Sunday, March 30, 2014

የኑሮ ውድነት ሽክም የጫነብን ማን ይሆን?

ግርማ ሠይፉ ማሩ

በሀገራችን የኑሮ ውድነት ከእለት እለት እየከፋ የድሃውን ህዝብ ጉስቁልና እያበዛ እንደሆነ ነጋሪ የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡ በቤተ መንግሰትና አካባቢ የሚኖሩት ይህ ጉዳይ አይመለከታቸውም፡፡ ለዚህ የኑሮ ውድነት አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት የዋጋ ንረት መሆኑን ብዙዎች ይረዳሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ ዛሬ ለፅሁፌ ዋና ማጠንጠኛም የማደርገው የዋጋ ንረት ምንስዔው ምን እንደሆነ በተለይ የመንግሰት ሚና ከዚህ አንፃር ምን እንደሆነ ማስረዳት ነው፡፡

በእኔ አረዳድ በአቅርቦት እጥረት ምክንያት የሚከሰት የዋጋ ንረት አቅርቦቱ ሲሻሻል እንደሚቀንስ በሀገራችን እንደ ሲሚንቶ ያለ ጉልዕ ማስረጃ ማቅረብ አይቻልም፡፡ ከወጣበት ጣራ ወርዶ ትክክለኛም ባይሆን ጥሩ የሚባል ደረጃ ደርሶዋል፡፡ ጊዜው መቼ እንደሆነ ባላስታውሰውም በደርግ መንግሰት ማስታወቂያ ሚኒስትር የሚታተም አንድ መፅሄት “ወደ ላይ ተወርውራ የቀረች ኳስ” ብሎ በሀገራችን ዋጋ ከናረ የማይመለስ ነገር እንደሆነ መጣጥፍ ማቅረቡ ትዝ ይለኛል፡፡ እንደምሳሌ የተጠቀመው ግን አንድ ብር የነበረ ውስኪ ሦሰት ብር ገባ የጠርሙስ ውስኪ ዋጋ ቢቀንስም የመለኪያው አልቀንስ አለ የሚል ነበር፡፡ ይህ ግን የኛ ችግር አይመስለኝም፡፡ የእኛ ችግር ስኳር ቢቀንስ፤ ዱቄት ቢቀንስ፤ ወዘተ የሻይና የኬክ ብሎም የዳቦና ማኪያቶ ዋጋ ይቀንሳል የሚል ተሰፋ የለንም፡፡ ተስፋችን ለምን ጠፋ? ማን አጠፋው? የዚህ ፅሁፍ ማጠንጠኛ ይሆናል፡፡

ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ወደ መቃብር ካልወረደ ወይም አሁን ያሉተ ሰዎች መቃብር ከመውረዳቸው በፊት የዚህችን ሀገር የመሬት ስሪት የሚለውጥ ነገር ለህዝብ ይዘው በመቅረብ ይህን ጉዳይ ከህገ መንግሰት ድንጋጌነት ማውጣት የሚችሉበትን ዕድል ካልተጠቀሙና ተሰፋ ካልሰጡን ተሰፋችንን ያጠፋው ኢህአዴግ መሆኑ ግልፅ ይሆናል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ገዢው ፓርቲም እንደሚያምነው አብዛኛው ሌባ የተሰባሰበው በመሬት ዙሪያ ነው፡፡ መሬት የመንግሰት ነው፡፡ በፍፁም የህዝብ አይደለም፡፡ በፓርቲ ተመርጠው በመንግሰት የተሾሙት ሌቦች እንደፈለጉ የሚያዙበት የሀብታቸው ምንጭ ነው፡፡ ይህ እንዴት ዋጋ ያንራል ማለት ተገቢ ነው፡፡ ዋጋ ማናር ብቻ አይደለም ህይወትም ያስከፍላል፡፡ አለማየሁ አቶምሳን ልብ ይሏል!!

መንግሰት ዜጎችን እያፈናቀለ በሊዝ የሚቸበችበው መሬት አሁን ባለው ሁኔታ እስከ ሰላሳ ሺ ብር በካሬ ሜትር እየተከፈለበት ነው፡፡ በአዲስ አበባችን፡፡ ይህን በሰላሣ ሺ ብር በካሬ ሜትር የሚገዙ ሰዎች የገንዘብ ምንጫቸው ምንድነው? ብለን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ በህጋዊ መንገድ ያገኘውን ገንዘብ በካሬ ለባዶ መሬት (ወርቅ ውስጡ የሌለ ማለት ነው) ይህን ያህል ገንዘብ ከከፈለ፤ ይህን ገንዘብ ለማስመለስ ግልፅ የሆነው ህጋዊ መስመር መሬቱ ላይ ለሚገነባው ቤት ከፍተኛ ዋጋ መጠየቅ ነው፡፡ ይህ ቤት በሽያጭም ይሁን በኪራይ ውድ ይሆናል ስለዚህ እዚህ ቤት ውስጥ የሚሰጥ አገልግሎት ወይም የሚሸጥ ዕቃም ቢያንስ የቤት ኪራዩን መሸፈን ይኖርበታል፡፡ ስለዚህ ዋጋውን መጨመር የግድ ይላል፡፡ ይህ ትንተና የሚሰራው አዲስ በሚሰሩ በሊዝ ለተገዙ ቤቶች ነው የሚል የዋህ አይጠፋም፡፡ ነገር ግን ቤት አከራዮች አዲሶቹ ዋጋ ሲጨምሩ የድሮዎችም ይህንኑ ተከትለው ነው የኪራይ ዋጋ የሚጨምሩት፡፡ ለምሳሌ በአዲስ አበባ ከተማ ሰርቪስ ቤት በሁለት መቶ ብር ተከራይቶ መኖር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት በምንም ዓይነት አንድ ሰርቪስ ቤት ከሺ አምሰት መቶ በታች ማግኘት አይቻልም፡፡ ከገቢያችን አንፃር ማሰተካከያ ቢሰራለት ይህ ዋጋ አሜሪካን አገር እንኳን እንዲህ ዓይነት ዋጋ የለም፡፡

በቅርቡ ከአንደ ጓደኛዬ ጋር የመኖሪያ ቤት ገንብተው የሚሸጡ ሪል ኤስቴቶች አካባቢ ጎራ ብለን ነበር፡፡ እነዘህ ቤት ገንቢዎች ዋጋቸው በፍፁም በሀገር ውስጥ የምንኖር ዜጎችን ያማከለ አይደለም፤ ቤታችንን መንግሰት አይሰራልንም የምንል ዜጎችም ብንኖርም እጃችን ተጠምዝዞ መንግሰትን ደጅ እንድንጠና የሚያደርግ ነው፡፡ ለእነዚህ ቤቶች መወደድ አንዱ ምክንያት የመንግሰት የሊዝ ፖሊስ እንደሆነ መረዳት ብዙ እውቀት የሚጠይቅ አይደለም፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እነዚህ ቤት ገንቢዎች ከቤት ገዢዎች የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰብሰበው ለመንግሰት ገቢ ያደርጋሉ፡፡ ከቤቱ ዋጋ አስራ አምሰት ከመቶውን የያዘው ለመንግሰት የሚከፈለው ታክስ ነው፡፡ ሌላው የታዘብኩት ነገር ደግሞ ለዋጋ ንረቱ ከሊዝና ታክስ በተጨማሪ ሌላ አቁስል ምክንያት መኖሩ ነው፡፡ ከጋደኛዬ ጋር ቤቱን መግዛት እንዳለብን ከምታግባባን የሽያጭ ሰራተኛ ማዶ ሌላ ሽያጭ ሰራተኛ ሁለት ሴቶችን ከፊት ለፊቷ አሰቀምጣ ቤቱን እንዲገዙ በተመሳሳይ ዝርዝር መረጃ ሰጥታ የማግባባት ሰራዋን ሰታጠናቅቅ፤ በዋጋው ውድነት ብስጭት በማለት የተለያየ ሃሳብ መሰንዘር ይጅምራሉ አንዷ ግን እንደ መፍትሔ ሃሣብ አቅረበች “አንገዛም ማለት አለብን!!” አለች፡፡ ልክ ነበረች ገዢ ሲጠፋ ዋጋ መቀነስ የታወቀ የንግድ ሰርዓት ውስጥ የሚወሰድ እርምጃ ነው፡፡ ትክክለኛ የገበያ ህግ በሚሰራበት ሀገር ማለቴ ነው፡፡ ጓደኛዋ ግን በዚህ መፍትሔ አልተስማማችም እንዲህ አለች “ምን መሰለሽ እዚህ ሀገር ብዙ በህገወጥ መንገድ ገንዘብ የሚያገኙ ሰዎች አሉ፤ እነርሱ ደግሞ በህገወጥ መንገድ ያገኙትን ገንዘብ ህጋዊ ማድረጊያ መንገዳቸው አንዱ ቤት መግዛ ነው” ብላ ተጨማሪውን የዋጋ ንረት ምንጭ ነካችው፡፡

ቤት ገንቢዎች ለምን ቤቱን አስወደዱት ብዬ እንደማልከሳቸው ማወቅ አለባቸው ግን በፍፁም ልክ ያልሆነ ነገር በእግረ መንገድ ላስቀምጥ “ይህን ያህል ካሬ ሜትር ቤት በዚይን ያህል ዋጋ” ብለው ማስታወቂያ ሰርተው ለመግዛት የሚሄደው ሰው ግን የሚያገኘው ሰባ ከመቶ አይሆንም፡፡ ምን ነው ? ሲባል ለመኪና ማቆሚያ፤ ለመተላለፊያ፤ ለሊፍት፤ ለጋራ አገልግሎት፤ ወዘተ የሚሉ ቦታዎች ተደምረውበታል ይባላል፡፡ ይህ ምን ያህል ቤት ፈላጊዎችን እንደሚያሳስት ግን ከሻጮቹም የተሰወረ አይደለም፡፡ ማስታወቂያው ሀቅን መሰረት ያድርግ!! ለቤት ገንቢዎች በእግረ መንገድ ያለኝ ምክር ነው፡፡

በዚህች ሀገር የገበያ ህግ እንዳይሰራ እነዚህ ህገወጦች በቀጥታ በጉቦ፣ አገልግሎት በመንፈግ የሚያደርሱብን ጉዳት አልበቃ ብሎዋቸው ሰርቀው ያገኙትን ገንዘብ ህጋዊ ለማድረግ ምስኪን ዜጎች ማረፊያ እንዳይኖረን የሚያደርጉት አስተዋፅኦ እንዲሁም ለዚህም ዋነኛው ተባባሪ በውድ መሬት የሚቸበችበው መንግሰት መሆኑ ታሰቦኝ፤ እንደ አዲሰ እውቅት መብገን ጀመርኩና እናንተም ትበግኑ ዘንድ ነው ይህን ላካፍላችሁ የወደድኩት፡፡ እንግዲ ይህ ገፊ ምክንያት ሆኖን የመሬት ሰሪቱ በዕለት ከዕለት ኑሮዋችን መጥቶ እያሰቃየን ነው ብልን ለለውጥ ካልተነሳን፣ ሌላ ምን በቂ ምክንያት ነው የምንጠብቅው? የሚለው ጥያቄ በእንጥልጥል የሚቆይ ነው፡፡ በህጋዊ መንገድ መሬት የሚፈልጉ ሰዎችም ከህገወጦቹ ጋር ነው ግብ ግብ የሚያያዙት፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያት የቁጥ ቁጥ መሬት አቅርቦት ፖሊስ ነው፡፡ መንግስት የመሬት አቅርቦቱን ሆን ብሎ እያሳጠረ፤ ሌቦቹ እንዲመቻቸው ዕድል እንዲፈጠር እያደረገ ነው፡፡ መሬት በመግቢያዬ እንዳልኳችሁ የመንግሰት ነው እንጂ በፍፁም የህዝብ አይደለም፤ ህዝብማ በመንግሰት እጅ በተያዘ መሬት ሰበብ የሻይና ማኪያቶ ዋጋ ላይ ጭምር ጫና የሚፈጥር ሆኖበታል፡፡ የዚህ መሬትን በመንግስት እጅ የማቆየት ፖሊስ ዋናው ገፊ ምክንያት ፖለቲካም መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡ መሬቱን ይዞ የሊዝ ሂሣብ ሳይከፍል፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ ሳይኖርበት፣ ግብዓቶችን ከቀረጥ ነፃ አሰገብቶ ኮንዶሚኒየም በርካሽ እሰራላሁ እያለ ለዚህም በስልጣን መቆየት አለብን እያለ ይገኛል፡፡ ገዢው ፓርቲ፡፡ ዋናው ፖለቲካዊ ግቡ በስልጣ ገዢውን ፓርቲ ማቆየት ነው፡፡ ይህ ገዢ ፓርቲ በስልጣን ላይ ከቆየ ገዢ መደቦች እየሰረቁ ገንዘብ ያገኛሉ፤ በስርቆት ያገኙትን ገንዘብ ደግሞ በውድም ቢሆን መሬት በመግዛት ዘላቂ ጥቅማቸውን የሚያስጠብቅላቸው በኢኮኖሚ ደንዳና የሆነ ሰርዓት ይገነባል ብለው ያምናሉ፡፡

