Sunday, June 2, 2013

የሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰሳማዊ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ


ሟቹ የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ የዛሬ ስምንት አመት ገደማ ይመስለኛል በራሳቸው አንደበት ጋዜጠኛም ሳያስፈልጋቸው በቴሌቪዢን መስኮት ብቅ ብለው ማንም ሰው ከዛሬ ጀምሮ ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ ስብሰባ ማድረግ የማይችል መሆኑን አስረግጠው በማስፈራሪያ መልክ የተናገሩት፡፡

ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ለረዥም ጊዜ /ላለፉት ስምንት/ ዓመታት ሰላማዊ ሰልፎች በሃገራችን ላይ ሳይደረጉ የህዝባችንም ድምፅ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ትእዛዝ ታፍኖ ቆይትዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ህገመንግስታዊ መብቱን በመጠቀም በዛሬው እለት የጠራው ሰልፍ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ በሰለማዊ መንገድ የተለያዩ መፈክሮችን በማሰማት እንዲሁም  ያለ አግባብ የታሰሩ የፖለቲካ የሀይማኖት እና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ፤  ከቀዬአቸው የተፈናቀሉ ዜጎች በአግባቡ እንዲመለሱ እና አፈናቃዮች ለፍርድ እንዲቀርቡ፤ የኑሮ ውድነቱ አስተማማኝ እልባት እንዲሰጠው እና ሌሎችንም በርካታ ጥያቄዎች ያቀረቡ ሲሆን

Titel: Demo. in Addis Abeba
Schlagwörter: Demo. blaue Partei, Äthiopien
Autor: Y. G.Egziabher ( DW Correspondent Addis Abeba
Datum: 02.06.2013

መንግስት እነኚህን የህዝብ ጥያቄዎች በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ ካልመለሰ ድምፃቸውን በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚያሰሙ የፓርቲው አመራር ገልፀዋል፡፡

ሰልፉ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ጀምሮ እስከ ስምንት ሰዓት ድረስ እጅግ ደማቅ በሆነ መልኩ የተከናወነ ሲሆን ቀበና ከሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት አንስቶ በአራት ኪሎ በፒያሳ እና በቸርቸር ጎዳና ሄዶ መድረሻውን ኩባ አደባባይ ያደረገው ሰልፍ ባልተጠበቀ የህዝብ ቁጥር ብዛት በኢትዮጵያዊ ጨዋነት በሰላም ተጠናቋል፡፡

944521_502719046450298_831415286_n
እንግዲህ ወያኔዎች ከዚህ የሰላማዊ ሰልፍ ብዙ ልትማሩ የሚግባችሁ ይመስለኛል ህዝቡ ምን ያህል ድምፁ ታፍኖ እንደነ በረና እንደተማረረ ብሶቱን ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ መግለጽ እንደሚፈልግ እንዲሁም በሃገራችን ውስጥ የስርአት ለውጥ እንደሚያስፈልገን መገንዘብ ይኖርባችኌል፡፡ በመሆኑም በጠመንጃ አፈሙዝ፤ በዘር በሃይማኖት ከፋፍሎ የአንድ የብሄር የበላይነትን አጉልቶ ሌላውን ብሄር በማሳነስ ሃገር መግዛት አይቻልምና  ሃገራችን የብሄር ብሄረሰቦች እኩልነት የሚከበርባትና ሁሉም ዜጋ በሃገሩ ሳይሸማቀቅ አንገቱን ቀና አድርጎ የሚኖርባት አንዲት ኢትዮጵያ እንድትኖረን እንፈልጋለንና ሃገራችንን ብትለቁልን በሚል የግል አስተያየቴን በመስጠት ሰማያዊ ፓርቲዎችን በርቱ ተበራቱ እኛም ከጎናችሁ ነን ለማለት እወዳለሁ፡፡

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር

ሄለን ንጉሴ  

No comments:

Post a Comment