Tuesday, April 15, 2014

በኖርዌ ኦስሎ ከተማ የግንቦት 7 አመራር አባል አቶ ብዙነህ ፅጌ በተገኙበት ታላቅ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ

በሁለገብ ትግላችን ወያኔን እናስወግዳለን በሚል መሪ ቃል የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ በአፕሪል 12, 2014 በወቅታዊ የሐገራችን ሁኔታ ላይ ታላቅ ህዝባዊ ውይይት አዘጋጀ። በዝግጅቱ ላይ ተጋባዥ እንግዳ የነበሩት የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ብዙነህ ፅጌ ነበሩ። 

የኦስሎ ነዋሪዎች እና ከኖርዌ የተለያዩ ከተሞች የመጡ በርካታ ታዳሚዎች በዝግጅቱ ላይ የተገኙ ሲሆን በኖርዌጂያን የሰአት አቆጣጠር ከቀኑ 15፡00 የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ የህዝብ ግንኝነት ሃላፊው በወያኔ ስርአት ለተጎዱ ወገኖቻችን እንዲሁም በየእስር ቤቱ ያለወንጀላቸው ለሚሰቃዩና ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን በሙሉ መታሰቢያ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት እንዲያደርግ ታዳሚውን ጋብዘው ፕሮግራሙን አስጀምረዋል። በመቀጠል የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ዋና ሊቀመንበር የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ በተመለከተ አመሰራረቱን እና የቆመለትን አላማ እንዲሁም የትኛውን የፖለቲካ ድርጅት እንደሚደግፍ እንዲሁም ድርጅቶቹን ለምን እንደሚደግፍ እንዲሁም የድርጅቱን አላማ በማስመልከት ለታዳሚው ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ተጋባዥ እንግዳው አቶ ብዙነት ፅጌ በተራቸው ስለ ኢትዮጵያ ያለፉት መንግሰታት ከንጉሱ ጊዜ ጀምሮ የደርግን መንግስት እና አሁን እስከደረስንበት የአፈና አገዛዝ ድረስ ያለውን የኢትዮጵያ መንግስታቶች ታሪክ በዝርዝር ለታዳሚው በሚገባ መልኩ አስረድተው በተለይ አሁን ያለውን የአምባገነን ስርአት ከድሮው መንግስታቶች ጋር በማነፃፀር ምን ያህል አስከፊ እንደሆነ አስረድተዋል። ማብራሪያቸውን ከጨረሱ በኋላ የተለያዩ ታዳሚዎች በተለያዩ የሃገራችን ጉዳዮች እና ግንቦት 7 ትን አስመልክቶ ላቀረቡላቸው ጥያቄች በቂ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዝግቱ ላይ የተለያዩ አዝናኝ ባህላዊ ውዝዋዜዎች እንዲሁም ምግብና መጠጥ የተዘጋጀ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ም/ክትል ሊ/መንበር ሰፋ ያለ ቀስቃሽ የአቋም መግለጫ በመስጠት የማጠቃለያ ንግግር አድርገው ዝግጅቱ ከምሽቱ በ21፡00 በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር
ሄለን ንጉሴ/ኖርዌ

No comments:

Post a Comment