ይህች ፍልሰፍና ግን የብዙሃኑን ተጠቃሚነት በጎዳ መልኩ ስለሆነ እየተሰራ ያላው በምንም መልኩ ሊሳካ የሚችል አይደለም፡፡ በአሸዋ ላይ የተሰራ ቤት ዓይነት ነው፡፡ አውሎ ንፋስ አይጠብቅም ትንሽ ንፋስ ጠራርጎ ያፈርሰዋል፡፡ ልብ መግዛት ያለብን ይመስለኛል፡፡ ፅሁፌን ከዘጋው በኋላ ዋጋው በአቅርቦት መሻሻል ይቀንሳል ብለን ተሰፋ ያደረግነው ሰኳርም ቢሆን የዋጋ ጭማሪ ያደረገ መሆኑን በሬዲዮሰማው፡፡ ይህ ምንም አያስገርምም፡፡ የሚያስገርመው መግለጫ የሰጡት ኃላፊ ማብራሪያ ነው፡፡ የዋጋ ጭማሪ የሚባል ነገር የለም፡፡ ነገር ግን ለትራንስፖርት ተብሎ ዘጠና አምሰት ሳንቲም በኪሎ ተጨመረ እንጂ፤ የዚህ ምክንያት ደግሞ ቀደም ብሎ ሰኳሩ ከውጭ ስለሚመጣ ከጅቡቲ በቀጥታ ይገባ ስለነበር ነው፡፡ በማለት ቀደም ሲል ስኳር የትራንሰፖርት ወጪ የለበትም የሚል መንፈስ ያለው መግለጫ ሰጡ፡፡

ይህ መግለጫ ህዝቡን እንዴት እንደናቁት ከማሳየት ውጪ አንድም የእውቀትና እውነት መሰረት የለውም፡፡ የዋጋ ጭማሪ አይደለም
የትራንሰፖርት ነው!! ምን የሚሉት ፌዝ ነው፡፡ ዋጋ እንዴት ነው የሚተመነው? ፋብሪካው ይህ የመጀመሪያ ምርቱ ነው? እሰከዛሬ
ትራንስፖርት ማን ነበር የሚሸፍነው? መግለጫውንም ሁሉንም ትተን አሁንም ቢሆን በተጨመረው ዋጋ ስኳሩ የታለ ነው? ያለው
ጭማሪውን ዋጋም ጨምሮ ይገዛል፡፡ የሌለው ድሮ ከሚገዛው መጠን ቀንሶ ይገዛል፡፡ በተለይ የመንግሰት ሰራተኛው በቅርቡ የትራንሰፖርት ዋጋ ተጨመረበት፣ አሁን ደግሞ የስኳር ማጓጓዣ ተጨመረበት፣ ቀጥሎ ስኳርን ተከትሎ ዳቦ ይጨምራል ወዘተ.. ደሞዝ ግን እንዳለች ነው፡፡ መፍትሔው ልጆችን ስኳር ለጤና ጥሩ አይደለም ብሎ ማስተው ነው፡፡ ዳቦ እንዴት ተብሎ ይከለከል ይሆን? ታስታውሱ እንደሆነ የተለያዩ ምክንያቶችን እየደረደረ ዋጋ ይጨምር የነበረው ሙገር ሲምንቶ ፋብሪካ አሁን ዋጋ መቀነሱን ማስታወቂያ ከፍሎ እየነገረን ነው፡፡ ምክንያቱም የመንግሰት ያልሆኑ ተወዳዳሪዎች ስለመጡበት እና እየመጡበት ስለሆነ ነው፡፡ ስኳር ይህን እድል እንዳያገኝ ማዕቀብ ያደረገብን መንግሰት ነው፡፡ ሁሉም ፋብሪካ እኔ እስራለሁ ብሎ፡፡ ቢሰራውም ዋጋ አይቀንስም፡፡ ለምን? የሚታለብ ላም ነው ይለናል፡፡ ስለዚህ ይህን የኑሮ ውድነት የጫነብን እየጫነብንም ያለው፣ በመንግሰት ስም የተቀመጠው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ዘራፊ ቡድን ነው፡፡ 

ቸር ይግጠመን፡፡
ኢትዮሚድያ - Ethiomedia.com
March 29, 2014

Saturday, March 29, 2014

የወያኔን ከፋፋይ አገዛዝ እናምክን (ግንቦት 7)


March 29, 2014

Ginbot 7 weekly editorial
የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰብ ሊከበርላቸውና ሊያሳድጋቸው የሚገቡ የተለያዩ የባህልና የታሪክ ቅርሶች ያሏቸውን ያህል በብዙ መንገድ የሚያይዝ የጋራ ታሪክ ቅርስና ዝምድና አላቸው። ልዩነቶቹ ራሳቸው ተጠቃቃሚ ለሆነ የእርስበርስ ግንኙነታቸው ጠቃሚ እንጂ ከአንድ ሀገር ማህበረሰብነታቸውና ከጋራ ህልማቸው ጋር የሚጋጩ የጠብና የግጭት መንስኤዎች አይደሉም። ከጠብና ግጭት ማንኛውም ብሄር ብሄረሰብ ተጠቃሚ አይደለም። ከጠብና ግጭት ጥቅም ይገኛል ብለው የሚያስቡ “ግርግር ለሌባ ይመቻል” የሚለውን የወሮ በላ ፍልስፍና የሚከተሉ የቀን ጅቦች እንጂ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች አይደሉም። በወያኔ የግዛት ዘመን የደረሱትን ግጭቶች መፈናቅሎችና የተፈጠሩትን የእርስበርስ ጥርጣሬዎችን ልብ ብሎ ለተመለከተ ሁሉም በአገዛዙ እና በሎሌ የበታች ሹማምንቱ የተፈጠሩ እንጂ አንድም ጊዜ እንኳን ከህዝብ የመነጩ አይደሉም።

የወያኔ ጉጅሌ በአገዛዝ ዘመኑ ሁሉ ብሄር ብሄረሰቦችን ከሚያይዟቸው የጋራ ማህበራዊ ቅርሶችና ህልሞች ይልቅ ካለመታከት ልዩነቶቻችን ላይ ያተኮረ ፖለቲካ እያካሄደ እንዳለ ግልጽ ነው። ከዚህ አልፎም አዳዲስ የእርስበርስ ግጭቶችን እና ጠቦች እንዲፈጠሩ ተግቶ የሚሰራ ከፋፋይ ቡድን ነው። እርስበርሱ መጠራጠርና መፈራራት እንዲሰፍን ልዩ ልዩ ስልቶችን ይቀይሳል። ከአንዱ ብሄረሰብ ተንኳሽ አዘጋጅቶ ሌላው ብሄረሰብ ላይ አደጋ እንዲደርስ ከዚያም ተጠቃሁ የሚለው አጸፋ እንዲመልስ ያደርጋል። የአንዱን ብሄረሰብ መንደርና ንeበረት በእሳት ለኩሶ በሌላው ብሄረሰብ እንዲመካኝ ያድርጋል። አንዱ በአንዱ ላይ እንዲያማርር ከንፈሩን እንዲነክስ ማድረግ ለወያኔ ጉጅሌዎችና ለሎሌዎቻቸው እንደፖለቲካ ጥበብ ከታየ ሁለት አስርት አመታት አልፈዋል። በየትኛውም የሀገራችን አካባቢዎች የተቀሰቀሱ የርስበርስ ጥርጣሬዎችና ግጭቶችን ያሸተተ ሁሉ ወያኔ፣ ወያኔ እንደሚገሙ ያረጋገጠው ጉዳይ ነው።
ወያኔዎች የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦች ከፋፍለውና ከቻሉም አጋጭተው ካልሆነ በስተቀር የዝርፊየ ኢኮኖሚያቸውን መቀጠል እንደማይችሉ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች የጋራ ጥቅማቸውንና ህልማቸውን ይዘው የተነሱ እለት ወያኔ ያከተመለት መሆኑን ያውቃል። ለዚህም ነው በየክልሉ እና ዞኑ በፍጹም ከሆዳቸውና ጥቅማቸው በላይ ማሰብ የማይችሉ ግለሰቦችን ከየብሄረሰቡ እየመረጠ የሚሾምልን። ወያኔ ነጻ የህዝብ ምርጫ የሚፈራው ለዚህ ማረጋገጫ ነው፡፡
የወያኔ ጉጅሌዎች ከጊዚያዊ ጥቅም በዘለለ ማሰብ ስለተሳናቸው እንጂ ይህ አካሄዳቸው ለራሳቸውም ለዘለቄታው የማይጠቅም መሆኑን ዘንግተውታል። በልዩነታችን ላይ መጫወት ማለት በእሳት እንደ መጫወት የማይመስላቸው ለዚህም ነው። ይህ የተጀመረው እሳት ራሳቸውንም አይምርም።
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ መላው የኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች የጋራ ግብና የተሻለው የነገ ነጻነት ተስፋቸው የሚረጋገጠው በጋራና እጅ ለእጅ ተያይዘው በሚያደርጉት ትግል ብቻ ነው ብሎ ያምናል። ለዚህ የወያኔ መሰሪ የከፋፍለህና አጋጭተህ ግዛ ተንኮል ራሳችንን እንዳናመቻች የገዛ መከራችንን ማራዘሚያ እድል ለዘራፊ ገዥዎቻችን እንዳንሰጥና ለጋራ ህልማችን እንድንቆም ጥሪውን ያቀርባል።
የወያኔ ጉጅሌ ሆን ብሎ በቀጥታና በተዘዋዋሪ የኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች እንዲጋጩ፣ እርስበርስ በጥርጣሬ እንዲተያዩና እንዲፈራሩ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ድርጊቱ በእሳት መጫወት መሆኑን አውቆ ከዚህ እኩይ ተግባር እንዲታቀብ ግንቦት 7 እያሳሰበ በማንኛውም ሁኔታ በማህበረሰቦች መካከል ለሚደርስ ግጭትና ጉዳት ሙሉ ሀላፊነቱ የወያኔና የወያኔ ብቻ መሆኑን አጥብቆ ያስገነዝባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Thursday, March 27, 2014

