 ሊቀመንበር ዶ.ር ብርሀኑ ነጋ ፣ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ እና ሌሎችም ምሥክርነት ሰጡ


ሰኔ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- የአፍሪካ ጉዳዮች ሃላፊ ዶናልድ ያማማቶ፣ በአፍሪካ የዩሴ አይ ዲ ዳይሬክተር ኤሪል ጋስት፣ በአፍሪካ  ጉዳዮች ተመራማሪ  ዶ/ር ፒተር ፓሀም፣ የግንቦት7 ሊቀመንበር ዶ.ር ብርሀኑ ነጋ ፣ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር  አቶ ኦባንግ ሜቶና የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የአሜሪካ ተወካይ  ሚስተር አዶቲ አኪዌ እና ሌሎችም ታዋቂ ምሁራን ፖለቲከኞች የተሳተፉበት ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ አምባሳደር ያማማቶ እና ዶ/ር ጋስት ኢትዮጵያ በመስቀለኛ መንገድ ላይ እንድምትገኝ ገልጸዋል።
የኢህአዴግ መንግስት የኢኮኖሚ እድገት ማምጣቱን የገለጹት አምባሳደር ያማማቶና ሚስተር ጋስ፣  በሌላ በኩል ግን መንግስት ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብቶች ረገጣ በመፈጸሙ የአገሪቱን መጻኢ እድል አደጋ ላይ ጥሎታል ብለዋል።
ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ፣ አቶ ኦባንግ ሜቶ እና ሚ/ር አክዌ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን፣ ዶ/ር ብርሀኑ ከአቶ መለስ ሞት በሁዋላ ያለው የኢትዮጵያ ሁኔታ በመለስ ጊዜ እንደነበረው ምናልባትም ከዚያ በበሳ ሁኔታ አስከፊ እየሆነ መሄዱን ገልጸዋል። የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከፍተኛ ገንዘብ የዘረፉ እና ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን የፈጸሙ በመሆናቸው እንጠየቃለን በሚል ፍርሀት ስልጣን በቀላሉ ለመልቀቅ እንደማይፈልጉ ዶ/ር ብርሀኑ አክለዋል።
ዶ/ር ብርሀኑ መንግስትን በሀይል ለማውረድ የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች እየተጠናከሩ መሄዳቸውን፣ አገሪቱ ወደ አልተፈለገ ግጭት ከማምራቷ በፊት የአሜሪካ መንግስት አሁን የሚከተለውን ፖሊስ ቆም ብሎ እንዲፈትሽ አሳስበዋል።
አቶ ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው ኢትዮጵያውያን አሜሪካ ነጻ ታወጣናለች ብለው እንደማይጠብቁ፣ የራሳቸውን መብት በራሳቸው ለማስከበር እንደሚችሉ ገልጸው፣ አሜሪካ ከአምባገነኑና ዘረኛው የህወሀት መንግስት ጋር የምታደርገውን ግንኙነት እንደገና እንድትፈትሽ ጠይቀዋል።
የውይይቱ ሊቀመንበር የተከበሩ ሚስተር ክሪስ ስሚዝ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በዝርዝር ለተሰብሳቢው አቅርበዋል።

Ethiopia’s opposition vows sustained national protests against the ruling party


June 20, 2013

by Associated Press

ADDIS ABABA, Ethiopia — Ethiopia’s main opposition party says it will launch what it said will be a sustained national campaign against the country’s ruling party.The Unity for Democracy and Justice Party
The announcement Thursday follows a peaceful demonstration on June 2. It was the first public protest since 2005 when security forces killed hundreds of protesters in postelection violence.
The Unity for Democracy and Justice Party said the country is heading toward “absolute dictatorship” under the ruling party, which has been in control since 1991.
The party said it would hold rallies to pressure the government to remove the anti-terrorism law. It will also call for the respect of human and democratic rights and will demand the release of jailed dissidents, journalists and political leaders.
The protests are the first show of disapproval against Prime Minister Hailemariam Desalegn.
Copyright 2013 The Associated Press. All rights reserved. This material may not be published, broadcast, rewritten or redistributed.