“ለውጡ እንደቀረበ ጥርጥር የለኝም” ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር


March 27, 2014
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሁለት ወር በፊት ወደ አሜሪካና የአውሮፓ አገራት ለስራ ጉብኝት ሄደው ነበር፡፡ አሁንም ወደ አሜሪካ ጉዞ ሊያደርጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ፡፡ የአሁኑ ጉዞ አላማ ምንድን ነው?
Eng. Yilkal Getnet Semayawi party chairman with Negere Ethiopia newspaper
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር
ኢንጅነር ይልቃል፡- መጀመሪያ ያደረኩት ጉዞ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም፣ የሰራናቸውን እንዲሁም ወደፊት ልንሰራቸው ያሰብናቸውን ስራዎች፤ ሰማያዊ እንደ አዲስ ኃይል ሲመጣ የቆመላቸው ሀሳቦችና እምነቶች ምን እንደሆኑ ለማስተዋወቅ ታስቦ የተደረገ ነበር፡፡ የአሁኑ ግን ከበፊቱ የተለየና ለሰማያዊ ሊቀመንበር በሚል በቀጥታ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት የተደረገ ግብዣ ነው፡ ፡ የአሁኑ ወጣት የአፍሪካ መሪና ወደፊትም ለአገራቸው መሪ ሊሆኑ የሚችሉ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ጥሩ ስራ የሰሩ፣ በውድድር ከተመረጡ በኋላ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት በሚደረግ ምርጫ መመዘኛዎቹን ለሚያሟሉ ሰዎች የሚሰጥ እድል ነው፡፡ በመመዘኛዎቹ መሰረት በማሸነፌ የአሜሪካ መንግስት ሙሉውን ወጭ ሸፍኖ ለሶስት ሳምንት በአሜሪካ የመንግስት አወቃቀርና ዴሞክራሲን ጨምሮ በተግባር የሚሰጡ ስልጠናዎችን የማግኘትና፣ የአሜሪካ መንግስት ባለስልጣናትም ባሉበት ከተለያዩ ተቋማት ጋርም ለመገናኘት እድል ይኖረኛል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መሪዎች ጋር ተወዳድረው ነው ያሸነፉት ማለት ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አዎ! ግን ሌሎች ያሸነፉ ተጨማሪ ሰዎች ይኑሩ አይኑሩ አላውቅም፡፡ ይህ የፕሬዝዳንቱም ‹ኢኒሸቲቭ› ይመስለኛል፡፡ ለእኔ ግን የተሰጠኝ አዲስ ትውልድ አመራሮች፣ ወደፊትም በአገራቸው መሪ መሆን የሚችሉ፣ ስትራቴጅካሊ የሚያስቡ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይም ሆነው መልካም ስራ ለሰሩ ሰዎች የሚሰጥ ልዩ የጉብኝት እድል ነው፡፡ በአጠቃላይ ውድድርም ተደርጎ የሚወሰድ ነው ማለት ይቻላል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ይህንን እድል ሲሰጥ እርስዎ እንደ መሪም ሆነ ሰማያዊ እንደ ፓርቲ ያሸነፋችሁበትን ዋና ዋና መመዘኛዎች ነግረዋችኋል?
ኢንጅነር ይልቃል፡- ሲመርጡኝ ዝርዝር መረጃዎችን ወስደዋል፡ ፡ መሰረታዊ የሚባሉትን ለምሳሌ ያህል የፖለቲካ ቆይታዬ፣ የትምህርት ዝግጅቴን፣ በፖለቲካው ውስጥ የነበረኝን ተሳትፎ የመሳሰሉትን መረጃዎች ለእጩነት በቀረብኩበት ወቅት ከእኔ ወስደዋል፡፡ ከዛ በኋላ ያስመረጠኝን ዝርዝር መስፈርት አላውቅም፡፡ ነገር ግን ወጣት (እስከ 45 አመት ባለው ውስጥ)፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ መልካም ስራ የሰራ፣ ወደፊትም የአገሩ መሪ ሊሆን የሚችል የሚሉት ዋና ዋና መመዘኛዎች እንደሆኑ አውቃለሁ፡ ፡ ይህም በተለይ ከሰማያዊ አንጻር ከሁለት ነገሮች አኳያ እንድናየው ያደርጋል፡፡ አንደኛው በምስራቅ አፍሪካ ያለውን ፖለቲካና እስካሁን ጠቅልሎ የያዘው ኢህአዴግ ነበር፡፡ ሌላ አማራጭ እንደሌለ አድርጎ ነበር የሚያየው፡፡ ሆኖም እንደዚህ አይነት እድል እንደ አሜሪካ ባለ ትልቅ መንግስት የተቃዋሚ መሪ የተለየ ስራ ሰርቷል ተብሎ ሲጋበዝ ሰማያዊ ፓርቲ አዲሱንና ወደ ፖለቲካ ያልመጣውን ትውልድ ወደ ፖለቲካው ለማምጣት በሚያደርገው ጥረት እንደ አንድ ማበረታቻ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ይህ በሌሎች መስኮች ከምናደርጋቸው የዲፕሎማሲ ስራዎች በተጨማሪ ለሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች በተለየ ይህኛው ግብዣ ሲደረግለት ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
ከአሁን በፊት ለሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በአሜሪካ ኤምባሲ ውስጥ የ35 አገራት ኤምባሲዎች የ‹ኢትዮጵያ ፓርትነርስ ግሩፕ› የሚባለው ሲደረግ በአመታዊ ስብሰባቸው ላይ ዋና ተናጋሪ ሆኜ ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካና ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ዋና የትግል እንቅስቃሴና የወደፊት አላማችን እንዳስረዳ የተለየ እድል ተሰጥቶኛል፡፡ ይህም ለፓርቲው ሌት ተቀን ለሚሰሩ ወጣቶች፣ እንዲሁም ሁል ጊዜም ቢሆን ወጣቱ ተከታይና ጀሌ እግረኛ ከመሆን አልፎ ራሱ ኃላፊነት የሚወስድ፣ መምራትና የራሱን መሪዎች ማውጣት የሚችል ትውልድ መምጣቱን የሚያሳይ መልካም ጅምር ነው፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ከ9/11 እንዲሁም ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ሶማሊያ ውስጥ ባለው ጥቅም ኢህአዴግ ላይ እስከመጨረሻ ግፊት ማድረግ አልቻለም ነበር፡፡ አሁን ለእርስዎና ለፓርቲዎ ይህን እድል ሲሰጥ ለኢህአዴግ የሚያስተላልፈው መልዕክት ምንድን ነው? የተቃውሞ ጎራውም ቢሆን እስካሁን የሚመራው በ1960ዎቹ ፖለቲከኞች ነው፡፡ አሁን የአሜሪካ መንግስት ይህን እድል ለእርስዎ እንደ መሪና ለሰማያዊ እንደ ወጣት ፓርቲ ሲሰጥ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚኖረው አንድምታ ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እንግዲህ ይህን ጉዳይ ህዝቡም ሆነ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ማህበረሰቡ እየተረዳው የመጣ ይመስለኛል፡፡ ባለፈው አርባ አመት በገዥውም ሆነ በተቃዋሚው ያለው በአንድ አይነት እድሜና የግራ ርዕዮት የሚሽከረከር ነበር፡፡ ይህም የኢትዮጵያን ፖለቲካም ሆነ ኢትዮጵያን በሁሉም መመዘኛዎች ወደ ፊት ሊያራምድ አልቻለም፡፡ እንዲያውም ጥላቻ፣ ቂምና ቆርሾ፣ የእስር በእርስ መጠላፍና የዜሮ ድምር ፖለቲካ ሆኖ ቆይቷል፡ ፡ ያ ትውልድ ያላመጣውን ውጤትም ወጣቱ ያመጣዋል የሚል ነው፡ ፡ ኢትዮጵያ የወጣት አገር ነች፡፡ 70 ከመቶ የሚሆነው ከ35 አመት በታች ነው፡፡ ይህ የህብረተሰብ ክፍል በውክልና ደረጃም ሆነ አዲስ አስተሳሰብና ከበድ ያለ ነገር ይፈልጋል፣ ከዓለም ከተለያየ አቅጣጫ መረጃ ያገኛል፣ በአስተዳደጉም አንጻራዊ ነጻነት አለው፣ በአመለካከትም ቢሆን ይህ የህብረተሰብ ክፍል ወደ ፊት እየመጣ ነው፡፡ ከዚህም አንጻር በታክቲክም ሆነ በአመለካከት ይህን የህብረተሰብ ክፍል መደገፍ የሚያዋጣና አይቀሬነቱን የሚያሳይ ይመስለኛል፡፡
ዋናው የኢህአዴግ የፖሊሲ መሰረት ማታለል ነው፡፡ ‹‹እኔ ከሌለሁ ኢትዮጵያ ትበታተናለች፡፡›› በሚል የምስራቅ አፍሪካንም ሆነ የሶማሊያን የሽብር ሁኔታ እንደ ማታለያ እየተጠቀመ፤ እነሱ የስጋት ፖለቲካ ውስጥ መግባታቸውን ስለሚያውቅ እሳት የማጥፋት ስራ ነበር የሚሰራው፡ ፡ ይህ ግን መሰረታዊ መፍትሄ የሚያመጣ ሳይሆን ነገሮችን እያዳፈነ፣ ችግሩን እያባባሰ በመሆኑ እንዲሁም የጠቅላይነት ፖለቲካን ለቀጠናውም ሆነ ለኢትዮጵያ እየጠቀመ አለመሆኑ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ኃይሎች ተረድተውታል፡፡ አማራጭ የፖለቲካ ኃይልና መሰረታዊ የሆኑ የዴሞክራሲ መመዘኛዎችን ማምጣት፣ መሰረታዊ የሆኑ የዜጎች ልማትና ዴሞክራሲ ማፋጠን፣ በአቻነት የተመሰረተ ግንኙነትን ካልሆነ በስተቀር በጉልበትና በጠብመንጃ የሚደረገው አገዛዝ እንደማያዋጣ የተረዱበት ጊዜ ነው፡፡ አሜሪካኖች አባቶቻቸው የሞቱበት ነገር (the ideals of ower founding fa­thers) የሚሉት የሰውን ልጅ መብትና የሰብአዊ መብት ማክበር ለሁሉም አገራት መድሃኒት መሆኑን ራሳቸው አፍጋኒስታንና ኢራቅ ውስጥ በነበሩበት ወቅት አይተውታል፡፡ በየመን፣ በምስራቅ አፍሪካዋ ሶማሊያም ቢሆን ተመሳሳይ የእሳት ማጥፋት ፖለቲካ ለውጥ እንዳላመጣ ተገንዝበውታል፡፡ በየ ደረጃው በህዝብ ተሳትፎ የሚያድግ ዴሞክራሲና በዜጎችም ይሁን በአገራት መካከል በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ግንኙነት መምጣት ካልቻለ አፋኝነት እንዳልጠቀመ የተረዱበት ጊዜም ይመስለኛል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- እስካሁን ድረስ ዲያስፖራውም ሆነ አገር ውስጥ ያው የተቃውሞ ኃይል ድምጹን ለማሰማት ሲሞክርም የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ትኩረት አናሳ እንደነበር ይታወቃል፡፡ እናንተ ይህንን አጋጣሚ ስታገኙ ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በስርዓቱ ላይ ትኩረት እንዲሰጥ በአጽንኦት የምታስረዱት ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አንደኛ ከመንግስት ጋር መስራት በሚሉት መርህ ላይ ኢህአዴግ ስልጣን ስላለው ብቻ በአጭር ጊዜ የጮሌነት ግንኙነት፣ ከዛም በኋላ ለአሸነፈውና የኃይል ሚዛኑ ካደላው ጋር ግንኙነት የማድረግ ዋናው የዘመኑ መገለጫ፣ ስግብግብነትን መሰረት ያደረገ የካፒታሊዝም መርህ ስለሆነ በየትኛውም መንገድ ተሂዶ የአገርን ጥቅም ማስጠበቅ የሚባለው እንደማይጠቅም ማስረዳት እንፈልጋለን፡፡ መንግስት ቢያልፍም በህዝብ ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍን እያዩ እንዳላዩ ማለፍ ለዘላቂ የአገራቸው ጥቅም እንደማይበጅ፣ ሁል ጊዜም ቢሆን ግንኙነት መመስረት ካለበት ከአገሪቱና ከአገሪቱ ህዝብ ጋር እንደሆነ፣ ግንኙነቱ ታሪካዊና የህዝብን መሰረታዊ መብቶች ጠብቆ የሚደረግ እንጅ ከአንድ ቡድን ጋር የሚደረግ ግንኙነት ኢትዮጵያን ለመሰለ ታሪክና ክብሩን ለሚወድ ህዝብ ውሎ አድሮ የማይጠቅም መሆኑን፣ በአጠቃላይም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ፣ መሰረታዊ መብቶችና ሀሳቦች በሚከበርባቸው መልኩ የሚያራምድ አይነት አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ ግንኙነት እንዲያደርጉ ነው በዋነኛነት ማሳሰብ የምንፈልገው፡ ፡ ከአንድ ቡድን ጋር የሚደረግ የአጭር ጊዜ ግንኙነት ራሳቸውንም እንደሚጎዳቸው፣ በቀጠናው ይገኛል የሚባለውን መረጋጋትና ሰላምም ሊያመጣ እንደማይችል እንዲረዱት እንፈልጋለን፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ከዲያስፖራው ጋር በመገናኘት የምትሰሩት ሌላ ድርጅታዊ ስራስ ይኖር ይሆን?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ባደረገልኝ ግብዣ ላይ ለሶስት ሳምንት እቆያለሁ፡፡ የትኬትና ተመሳሳይ ጉዳዮችን ከሚሰሩት የአሜሪካ ሰዎች ጋር ስንነጋገር ከዚህ ውጭ አንድ ወር ያህል አሜሪካን አገር እንደምቆይ ገልጨላቸዋለሁ፡፡ በዚህም አጋጣሚ ባለፈው በአየር ንብረትና በድካም ምክንያት ያላዳረስኳቸው ቦታዎች ላይ ስብሰባ የማካሄድ ሀሳብ አለኝ፡፡ ምን አልባትም ወደ ለንደንና ካናዳ ልሄድ የምችልበት አጋጣሚ ይኖራል፡፡ ይህ እንግዲህ ከዚህ ካለው ስራ፣ ከጉዞ ሰነዶችና ከጊዜም ጋር ተደማምሮ በሂደት የምናየው ይሆናል፡፡ በድርጅታዊ ጉዳይ ላይ ለመስራት እቅዱም ሀሳቡም አለን፡፡ እዚያው ያሉት ደጋፊዎቻችንም በጉዳዩ ላይ እየሰሩበት ይገኛሉ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ወደ ሌላ ርዕሰ-ጉዳይ ልውሰድዎትና፣ ባለፈው እሁድ ሴቶች በተሳተፉበት የታላቁ የጎዳና ላይ ሩጫ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስታችኋል በሚል ከተያዙ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ‹‹መረጃን ለማሰባሰብ›› በሚል ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ይህን እንዴት ያዩታል?
ኢንጅነር ይልቃል፡- በዚህ ጉዳይ ከማዘንና ከማፈር ውጭ የምለው ነገር አይኖርም፡፡ ኢህአዴግ በዴሞክራሲ እየማለ፤ ለዜጎች እኩልነት፣ ለጎሳና ሀይማኖት እኩልነት፣ ለሴቶች እኩልነት ጠብመንጃ አንስተን በመዋጋት የልጅነት እድሜያችንን በበርሃ አጥፍተናል እያሉ፤ 23 አመት ቆይተው ግን ሴቶች ለነጻነት በተሰለፉበት ቀን ስለ አገራቸው አንድነትና ስለ መሰረታዊ መብቶች የጠየቁ ሰዎችን እስር ቤት ሲያጉሩ ምን ያህል የማይማርና ወደ ኋላ እየተንደረደረ የሚገኝ፣ የራሱን ሞት እየጠበቀ ያለ መንግስት እንደሆነ ለመረዳት ችያለሁ፡፡ ከዚህ ውጭ ምንም አዲስ ነገር ባላይበትም ትግሉ ውስጥ መግባታችን ምን ያህል ትክክል እንደሆነ ግን አረጋግጦልኛል፡፡ እሱ የማይፈልገው ሀሳብ ከሆነ ለምንም ነገር የማይመለስና ሴት፣ ህጻን፣ ህጋዊም ሆነ አልሆነ ለእሱ ምኑ እንዳልሆነ፣ በስልጣኑ ላይ ለመጣ ወደኋላ የማይመለስ መንግስት መሆኑን ተረድተንበታል፡፡ ይህም ዘላለም ለመጨቆን የተዘጋጀ መንግስት በመሆኑ ወደ ትግል መግባታችን ትክክል መሆኑ እንድንረዳ አድርጎናል፡፡ ይህም ለትግሌ መሰረት ስንቅ ከመሆኑ በተጨማሪ በኢህአዴግ ላይ አዝኛለሁ፣ አፍሬያለሁ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ባለፉት ሁለት አመታት አረቦቹ አብዮት አካሂደዋል፡፡ ዩክሬን ውስጥ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለውጥ ነበር፡፡ ለባለፈው አንድ አመት ተኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥም የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ በአንጻራዊነት እየተጠናከረ ነው፡፡ አመጽ እየተለመደ ከመምጣቱ፣ የኑሮ ውድነትና ጭቆናው ከመባባሱ ጋር ተዳምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣይነት የሚመጣውን ለውጥ እንዴት ነው የሚያዩት?
ኢንጅነር ይልቃል፡- መቼም እኔ የምናገረው ምኞቴንና የምሰራበትን ነገርም ነው፡፡ ከዛ ውጭ ያለውን ነገር ብንወደውም ባንወደውም ራሱ መምጣቱ ስለማይቀር፣ ስለ እሱ መናገር ለእኛ አወንታዊ አስተሳሰብ ስለማይበጅም ሆነ እርግማት ተናጋሪ ስለሚያሰኝ ማድረግ የሚቻለውን በጎ ነገር እያደረግን ብንሄድ የተሻለ ነው የሚሆነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ አይነት በዓለም የመጨረሻ ድሃ ለሆነ፣ ብዙ የጎሳና የእምነት መቃቃር በተፈጠረበት አገር፣ በሩቅም በቅርብም የኢትዮጵያን መረጋጋት የማይወዱ አካላት ባሉት ቀጠና ላይ ሆነን፣ እርስ በራሳችንም በተለያዩ የታሪክ ግጭቶች ውስጥ እያለን እንዲህ አይነቱ ለውጥ ባይኖር ደስ ይለናል፡ ፡ ነገር ግን አልፈለግነውም ማለት አይከሰትም ማለት አይደለም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲህ አይነት ጉዳይ እንዳይከሰት የተጠና፣ አስቀድሞ በድርጅቱ የተመራ፣ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ የሚካሄድ የስልጣን ሽግግር እንዲኖር ሌት ተቀን ይሰራል፡ ፡ ሆኖም ገዥው ፓርቲ በጠቅላይነትና ባታላይነት እቀጥላለሁ ካለ ህዝቡ ውስጥ መሰላቸት በግልጽ ይስተዋላል፣ ችግሮች ከዕለት ዕለት እየተደራረቡ ነው፣ ህዝብ አገሩ ውስጥም ሆነ በአካባቢው የለውጥ ምሳሌዎችን እያየ ነው፣ ችግሩ መሸከም ከሚችለው በላይ ሆኖበታል፡፡
በመሆኑም እነዚህ ለለውጥ መሰረት የሆኑ ነባራዊ ሁኔታዎች እየመጡ ስለመሆኑ የፖለቲካ ተንታኝ መሆን አያስፈልግም፡፡ በዚህ ሁኔታ አገዛዙ ውስጥ ያሉት ሰዎች የሚፈተኑት ከመግዛትና ከመጨቆን አስተሳሰባቸው ወጥተው ወደ እውነታው ቀርበው ለለውጥ ይዘጋጃሉ ወይንስ በተለመደው ግትርነት ይቀጥላሉ? በሚለው ነው፡፡ በሌላ በኩል እኛም ደግሞ አማራጭ ሆነን፣ እነሱን ሳናስደነብር፣ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲፈጠር መቻቻልና ይቅር ባይነቱ ኖሮን አገራችንን ማዳን የምንችልበት ሆደ ሰፊነትና አስተዋይነት ፖለቲካ በሁለታችንም በኩል ይጠበቃል፡፡ ግን ይህን ታሪካዊ ጉዳይ ከሁለታችን አንዳችን ከሳትነው ሂደት በተፈጥሮ የሚያመጣው ጉዳይ አለ፡፡ ሁሌም ታሪክም፣ ስልጣኔም፣ የሰው ልጅም ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ይለወጣል፡፡ ልቡን የደፈነ ሰው ካልሆነ በስተቀር ለውጥ አይቀሬ ስለመሆኑ የሚጠራጠር ያለ አይመስለኝም፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ምን ያህል ንብረት ይወድማል፣ ምን ያህል የሰው ነፍስ ይጠፋል፣ በሂደቱ ምን ያህል የተጠና እና ለአገራችን የሚጠቅም ለውጥስ ይመጣል የሚለው ነው እንጂ የሚያስጨንቀኝ ለውጡ እንደቀረበ ጥርጥር የለኝም፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ይህ ለውጥ ቢከሰት ለውጡን በሚገባው መልኩ ለማስተናገድና ለመምራት ትክሻ ያለው አካልስ አለ ብለው ያስባሉ?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኛ ሰማያዊ ይህን ለውጥ መሸከም የሚችል ትክሻ አለው ብለን ነው የምናምነው፡፡ በእኛ አገር ይህንን አይነት ነገር ደፍረን ስንናገር በሁሉም ወገኖች ዘንድ አይወደድልንም፡ ፡ ለምን እንደማይወደድም ይገባናል፡፡ ባይወዱትም መናገር አለብን፡፡ ከማይወደድበት ምክንያት የመጀመሪያው በጭቆና መንፈሳችን መላሸቁ ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹ይቻላል!›› ማለት እንደ ቅዠትና እብደት ይቆጠራል፡፡ ይህም ‹‹ይቻላል›› የሚለውን ከመጥላት፣ ከጭቆናው መብዛት፣ በተደጋጋሚ ከመክሸፍ የመጣ የአቅመ ቢስነት ችግር እንጅ የእኛ ችግር አይደለም፡፡ እነዚህ በጭቆና አስተሳሰብ ስር የወደቁት የእኛን አመለካከት እንዲይዙ ጥረት በማድረግ በተደጋጋሚ ስለ ጉዳዩ እንናገራለን፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ድርጅት ሆነን ስንቋቋም እኛ የተሻለ አማራጭ አለን፣ አገርና ህዝብን ወደተሻለ ደረጃ እናደርሳለን ብለን ነው፡፡ ስለሆነም ስለ ራሳችን ስለ ድርጅታችን በሙሉ ልብ ‹‹እንችላለን!›› ስንል፣ ሌሎች ድርጅቶች ቅር ይላቸዋል፡፡ ይህ ከፖለቲካ እውቀት ማነስ የመጣ ነው፡፡ እኛ እንደ ድርጅት ተቋቁመን ‹‹እንችላለን!›› ካላልንና ህዝብና አገርን ወደ ተሻለ ደረጃ እንደምናደርስ መናገር ካልቻልን ህዝቡ እንዴት ሊከተለን ይችላል? ለምንስ ጊዜያችንን እናጠፋለን?
ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው አንድ አመት ተኩል የፖለቲካ ነገር በቀላሉ የማይመዘን ሆኖ እንጅ መብት መጠየቅን፣ መነቃቃትን፣ ከአይቻልም ባይነት ይቻላል ባይነትን፣ አዲሱ ትውልድ የራሱን እጣ ፈንታ ለመወሰን በድርጅት የመታቀፍንና የመታገልን በአዲስ መልክ ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ይህም ለረዥም ጊዜ በወደቀና በከሸፈ የፖለቲካ አመለካከት ውስጥ በጣም ረዥም ጊዜን የሚጠይቅ ስራ ነው፡ ፡ ይህም በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን በርካታ የሰማያዊ ወጣቶች የራሳቸውን የህይወት አማራጭ ትተው በዚህ ጉዳይ ላይ ጥርሳቸውን ነክሰው፣ በግልጽ የፖለቲካ አመለካከት ሌት ተቀን ከአገዛዙ ጋር እየተጋፈጡ፣ እየታሰሩ፣ ዋጋ እየከፈሉ የመጣ ነገር ነው፡፡ በዚህ ሂደታችን ውስጥ ወጣቶች ወደ ፖለቲካው እንዲመጡ ማነቃቃት ችለናል፡ ፡ ከትልልቅ የአደባባይ ምሁራን፣ ከዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮች፣ ከውጭም ከአገር ውስጥም ክብርና ይሁንታን አግኝተናል፡፡
ከክርስትናም ሆነ እስልምና ሀይማኖት መሪዎችና አማኞች አካባቢም መከበር ችለናል፡፡ ከዓለም አቀፍ ማህበረሰቡም ቢሆን እንደሚታየው ወጣትና ወደፊት አገራቸውን መምራት የሚችሉ ተብለን መወደስና መሸለም ችለናል፡፡ የዓለም አቀፉም ሆነ የአገር ውስጥ ሚዲያው እንደ አንድ የፖለቲካ ኃይል አይቶናል፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ለስልጣን መሰረት የሆኑት ነገሮች እነዚህ ናቸው፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ወጣቶች፣ የአደባባይ ምሁራን፣ ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡና ሚዲያው ሰማያዊን እንደ አንድ የፖለቲካ ኃይል ማየት ችሏል፡፡ በእነዚህ ኃይሎች ተቀባይነት ካገኘ አገሪቱን ለመምራት የሚያቅተው ምንም ነገር አይኖርም ማለት ነው፡፡ የራሱ አላማ፣ የራሱ ፕሮግራም አለው፡፡ ይህን ለማስፈጸም የሚችል ቆራጥ አመራር አለው፡፡ በእርግጥ ኢትዮጵያ ትልቅ አገር ብትሆንም ሰማያዊ ለውጥን በአግባቡ ለመረከብና ለመምራት የሚያስችል አቅም እንዳለው መግለጽ እፈልጋለሁ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ዲያስፖራው የገንዘብም፣ የመረጃና የእውቀትም አቅም እንዳለው ቢታመንም ከ1997 በኋላ ግን ለአገሪቱ ፖለቲካ አሉታዊ ጎን እንደነበረው በስፋት እየተጠቀሰ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት እናንተ ከዲያስፖራው ተቀባይነት እያገኛችሁ ነውና መልካም ጎኑንና ፖለቲካውን ላይ አለው የሚባለውን አሉታዊ ተጽዕኖ እንዴት ነው የምታስታርቁት?
ኢንጅነር ይልቃል፡- ሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ አንድን አካል በቅራኔ መድቦ መታገል የተለመደ ባህል አይደለም፡፡ ለምሳሌ ሰማያዊ ፓርቲ ወጣቱ ላይ ያተኩራል ሲባል፤ በየትኛውም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ግን የሽማግሌዎችን፣ የአደባባይ ምሁራንንና የትልልቅ ሰዎችን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የሰማያዊ አመራር አገር ውስጥ ቢሆንም የራሳቸው የፖለቲካ ፋይዳ፣ ካፒታል፣ አንጻራዊ ነጻነት ያላቸው፣ የአገራቸውን ነጻነት በቀናነት የሚመኙ፣ በመረጃው በኩል ቅርብ በመሆናቸው በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ እገዛ ከሚያደርጉት በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ትልቅ ተቀባይነት አለው፡፡ ይህን ጉዳይ ሚዛናዊ በመሆነ መልኩ የመምራት ችግር ካልሆነ በስተቀር በውጭ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ከሚገኙት የተለዩ አይደሉም፡፡ አገር ውስጥ እንዳለው ሁሉ ውጭ ያለውም የአገሩ ሁኔታ ያሳስበዋል፡፡ የአገር ውስጡ የራሱ ሚና ይኖረዋል፡ ፡ በውጭ የሚኖረው ደግሞ የራሱ የሆነ ሚና ይኖረዋል፡፡
እነዚህን ሁለት ጉዳዮች አገር ውስጥ ያለው በተገቢው መንገድ ማስተባበር ይኖርበታል፡፡ አገር ውስጥም ውጭም ያለውን አጣጥሞ የማስኬድ ስራ ነው የምንሰራው፡፡ መሪነት ሲባል እኮ የሰዎችን አቅም ለግብ መጠቀም ነው፡፡ የትኛውም የማህበረሰብ ክፍል፤ አርሶ አደር፣ ነጋዴ፣ ውጭ ያለ፣ አገር ውስጥ የሚገኝ፣ የተማረም ይሁን ያልተማረ፣ ሁሉ ጥቅምና ፍላጎት አጣጥሞ ወደፊት መምራት ነው ዋናው ስራችን፡፡ ዲያስፖራውንም እንደ አፈንጋጭ፣ እንደ አጥፊና ለኢትዮጵያ ችግር ተጠያቂ አድርጎ ማየት በሰማያዊ ፓርቲ የተለመደ አይደለም፡፡
ባለፈው ጉብኝት ባደረኩበት ወቅት የዲያስፖራውን ድክመትና ስህተቶች ያልኳቸውን በአደባባይ ተናግሬያለሁ፡፡ እነሱም ከጊዜ ብዛትና ከመውደቅ መነሳት ብዙ የተማሩት ነገር አንዳለ ተረድቻለሁ፡፡ ይህን ጉዳይ አጣጥሞ የሚመራ አስተዋይ፣ ብልህና ሆደ ሰፊ መሪ ያስፈልጋል፡፡ ይህ እኛ እንደ ድርጅት አዲስ ብንሆንም በፖለቲካው መውደቅ መነሳት ከ1997 ዓ.ም ጀምረን የነበርን ሰዎች በመሆናችን የተፈጠሩትን ነገሮች በቅርበት እናውቃቸዋለን፡፡ ባገኘነው በቂ ልምድም ጉዳዩን በጥበብ መያዝ ችለናል፡፡ ወደፊትም በጥሩ ሁኔታ እንሄዳለን የሚል እምነት አለኝ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የዲያስፖራውን ጉዳይ ካነሳን አይቀር፤ ከ1997 በኋላ በነበረው ፖለቲካ ተስፋ ከመቁረጡም ባሻገር በቅንጅት አባል ፓርቲዎች መካከል ተከፋፍሎ እንደነበር ይነገራል፡፡ ባለፈው ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ዲያስፖራውን እንዴት አገኙት? አሁንስ ምን አዲስ ነገር ይጠብቃሉ?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኔ ስሄድ የምጠብቀው አነስ ያለ ነገር ነው፡፡ ትግል ውስጥ ስትገባ ያለውን አስቸጋሪ ነገር ቀይሬ ከዚህኛው ወደዚህኛው አሻሽለዋለሁ ነው እንጂ፣ ይህኛው አለኝ ብለህ አትኩራራም፡፡ የዓለም የመጨረሻ ድሃ አገር ነን፡፡ የፖለቲካ ባህላችን አስቸጋሪ ነው፡፡ የእምነት አገር ነው፡፡ የ1966 አብዮት የፈጠረው ችግር አለ፣ 1997 የፈጠረው ችግር አለ፡፡ እንደ ፖለቲከኛ ይህን ችግር እለውጣለሁ የሚል እምነት ይዤ ነው የተነሳሁት፡ ፡ ከላይ የተጠቃቀሱት ችግሮች በአንድም ሆነ በሌላ ምክንያት መኖራቸውን ብገነዘብም አንድ መልካም ነገር መኖሩ ሌሎቹን ችግሮች ያቃልላቸዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል የኢሳት መኖር በአገሩ ጉዳይ ተስፋ ቆርጦ የነበረውን የዲያስፖራ ማህበረሰብ መረጃ እንዲኖረውና ተነቃቅቶ እንዲጠብቅ በማድረግ መልካም ስራ አከናውኗል፡፡ በተለይ የሰማያዊ ወጣቶች ‹‹አይቻልም!›› በተባለበት አገር ትንሽም ነገር ሲሰሩ ሲታይና ይህም የማህበረሰባዊ ድህረ- ገጾችን ጨምሮ ለበርካታ ሰዎች መድረሱ አድናቆት አስገኝቶልናል፡፡
እንዲያውም እኛን ከልክ በላይ የማወደስና ነጻ አውጭ አድርጎ የማየት እንጂ በእኛ ላይ ቅሬታ ያለው ሰው የለም፡፡ ለዚህም እድሜያችን እንደመልካም አጋጣሚ ሊታይ የሚችል ነው፡ ፡ እድሜያችን፣ በኢህአፓ፣ በደርግ፣ በመኢሶን የተቋሰለው ትውልድ አለመሆናችን ለፍረጃ ክፍተት አልሰጠም፣ ሰውም እንዲጠላን ምክንያት አልሆነም፡፡ ይህ በእኛ ስራ ሳይሆን በትውልድ ያገኘነው መልካም አጋጣሚ ነው፡፡ እንዲያውም በሰማያዊ በኩል እንደ ችግር ይቆጠራል ከተባለ ሁሉም ኃይል የራሱ ለማድረግ ስለሚሞክር ሚዛን የማስጠበቅና ማዕከል ላይ ሆኖ የማሰባሰብን ሚና ነው እየተወጣ የሚገኘው፡፡
ከዚህ ውጭ ከርቀት ሆነው ወጣትነታችን ሲያዩ የቆዩና ትውልዱ ጫታም፣ ስደተኛና ይህ ነው የሚባል ቁም ነገር የማይሰራ የሚመስላቸው የነበሩ ሰዎች ስንቀራረብ ትልቅ አድናቆት ችረውናል፡፡ መጀመሪያ ላይ በሆይ ሆይታና በጮኸት የተሰባሰብን ቢመስላቸውም ስለ እኛ ካወቁ በኋላ ‹‹እንዲህ አይነት ወጣትም አለ?›› በሚል ተገርመውብናል፡፡ በመልካም ሁኔታም ነው የተቀበሉን፡፡ እስካሁን ያለው ተስፋ ሰጭ ቢሆንም አሁንም ትልቅ ስራ ይጠይቃል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ያለፉት የፖለቲካ ውድቀቶች በመፍራት ወጣቱም ሆነ ዲያስፖራው ፓርቲዎችን ለመቅረብ ይፈራል፡፡ ‹‹ምንድን ነው ማረጋገጫችን?›› የሚል ጥያቄም በስፋት ሲነሳ ይስተዋላል፡፡ ለዚህ ጥያቄ እናንተስ መልሳችሁ ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኛ የምንሰራው ለአገራችን ብለን እንጂ ማንም እንዲያወድሰንና እንዲያምነን ብለን አይደለም፡፡ የሰራነው ነገር ሲያሳምነው ይከተለናል፤ ያምነናልም፡፡ ባለፈው 10 አመት ውስጥ ፖለቲካው ውስጥ ስለነበርን በመውደቅ በመነሳቱ ላይም አልፈናል፡፡ የራሳችንን ታሪክ ያለን እንጂ ከምንም ዱብ ያልን ፖለቲከኞች አይደለንም፡፡ የሚያከብሩን ሰዎች አሉ፣ በቅርብ የተማርንባቸው ሰዎችም አሉ፣ በተግባር ውጣ ውረድ ውስጥም አልፈናል፡፡ ይህ ለመታመን በቂ ይመስለኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰማያዊን የመሰረትን ሰዎች ስብሰባ ላይ በአጋጣሚ የተገናኘን ሳይሆን ከእነ ድክመትና ጥንካሬያችን ለረዥም ጊዜ የምንተዋወቅ ሰዎች ነን፡፡ በጎሳ፣ በወንዝ ልጅነት ሳይሆን ነጻ በሆነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ተገናኝተን በደንብ የተዋወቅን ሰዎች በመሆናችን በቀላሉ እንዳንፈርስ መልካም እድል ይሰጠናል፡፡
በተጨማሪም ይህ አስተሳሰብ ከመውደቅ የመጣ እንጂ ከእኛ ጥፋት የመጣ አይደለም፡፡ ስጋቱ ቢኖርም እኛ በመታመን እንሰራለን እንጂ አያስጨንቀንም፡፡ ምክንያቱም ችግሩ ከእኔ አሊያም ከአንዱ ጓደኛዬ ድክመት የመነጨ ስላልሆነ ነው፡፡ አገራችን ውስጥ አለመተማመን በመኖሩ፣ ሰዎች ደጋግመው በመውደቃቸው፣ አጠቃላይ ክሽፈት በመብዛቱ የተፈጠረ የወል ስነ ልቦና ነው፡፡ ይህ እንደ አገር የጋራ ችግራችን በመሆኑ ይህን ባህል ለመቀየር እንሰራለን እንጂ አንድ ሰው ለምን አላመነኝም ብዬ አልጨነቅም፡፡ ይህን የወል ስነ ልቦና በድፍረት፣ ከራስ ወዳድነትና ከዝርክርክነት ወጥተን፣ አርዕያና ታማኝ በመሆን፣ የውሳኔ አሰጣጥም ሆነ የገንዘብ አወጣጥን ተጠያቂነት በተሞላበት መንገድ በመፈጸም፣ ከአባላት ጋር የቅርብ ግንኙነት በመመስረት፣ የስልጣን ልዩነትን በማጥፋት ሰው ከአሉባልታ ይልቅ በሳይንስና በምክንያታዊ ነገር እንዲመዘን ማድረግ ይቻላል፡፡
እኛ ልናደርግ የምንችለው ሰውን ተስፋ ያስቆረጡትንና ለመለያየት ምክንያት የነበሩትን ነገሮች መቀነስ ነው፡፡ አለመተማመኑ ግን ደጋግሞ የመክሸፉ ችግር እንጂ የሰማያዊ ልጆች ችግር አይደለም፡፡ የሰማያዊ ልጆች ከአሁን በኋላ ምንም ይምጣ እስካሁን ባደረጉት ነገር ብቻ ሊደነቁ ይገባቸዋል፡፡ ባለፈው አስር አመት ውስጥ የግል ህይወታቸውን መኖር እየቻሉ ለአገርና ለወገን ሲሉ ብዙ ስቃይን የሚቀበሉ ልጆችን ማፍራት ችለናል፡፡ ለነጻነታቸው የሚዘምሩ ወጣት ሴቶችን ማፍራት ችለናል፡፡ የወደቀውንና አይቻልም የሚለውን መንፈስ ማነቃቃት ተችሏል፡፡ የወደፊቱ እንዳለ ሆኖ በእስካሁንም ቢሆን ሊመሰገኑ ይገባቸዋል፡ ፡ አለመተማመኑ በውድቀት የመጣ እንደመሆኑ እሱን መቀየር የሚቻለው በስራ ነው፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ለነበረን ቆይታ አመሰግናለሁ::
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኔም አመሰግናለሁ፡፡

Wednesday, March 26, 2014

የተፈናቃዮቹ ድምፅ

 የተፈናቃዮቹ ድምፅ
የአማራ ተወላጆች ዛሬም ተሰደው በአንድነት ፓርቲ ፅህፈት ቤት ይገኛሉ። በአምቦ ከአስራ ዘጠኝ ዓመታት በላይ ከኖሩበት ምድር ልጆች ወልደው ካሳደጉበት ሃብት ንብረት ካፈሩበት ምድር መንግስት ሆን ብሎ ሽብር በማስነሳት በገጀራና በዱላ እየተደበዱ ህይወታቸውን እስከማጣት ድረስ ደርሰዋል የአማራ ተወላጅ በመሆናቸው ብቻ ግፍ እየተፈፀመባቸው ይገኛል ክልሉ የናንተ አይደለም ወደ ክልላችሁ ሂዱ በሚል ሰበብ የዜግነት መብታቸው እየተነፈጉ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየደረሳባቸው ይገኛሉ። እነዚሁ ተፈናቃዮች ወደ አዲስ አበባ መጥተው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ጀምሮ በተዋረድ ላሉ ባለስልጣናት ችግራቸውን ቢያስረዱም ምንም አይነት መፍትሄ ባለማግኘታቸው የሚሰሩ እጆች ምፅዋተኛ ለመሆን ተገደዋል ኧረ ጎበዝ ምን ይሻላል መላ እንበል ሙሉውን ለመከታተል እዚህ ሊንኩን ያጫኑ 





የእሳት ፖለቲካ በኢትዮጵያ (Fire Politics in Ethiopia)

March 25, 2014
ይሄይስ አእምሮ፣ አዲስ አበባ
በሃይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች ዙሪያ ሰሞኑን አንዲት መጣጥፍ ጽፌ ለድረ ገፆች ልኬ ነበር፡፡ ለኅሊናቸው ተገዢ የሆኑ አወጡት – አስነበቡን፤ እግዚአብሔር ይስጣቸው፡፡ ለባህልና ለይሉኝታ ያደሩት እንዲሁም እነሱ በሚፈልጉት ሙዚቃ ብቻ ታንጎና ማሪንጌ መደነስ የሚፈልጉት ወደቅርጫታቸው ከተቱት – ይክተቱት፡፡ ሁሉም የመሰለውን የማድረግ መብት አለውና ያነበበም ያስነበበም፣ ያፈነም ያሳፈነም የኅሊናው ዳኝነት ይፍረደው ከማለት ውጪ በዚህ በውዥንብር ዘመን መወቃቀሱም ሆነ መካሰሱ ፋይዳ የለውም፡፡ ግን ግን የእውነት አምላክ ለሁላችንም እውነተኛውን የልቦናና የኅሊና ሚዛን እንዲሰጠን እጸልያለሁ፡፡ ሁለትና ሁለት ሲደመር አራት ብቻ የሚሆንበት ሃቀኛ ዘመን እንዲመጣልንም እንዲሁ፡፡ በተረፈ የልጆቼ ልጆች “Mother stomach is ranger.” ሲሉ እሰማለሁና በዚያ “ሜጀር” የተቃኘ የቅሬታ ዘፈኔን ጋብዣቸው በገዢዎቻችን አነጋገር ንቅድሚት እላለሁ፤ ሕይወት እንዲህ ናትና፡፡
This is the third time Harar experienced a deadly fire.
አንድ የብዕር ወዳጄ ያቺን መጣጥፍ ካነበበ በኋላ በነካ እጄ በዚህች ወያኔያዊ የእሳት ፖለቲካ ላይ ጥቂት ነገር እንድል አሳሰበኝ፡፡ ርዕሲቱንም የሰጠኝ እርሱ ራሱ ነው – Please take the credit dear Mr. Thingummy, wherever you may be.
ሀገራችን ተመልካች ያጣ የሕዝብ ብዛት ብቻ ሣይሆን ጭንቅት የሚያዞሩ እጅግ በርካታ ችግሮች የሚርመሰመሱባት በመሆኗ አንባቢን ላለማስቸገር ወይም ብዙ አንባቢ የለም በሚል ተስፋ መቁረጥ ወይም “አድማጭና የእርምት እርምጃ ወሳጅ ኃላፊነት የሚሰማው ጤናማ ወገን በሌለበት የኳስ አበደች ሀገራዊ ምስቅልቅል ሁኔታ ውስጥ ተነቦስ ምን ፋይዳ ሊያመጣ?” ከሚል ብሶት የተነሣ ሆን ብለን እየተውነው እንጂ መጻፍ የምንፈልግ ዜጎች የምንጽፈበት ጉዳይ በሽበሽ ነው፤ በበኩሌ አድማጭ ቢኖር ሃያ አራት ሰዓት ብጽፍ የማይደክመኝና የሚያጽፍ ጉዳይም ሞልቶ የተረፈ መሆኑን የምገልጸው የሚያፍኑኝን ድረ ገፆች ደስ አይበላቸው በሚል የመከፋት ስሜት ሳይሆን ተናግረን አድማጭ ባለመኖሩ ሳቢያ በእጅጉ የምቆረቆር መሆኔን በሚጠቁም የቁጭት ስሜት ነው፡፡ የወያኔው የዘረኝነት አባዜ ካስከተለብን ተነግሮ የማያልቅ ሰቆቃና የግፍ አስተዳደር ጀምሮ እነሚሚ ስብሃቱን የመሳሰሉ የሥርዓቱ ዘውጋዊ አባላትና እበላ ባይ ሆዳም ደጋፊዎቻቸው ባቋቋሟቸው የሠራተኛ አስቀጣሪ ድርጅቶች አማካይነት የሚካሄደውን ዘመናዊ ባርነት ብንመለከት ጉዳችን በጽሑፍም ሆነ በቃል ተዘርዝሮ የማያልቅ አስገራሚ ፍጡራን ሆነናል – እኛ “ኢትዮጵያውያን”፡፡ ቴዲ አፍሮ “እዚህ ጋ’ም እሳት፣ እዚያ ጋ’ም እሳት፣ እሳት፣ እሳት፣እሳት…” ሲል እንዳቀነቀነው ሀገራችን ወያኔያዊ እቶን ላይ ተጥዳ በየአቅጣጫው እንደባቄላ አሹቅ እየተንገረገበች ናት፡፡ ፖለቲካው እሳት፣ ሃይማኖቱ እሳት፣ ፌዴራሉ እሳት፣ ፖሊሱ እሳት፣ ቀኑና ሣምንቱ እሳት፣ ወሩና ዓመቱ እሳት፣ ኑሮው እሳት፣ ባለሥልጣናቱ እሳት፣ ነጋዴው እሳት፣ ዳኛው እሳት፣ በሽታው እሳት፣ ርሀቡ እሳት፣…፡፡ ሁሉም በእሳት አለንጋ ይጋረፋል፤ ይጠብሳል፤ ይሸነቁጣል፤ የት እንድረስ? የትስ እንግባ? ከነዚህ ከሲዖል ካመለጡ ሽፍቶች የሚታደገን ማን ነው? አምላከ ኢትዮጵያ ወዴት አለ? ኤሎሄ! ኤሎሄ! ኤሎሁም!  በዚህ መከራችን ላይ ነው እንግዲህ ወያኔ በሐረርም በአዲስ አበባም እንደዚያች ተዘውትራ እንደሚነገርላትና “እዚህ አካባቢ እሳት ይነሳል ብያለሁ” ብላ ባስጠነቀቀች ማግስት ራሷ እንደምትለኩሰው የደሴዋ ዕብድ ሴት በሹምባሾቹ አማካይነት በሚፈልጋቸው ቦታዎች ላይ እሳት እየለኮሰ፣ እንዳይጠፋም ከልካይ ዘብ እያቆመ በሀገር ሀብትና በሕዝብ ዕንባ እየተዝናና የሚገኘው፡፡ ለማንኛውም አስታዋሼን ላመስግንና በጠቆመኝ ሃሳብ ዙሪያ እንዳመጣብኝ ትንሽ ልብከንከን፡፡  እውነትን ላለማየት ዐይነ ኅሊናቸው የታወረ፣  እውነትን ላለመስማት ዕዝነ ልቦናቸው የተደፈነ፣ አእምሯቸው በፀረ-ለውጥ ቫይረስ ለፈውስ ባስቸገረ ሁኔታ  “corrupted” ለሆነ የ“ሚዲያ ሰዎች”ም የቮልቴርን አባባል ባስታውሳቸው ቅር አይለኝም – ቮልቴር እንዲህ አለ አሉ፡- “በምትናገረው ሁሉ ባልስማማም መናገር የምትፈልገውን ጉዳይ በነፃነት መናገር እንድትችል ግን ሕይወቴንም ቢሆን እገብርልሃለሁ!” አይ ኢትዮጵያ! በሁሉም ድሃ፡፡ ግን ተስፋ አለኝ – ትልቅ ተስፋ፡- ወደፊት አንድ ቀን ይህ ሁሉ ድንቁርናችንና ከንቱ ትምክህታችን እንደጤዛ ሲረግፍልን ሰው እንደምንሆን፡፡
በዓለማችን የፖለቲካ ዓይነቶች ብዙ መሆናቸው ከናንተ የተሠወረ አይደለም፡፡ የድንበር ፖለቲካ፣ የውኃ ፖለቲካ፣ የዘር ፖለቲካ፣ የዘውግ ፖለቲካ፣ የውጭ ብድርና ዕርዳታ ፖለቲካ፣ የሀገር ውስጥ የድርቅ ጊዜና የርሀብ ወቅት ዕርዳታ ፖለቲካ፣ የሃይማኖት ፖለቲካ፣ … ዝርዝሩ ብዙና ኪስን ሳይሆን አንጎልን የሚቀድ ነው፡፡ ወያኔ በኢትዮጵያ ላይ ያልሞከረው የፖለቲካ ዓይነት ደግሞ የለም፡፡ እርግጥ ነው ወያኔ ብቻውን አይደለም፡፡ ይህ ቀረሽ የማይባል ሁለንተናዊ ድጋፍ ለወያኔዎች በገፍ እየሰጡ በ17 ዓመታት ውስጥ የሰው ኃይሉን ከሰባት ሰውነት ወደሚሊዮንነት በማሳደግ ፀረ-ኢትዮጵያ አቋማቸውን በተግባር የገለጡት የውጭ ጠላቶቻችንም በዚህ ኢትዮጵያን ወደፖለቲካዊ ቤተ ሙከራነት የመለወጡ ሂደት ውስጥ ያሳዩት ጉልህ ተሳትፎም ለአፍታ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ከዓለም ሕዝቦች መካከል እኛ ኢትዮጵያውያን ላይ ያልተፈተሸ ፖለቲካዊ መርዝ የለም፡፡ ባጭሩ የወያኔ ብቻ ሣይሆን የፈረንጆቹም guinea pig ሆነን የቀረን ብቸኛ መዘባበቻ ዜጎች ብንኖር እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡ እርግጥ ነው እነኢራቅንና አፍጋኒስታንን ብንረሳ አግባብ አይደለም – እኛን እየገረፈን ያለው የኃያላኑ የእሳት ወላፈን እነሱንም እየጠበሰ ነውና፡፡ “አልማሊኪ ቡሽ፣ ካርዛይ ቡሽና መለስ ቡሽ እያሉ ሃቀኛ ሰላም አይኖርም፡፡”
ወያኔ ተግባር ላይ ካዋላቸው ሕዝብን የማሰቃያና ሀገርን የማውደሚያ መንገዶች አንደኛው እሳት ነው፡፡ እንዲህ የምላችሁ ወዳጄ አሁን ስላስታወሰኝ ብቻ እንዳይመስላችሁ፡፡ ከጥንትም በሚገባ አውቀዋለሁ፡፡ ለነገሩ ጨካኝና አምባገነን መንግሥታት ለዓላማቸው ስኬት የማያደርጉት ነገር የለም፡፡ ደርግም በተወሰነ ደረጃ ይህን የእሳት ፖለቲካ ይጠቀምበት እንደነበር በጊዜው ሰምቻለሁ፡፡ ሞኙ ደርግ እሳትን ይጠቀምበት የነበረው ኮንትሮባንድን ከመቆጣጠር አንጻርና በጣም በጥንቃቄ እንደነበር በወቅቱ የነበሩ አሁን ድረስ ያስታውሳሉ፡፡ የወያኔ ግን የተለዬ ነው፡፡
በመሠረቱ ወያኔ ምን እንደሆነ መናገር የዐዋጁን በጆሮ ነው፡፡ ይሁንና ወያኔዎች በተጣባቸው የትውልድ መርገምት ምክንያትም ይሁን በሌላ ከሆዳቸውና ያሻቸውን እንዲሠሩ ከሚጠቅማቸው የጨበጡት ሥልጣን በስተቀር የኢትዮጵያዊነት ስሜት በጭራሽ የሌላቸው፣ እንዲያውም ከያዙት ጥቅምና ሥልጣን ያስወግደናል ብለው የሚፈሩት በቀን ሰመመንና በሌት ቅዠት የሚያባትታቸው የኢትዮጵያዊነት ስሜት በመሆኑ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚልን ዜጋ ሁሉ በየሄደበት እያሳደዱና እየገደሉ በደም ባሕር እየዋኙ የሚኖሩ፣ ጥላቸውንም የማያምኑ የከተማ ወሮበሎች መሆናቸውን እዚህም ላይ በድጋሚ ማስታወሱ በአሰልችነት ሊያስወቅስ አይገባም፡፡ እናም አስታውሱ – ወያኔ የዜጎችን የላብ ውጤት የሆነ ሀብትና ንብረታቸውን ማቃጠል ብቻም ሣይሆን ሕዝብን በሠልፍ ኮልኩሎ እንደሂትለር የኦሽትዊዝ ቻምበር የማይፈልጋቸውን በጋዝ እየለበለበ ቢፈጃቸው የሰይጣናዊ ተፈጥሮው የሞራል ምሰሶ ክፋትና ጥፋት ነውና ደስታን የሚያስገኝለት እንጂ ሰብኣዊነት የሚሰማው ሩህሩህ ፍጡር አይደለም፡፡ ሰብኣዊነትና ወያኔ ዐይንና ናጫ ናቸው፡፡
ወያኔዎች እንደገቡ ሰሞን የምንሰማቸው ብዙ የእሳት አደጋዎች ነበሩ፡፡ እነዚያ እሳቶች እንደሰሞነኞቹ የሕዝብን አንጡራ ሀብትና ገንዘብ ለማቃጠል የታለሙ ሣይሆኑ ጫካና ደን የማያውቁት መደዴዎቹ ወያኔዎች ደቡብ ኢትዮጵያንም እንደሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ለማራቆት የታቀዱ ደኖችን የማቃጠል ወያኔያዊ የክተት ዘመቻዎች ነበሩ፡፡ በርካታ የደቡብና የኦሮሞ ብሔር መኖሪያ አካባቢዎች በነዚያ ወያኔ በቀሰቀሳቸው የሰደድ እሳቶች ተቃጥለዋል – አንጀታቸው ለተፈጥሮም የሚጨክን አረመኔዎች ናቸው፡፡ በምክንያትነት ሲቀርብ የነበረው ግን የኦነግን ሸማቂዎች ከምንጫቸው ለማድረቅና መደበቂያ ቦታ ለማሳጣት የሚል ነበር፡፡ ትግራይ ውስጥ ወያኔን ሊደብቅ የሚችል ዋሻ ካልሆነ በስተቀር ደንና ጫካ እንዳልነበረ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን ጫካ ቢኖር ኖሮ ወያኔን ለማጥፋት በሚል ሰበብ የደርግ መንግሥት ነዳጅ በቦቴ መኪናዎች ጫካ ውስጥ እየደፋ በአብሪ ጥይትም በአሻጋሪ እየለኮሰ ሀገር ለማቃጠል የሚያበቃው የሞራል ድቀት ውስጥ እንዳልነበረ ያንጀቴን እመሰክራለሁ – ሰው ካልሞተ ሚስትም ካልተፈታች ወይ ካልሞተች አይመሰገኑም ወንድማለም፡፡ ደርግ ዜጎችንና ሀገርን በእሳት አይቀጣም፤ ደርግ ኢትዮጵያዊ ጨካኝ እንጂ እንደወያኔ ወፍዘራሽ የባንዳ ውላጅ አልነበረም፡፡ እሳት ባለጌ ነው፡፡ እሳት እጅግ መጥፎ ነው፡፡ ምሕረትን አያውቅም፡፡ እንኳንስ ዜጋህን ጠላትህንም ቢሆን በአግባቡ ውጋው እንጂ፣ በአግባቡ ቅጣው እንጂ ኢ-ሰብኣዊ በሆነ ሁኔታ በእሳት አትገርፈውም፡፡ እነሂትለርና ሙሶሊኒ እንኳንስ ዜጎቻቸውን ጠላቶቻቸውንም ቢሆን በሰደድ እሳት አልቀጡም፤ በእሳት መቅጣት የጀግና ሙያ ሳይሆን የፈሪ ዱላ ነው፡፡ ወያኔ ግን ከየትኛው የጀሃነብ ሰማይ እንደወረደብን አይታወቅም ይሄውና ጫካና ደንን ከማቃጠል አልፎ የምሥኪን ዜጎችን ቤትና ንብረት እንዳሻው በሚያዛቸው ኅሊናቢስ ጀሌዎቹ እያቃጠለ ይገኛል፡፡ ወያኔ እኮ በእሳትም ብቻ ሳይሆን እንደተራ ተንኮለኛ ዜጋ ምግብንና መጠጥን በመመረዝና የታወቀ ጠንቋይ ቤት ድረስም በመሄድ የሚጠላቸውን የሚያስወግድ ጉደኛ ፍጡር ነው፡፡ ኪሮስ አለማየሁ እንዴት ሞተ? አለማየሁ አቶምሳስ? በውነት ቆሻሾች ናቸው፡፡ ምን አድርገን ይሆን ፈጣሪ እነዚህ ለቅጣት የሰጠን ግን? እስኪ ወደዬኅሊና ጓዳችን እንግባና ራሳችንን በቅጡ እንመርምር፡፡
በዚያን ሰሞን ሐረር ውስጥ የተቃጠለው መንደር የዚሁ የወያኔን ዜጎችን በእሳት የመቅጣት የእሳት ፖለቲካ ያሳያል፡፡ የኢትዮጵያን ገንዘብ ለራሱ ፖለቲካ በመጠቀም ዜጎችን በአነስተኛና ቀጫጭን የሚባል አዲስ ፈሊጥ እያደራጀ አንዱን ርሃብተኛ ሌላውን ጥጋበኛ እያደረገ እናያለን፡፡ በጥቃቅን የማይደራጅን በጠላትነት በመፈረጅ በገቡበት እየገባ ያሳድዳቸዋል፡፡ ከወያኔ የተለዬ ነጋዴ ኑሮውና ግብሩ እሳት ሆነው እንዲያቃጥሉትና ከሀገር እንዲጠፋ ወይም በርሀብ አለንጋ ተገርፎ እንዲሞት ሲደረግ ወያኔን የተጠጋ ሆድ አደር ግን እምብርቱ እስኪገለበጥ እየበላና እየጠጣ ተንደላቅቆ ይኖራል፡፡ እንዲህ እንዲኖርም በመዥገሮች የተወረረችው እናት ሀገር በወያኔዎቹ አማካይነት ለአንዱ የእንጀራ እናት ለሌላው ደግሞ የእውነት እናት ሆና ለሆዳም ጥገኞቹ ሁሉንም ነገር እያመቻቸችላቸው ትገኛለች፡፡ ለምሳሌ በወያኔ ማኅበር ያልተደራጀ ዜጋ ሁለት በሁለት ለሆነች የንግድ ቤት ከገቢው ጋር ፈጽሞ የማይመጣጠን እጅግ ከፍተኛ ኪራይና ግብር እንዲከፍል ሲገደድ (ሂድ አትበለው እንዲሄድ ግን አድርገው በሚሉት ፈሊጣቸው) ለሆዳሞቹ ግን ካስፈለገ ካለኪራይና ካለአንዳች ግብር በሕዝብ ገንዘብ እንደፈለጉ ይሆናሉ፡፡ ባንኮች ሳይቀሩ ለነሱ የግል ጥገቶች ናቸው፡፡ የሀገር ስሜት ዛሬ ያልጠፋ ታዲያ መቼ ይጥፋ?
ይህ መሰሉና ሌላው ግፍ ሁሉ አልበቃ ብሎ ነው እንግዲህ የእሳቱ ፖለቲካ በሀገር ደረጃ እየተፋፋመ የሚገኘው፡፡ እንደሰማነው በሐረር ከአንዴም ሁለት ጊዜ ቃጠሎ ተነስቶ በብዙ ሚሊዮን የሚገመት ብርና ሀብትና ንብረት ወድሟል፡፡ ይህ የሆነው በወያኔው ፈቃድና ይሁንታ መሆኑን የምንረዳበት መንገድ ደግሞ እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ሲደረግ አስቀድሞ የተዘጋጀው የወያኔ ጦር እሳቱን ከብቦ አላሰቀርብም ማለቱና የእሳት አደጋ ሠራተኞችም እሳቱ የሚፈለገውን ጥፋት ካገባደደ በኋላ ሥራቸውን እንዲሠሩ መፈቀዱ ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ግፍ ከኢትዮጵያ ውጪ የሚደረግ አይመስለኝም፤ እንዲያውም አይደረግም፡፡ ምክንያቱም የሀገር ዜግነቱን የካደና ሀገር እየቸረቸረ የሚሸጥ የሀገር መሪ ከኢትዮጵያ ውጪ በየትም ሥፍራ ይኖራል ብዬ አላምንምና፡፡
የሐረሩ እሳት መንስኤው ወያኔ ሆኖ ዓላማው ደግሞ ቦታውን ለወያኔያዊ ባለሀብቶች ለመስጠትና በእግረ መንገድም ተቀናቃኝ ኢ-ወያኔያዊ ባለሀብቶችን ለማክሰም ነው – ይህን እውነት ለማወቅ ጠንቋይ መቀለብ አያስፈልግም፡፡ በጣም ግልጽ ነው፡፡ መንታ ዓላማ  ያነገበ ቃጠሎ ነበር ማለት ነው፡፡ አንደኛውና ዋነኛው በሥርዓቱ የማይፈለጉ ዜጎችን ማደኽት – ሁለተኛው በነሱ ቦታ ደግሞ ለሥርዓቱ ዕድሜ ቀን ከሌት ተንበርክከው ሰይጣንን የሚለምኑ ፍቁራን አባላትንና ደጋፊዎችን ማቋቋም፤ በቃ፡፡ በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስ ይባላል፡፡ በኢትዮጵያ መሬት፣ በኢትዮጵያውያን ሀብትና ንብረት ፀረ-ኢትዮጵያ የሆኑ የመንግሥትን ሞሰብ ገልባጮችና ደጋፊዎቻቸው ይገባበዙበታል፤ ይጠቃቀሙበታል፡፡ እንግዴ ልጅ ሀገር ሻጭ ማዕዱን ሲጫወትበት ልጅ ከበይ ተመልካችነትም ወርዶ የሥቃይ ሰለባ ሆኗል፡፡ እየተራቡ በሀገር መኖርም ክልክል ሆኖ ለሞትና ለስደት መዳረግ ዕጣችን እንዲሆን ተፈርዶብናል፡፡ ይህን ቅሚያና ዘረፋ፣ ይህን የግፎች ሁሉ የበላይ የሆነ ግፍ በእሳት አማካይነት እውን ለማድረግ ደግሞ የኢትዮጵያን መለዮ ለባሽ ይጠቀማሉ -በዓይነቱ ልዩ የሆነ የታሪክ ምፀት ማለት ይህ ነው፡፡ ዋ እኔን! ይህች ቀን ልታልፍ እምቢልታው ሲነፋ እነዚህ ጉግማንጉጎች ምን ይውጣቸው ይሆን?
አዲስ አበባም ውስጥ በትንሹ ሁለት ያህል ቃጠሎዎች በነዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ ተከስተዋል፡፡ አንደኛው የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ሲሆን ሌላኛው በአንድ ግለሰብ ቤት የደረሰና የሦስት ሰዎችን ሕይወት የጠየቀ ቃጠሎ ነው፡፡ ያሳዝናል፡፡ ነፍሳቸውን ይማር፡፡ የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤቱ ግን ያጠያይቃል፡፡ እርግጥ ነው – ቃጠሎው ተፈጥሯዊ ሊሆን ይችላል፡፡ እንደማንኛውም አደጋ ሆን ተብሎ ሳይሆን ድንገት ሊነሳ የመቻሉ ዕድል እንዳለ ሆኖ ከወያኔ ባሕርይ ተነስተን ስንገምት መነሾው ፖለቲካዊ አንድምታም ሊኖረው እንደሚችል ብንጠረጥር “ጠርጣሪዎች(skeptics)” ተብለን ልንታማ አይገባም፡፡ እንዲያውም ስንትና ስንት ጥበቃ የሚደረግለት ትልቅ ድርጅት በቀላሉ ለእሳት ይዳረጋል ብሎ ከማሰብ አለማሰብ ይሻላል ብለን ብንከራከር የሚቻል ይመስለኛል፡፡ ስለሆነም ከድንገቴ አደጋነት ይልቅ የወያኔው ተንኮል እንደሚኖርበት መገመት አይከብድም፡፡ ወያኔ ለምን ብርሃንና ሰላምን ያቃጥላል? ምን ያገኛል? ከመገመት ባለፈ እውነተኛውን ነገር ማወቅ ሊከብድ ይችላል፤ መገመት ደግሞ ለማንም የማይከለከል የሁሉም መብት ነው፡፡
ከሁሉም በፊት ግን አንድ አጠቃላይ እውነት መኖሩን እንመን፡፡ ያም እውነት ወያኔ ቢቻል ቢቻል ኢትዮጵያ እንዳለች ብትቃጠል ወይም እንጦርጦስ ብትወርድ ደስ ይለዋል እንጂ የማይከፋ መሆኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ስሟ ሲነሳ የሚዘገንናቸውና ጠበል በመጠመቅ ያለ ሰው ላይ እንደተከሰተ ሰይጣን የሚያንዘረዝራቸው እነበረከትንና ሣሞራን የመሳሰሉ መፃጉዕ ዜጎች የሚገኙበት መንግሥታዊ መዋቅር የኢትዮጵያ ታሪክ የሚዘከርበትና አእምሯዊ ቅርስ የሚቀመጥበት ማዕከል ቢቃጠል አይደሰትም ብሎ ማሰብ የዋህነት ይመስለኛል፡፡ በዕንቆቅልሽ ሀገር ውስጥ ልንጠብቅ የማይገባንን ነገር ብንጠብቅ ብልህነት እንጂ ትዝብት ውስጥ ሊያስገባን የሚችል ሞኝነት አይደለም፡፡
በመሆኑም ወያኔ ይህን የእሳት ፖለቲካውን በመጠቀም ዜጎችን ራቁታቸውን ማስቀረቱንና ወደበረንዳ ሕይወት መለወጡን እንዲያቆም፣ የዘመናት ቅርሳችንን እያቃጠለ ታሪክ አልባ ሆነን እንድንቀር ማድረጉን እንዲገታና እስከተቻለ ደግሞ ነፃነታችንን እውን ለማድረግ የምንችልበትን የጋራ ሥልት መቀየስ እንድንችል የጋራ ጥረት እንድናደርግ ጥሪየን አቀርባለሁ፡፡ ሰላም፡፡

Tuesday, March 25, 2014

Who is who in the Ethiopian Ministry of Foreign Affairs?


Tewodros Adhanom, Minister of Foreign Afaairs (Tigre)
Tewodros Adhanom, Minister of Foreign
Afaairs (Tigre)
March 24, 2014

by Muse Abebe
Despite the claim of TPLF that the federal system has equally protected the rights of ‘nations and nationalities’, the political and economic power is fundamentally controlled by Tigayans who use the cultural differences in the country to their divide and rule strategy.  In the past, Ghinbot 7 and Esat Television were exposing the Tigrean monopoly of almost all positions in the Ministry of Defence, security apparatus and foreign diplomatic missions. Exposing the people who are in control of real power in the country helps to increase the awareness of the public about the nature of the apartheid like regime in Ethiopia. Ghnbot 7 and Esat as well as other democratic organizations need to continue working on this important issue. One of the federal institutions that are entirely controlled by the Tigay elites is the Ministry of Foreign Affairs. Among the top fifteen departments of the ministry,
Tigreans control at least eight of them. Does it mean that there are no Ethiopians from other ethnic groups who can carry out such responsibilities? Where is the diversity that TPLF cries day and night?

1. Tewodros Adhanom, Minister of Foreign Afaairs- Tigre
2. Berhane Gebre-Christo, State Minister of Foreign Afffairs-Tigre
3. Ambassador Negash Kibret,Director General for International Organizations-Tigre
4. Ambassador Grum Abay,Director General For European Affairs- Tigre
5.  Ato Mihreteab Mulugeta ,Chief of Protocol-Tigre
6. Ato Zewdu Gebreweld,Head of the ICT Center- Tigre
7. Gebremichale Gebre Tsadik ,Director General for Plan and Budge-Tigre
8. Dr. Desta Woldeyohannes, Head of the Office of Women’s Affairs-Tigre

“They Know Everything We Do”

MARCH 25, 2014

“They Know Everything We Do”

Telecom and Internet Surveillance in Ethiopia

Summary
Recommendations
To the Government of Ethiopia
To International Technology and Telecom Companies Serving Ethiopia
To the Governments of China, Germany, Italy, the United Kingdom, and Others
To the World Bank, African Development Bank, and other Donors

Ethiopia spies on citizens with foreign technology: HRW

March 25, 2014
AFP – Ethiopia is using foreign technology to spy on citizens suspected of being critical of the government, Human Rights Watch said in a report released Tuesday.
Ethiopia is using foreign technology to spy on citizens
The report accused the government of using Chinese and European technology to survey phone calls and Internet activity in Ethiopia and among the diaspora living overseas, and HRW said firms colluding with the government could be guilty of abuses.
“The Ethiopian government is using control of its telecom system as a tool to silence dissenting voices,” HRW’s business and human rights director Arvind Ganesan, said in a statement.
“The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses.”
The Ethiopian government dismissed the report as “mud-slinging” and accused the rights watchdog of repeatedly unfairly targeting the country.
“This is one of the issues that it has in the list of its campaigns to smear Ethiopia’s image, so there is nothing new to respond to it, because there is nothing new to it,” Ethiopia’s Information Minister, Redwan Hussein, told AFP.
He said Ethiopia is committed to improving access to telecommunications as part of its development program, not as a means to increase surveillance.
“The government is trying its level best to create access to not only to the urban but to all corners of the country,” Redwan added.
Ethiopia’s phone and internet networks are controlled by the state-owned Ethio Telecom, the sole telecommunications provider in the country.
HRW said the government’s telecommunications monopoly allows it to readily monitor user activity.
“Security officials have virtually unlimited access to the call records of all telephone users in Ethiopia. They regularly and easily record phone calls without any legal process or oversight,” the report said.
The rights watchdog said information gathered was often used to garner evidence against independent journalists and opposition activists, both inside Ethiopia and overseas.
In February, a US man filed a lawsuit against the Ethiopian government, accusing authorities of infecting his computer with spyware to monitor his online activity.
Rights groups have accused Ethiopia of cracking down on political dissenters, independent media and civil society through a series of harsh laws, including anti-terrorism legislation.
Only about 23 percent of Ethiopia’s 91 million people subscribe to mobile phones, and less than one percent have access to mobile internet, according to the International Telecommunications Union.
The government has committed to increasing mobile access by 2015, as part of an ambitious development plan.
Ethiopia has hired two Chinese firms, ZTE and Huawei, to upgrade the mobile network across the country.
———————
Human Right Watch Full Report

Ethiopia: Telecom Surveillance Chills Rights

Foreign Technology Used to Spy on Opposition inside Country, Abroad
(Berlin) – The Ethiopian government is using foreign technology to bolster its widespread telecom surveillance of opposition activists and journalists both in Ethiopia and abroad, Human Rights Watch said in a report released today.
The 100-page report“‘They Know Everything We Do’: Telecom and Internet Surveillance in Ethiopia,” details the technologies the Ethiopian government has acquired from several countries and uses to facilitate surveillance of perceived political opponents inside the country and among the diaspora. The government’s surveillance practices violate the rights to freedom of expression, association, and access to information. The government’s monopoly over all mobile and Internet services through its sole, state-owned telecom operator, Ethio Telecom, facilitates abuse of surveillance powers.
“The Ethiopian government is using control of its telecom system as a tool to silence dissenting voices,” said Arvind Ganesan, business and human rights director at Human Rights Watch. “The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses.”
The report draws on more than 100 interviews with victims of abuses and former intelligence officials in Ethiopia and 10 other countries between September 2012 and February 2014. Because of the government’s complete control over the telecom system, Ethiopian security officials have virtually unlimited access to the call records of all telephone users in Ethiopia. They regularly and easily record phone calls without any legal process or oversight.
Recorded phone calls with family members and friends – particularly those with foreign phone numbers – are often played during abusive interrogations in which people who have been arbitrarily detained are accused of belonging to banned organizations. Mobile networks have been shut down during peaceful protests and protesters’ locations have been identified using information from their mobile phones.
A former opposition party member told Human Rights Watch: “One day they arrested me and they showed me everything. They showed me a list of all my phone calls and they played a conversation I had with my brother. They arrested me because we talked about politics on the phone. It was the first phone I ever owned, and I thought I could finally talk freely.”
The government has curtailed access to information by blocking websites that offer any independent or critical analysis of political events in Ethiopia. In-country testing that Human Rights Watch and Citizen Lab, a University of Toronto research center focusing on internet security and rights, carried out in 2013 showed that Ethiopia continues to block websites of opposition groups, media sites, and bloggers. In a country where there is little in the way of an independent media, access to such information is critical.
Ethiopian authorities using mobile surveillance have frequently targeted the ethnic Oromo population. Taped phone calls have been used to compel people in custody to confess to being part of banned groups, such as the Oromo Liberation Front, which seeks greater autonomy for the Oromo people, or to provide information about members of these groups. Intercepted emails and phone calls have been submitted as evidence in trials under the country’s flawed anti-terrorism law, without indication that judicial warrants were obtained.
The authorities have also detained and interrogated people who received calls from phone numbers outside of Ethiopia that may not be in Ethio Telecom databases. As a result, many Ethiopians, particularly in rural areas, are afraid to call or receive phone calls from abroad, a particular problem for a country that has many nationals working in foreign countries.
Most of the technologies used to monitor telecom activity in Ethiopia have been provided by the Chinese telecom giant ZTE, which has been in the country since at least 2000 and was its exclusive supplier of telecom equipment from 2006 to 2009. ZTE is a major player in the African and global telecom industry, and continues to have a key role in the development of Ethiopia’s fledgling telecom network. ZTE has not responded to Human Rights Watch inquiries about whether it is taking steps to address and prevent human rights abuses linked to unlawful mobile surveillance in Ethiopia.
Several European companies have also provided advanced surveillance technology to Ethiopia, which have been used to target members of the diaspora. Ethiopia appears to have acquired and used United Kingdom and Germany-based Gamma International’s FinFisher and Italy-based Hacking Team’s Remote Control System. These tools give security and intelligence agencies access to files, information, and activity on the infected target’s computer. They can log keystrokes and passwords and turn on a device’s webcam and microphone, effectively turning a computer into a listening device. Ethiopians living in the UK, United States, Norway, and Switzerland are among those known to have been infected with this software, and cases have been brought in the US and UK alleging illegal wiretapping. One Skype conversation gleaned from the computers of infected Ethiopians has appeared on pro-government websites.
Gamma has not responded to Human Rights Watch inquiries as to whether it has any meaningful process in place to restrict the use or sale of these products to governments with poor human rights records. While Hacking Team applies certain precautions to limit abuse of its products, it has not confirmed whether and how those precautions applied to sales to the Ethiopian government.
“Ethiopia’s use of foreign technologies to target opposition members abroad is a deeply troubling example of this unregulated global trade, creating serious risks of abuse,” Ganesan said. “The makers of these tools should take immediate steps to address their misuse; including investigating the use of these tools to target the Ethiopian diaspora and addressing the human rights impact of their Ethiopia operations.”
Such powerful spyware remains virtually unregulated at the global level and there are insufficient national controls or limits on their export, Human Rights Watch said. In 2013, rights groups filed a complaint at the Organization for Economic Co-operation and Development alleging such technologies had been deployed to target activists in Bahrain, and Citizen Lab has found evidence of use of these tools in over 25 countries.
The internationally protected rights to privacy, and freedom of expression, information, and association are enshrined in the Ethiopian constitution. However, Ethiopia either lacks or ignores judicial and legislative mechanisms to protect people from unlawful government surveillance. This danger is made worse by the widespread use of torture and other ill-treatment against political detainees in Ethiopian detention centers.
The extent of Ethiopia’s use of surveillance technologies may be limited by capacity issues and a lack of trust among key government ministries, Human Rights Watch said. But as capacity increases, Ethiopians may increasingly see far more pervasive unlawful use of mobile and email surveillance.
The government’s actual control is exacerbated by the perception among many Ethiopians that government surveillance is omnipresent, resulting in considerable self-censorship, with Ethiopians refraining from openly communicating on a variety of topics across telecom networks. Self-censorship is especially common in rural Ethiopia, where mobile phone coverage and access to the Internet is very limited. The main mode of government control is through extensive networks of informants and a grassroots system of surveillance. This rural legacy means that many rural Ethiopians view mobile phones and other telecommunications technologies as just another tool to monitor them, Human Rights Watch found.
“As Ethiopia’s telecom system grows, there is an increasing need to ensure that proper legal protections are followed and that security officials don’t have unfettered access to people’s private communications,” Ganesan said. “Adoption of Internet and mobile technologies should support democracy, facilitating the spread of ideas and opinions and access to information, rather than being used to stifle people’s rights.”
Source. ECADEF