Friday, January 31, 2014

ኢህአዴግ ሚኒስትሮቹን የግንባሩን ስራ እንዲያከናውኑ መደበ


ኢህአዴግ ፓርቲውን እንዲመሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ሌሎች ሁለት ሚኒስትር ዴኤታዎችን ባለፉት ወራት መሾሙን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ጠቆሙ፡፡

ኢህአዴግ የመንግስት መዋቅርን ከፓርቲው መዋቅር ጋር አደበላልቆ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተደጋጋሚ ወቀሳዎችና ትችቶች እየቀረቡበት የቆየ ሲሆን በዚህ መልኩ ግልጽ የሆነ አደረጃጀት በመያዝ የመንግስት ከፍተኛ አመራሮችን ሲመድብ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሎአል፡፡
ቀደም ሲል የግንባሩ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመናብርት የግንባሩንና የአባል ፓርቲዎችን የሚመሩበት ሁኔታ የተለመደ ሲሆን የአሁኑ አደረጃጀት ግን ለየት የሚያደርገው በሚኒስትር ዴኤታ ማእረግ ጭምር በመንግስት ሃላፊነት ላይ የተመደቡ ሹማምንት ከነጥቅሞቻቸው ወደ ፓርቲው ሃላፊነት ተመድበው የመምጣታቸው ጉዳይ ነው፡፡ ሰዎቹ አብዛኛውን ጊዜያቸውን በፓርቲው ስራዎች እንደሚያጠፉ የጠቆሙት ምንጮቻችን ይህም ከመጪው ምርጫ ጋር በቀጥታ የተያዘ ነው፡፡
በዚሁ መሰረት አቶ ደመቀ መኮንን ምክትል ጠ/ሚኒስትርና የኢህአዴግ ጽ/ቤትን በበላይነት የሚመሩ ሲሆን አቶ ደስታ ተስፋው እና አቶ አማኑኤል አብርሃም በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ በጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት ሆነው ግንባሩን በተለያዩ ሃላፊነቶች እንዲመሩ ተመድበዋል፡፡ እነዚህ ሹማምንት በመንግስት ገንዘብ፣ ነዳጅና ጊዜ የፓርቲ ስራዎችን ማከናወናቸው ፖለቲካዊ ሙስና መሆኑን ስለጉዳዩ ያነጋገርናቸው ወገኖች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢህአዴግ የተማሩ አባሎች የሉትም በሚል የሚደርስበትን ትችት አስተባብሎአል። ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ያልቻለው የተማሩ አባላትና ተሿሚዎች ስለሌሉት ነው በሚል ከተቃዋሚዎችና ከሌሎች ወገኖች የሚቀርብበትን ተደጋጋሚ ትችት ሃሰት ነው ብሎአል፡፡
በጠቅላ ሚኒስቴር ቢሮ የሕዝብ ተሳትፎና አደረጃጀት ሚኒሰትር ዴኤታና የኢህአዴግ ጽ/ቤት የህዝብና የውጪ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ ደስታ ተስፋው ለመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ የዛሬ ዕትም በሰጡት መግለጫ በአሁን ወቅት የመልካም አስተዳደር ችግር አለባቸው የሚባሉት ስላልተማሩ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ መድረስ አያግባባም ካሉ በሃላ በአሁኑ ወቅት የኢህአዴግ አባላት የትምህርት ደረጃቸውን እያሻሻሉ ነው ብለዋል፡፡
ተቃዋሚ ፓርቲዎች አጀንዳ አድርገው የሚያቀነቅኑት በፍጹም የተሳሳተ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በአባላት መካከል ውድድር ቢካሄድ የኢህአዴግ አባላት በትምህርትና በብቃት እንደሚበልጡ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
አንድ የኢህአዴግ ተሹዋሚ ሲያጠፋ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ወደሌላ ቦታ ማዛወር ሁኔታ እንዳለ ለቀረበላቸው ጥያቄም ሲመልሱ በኢህአዴግ ውስጥ አንድ ቦታ ብቁ ሆኖ ያልተገኘ ሌላ ቦታ ሄዶ እንዲሰራ እንደሚደረግ አምነዋል፡፡“በኢህአዴግ ድርጅት ውስጥ ባለው አሰራር መሰረት እያንዳንዱ ግለሰብ ተግባር ይሰጠዋል፡፡  የተሰጠውን ተግባር እንዴት እንደፈጸመ ይገመገማል፡፡በግምገማ ውጤቱ ስራውን በብቃት የፈጸመ አባል ተመስግኖ ለቀጣይ ስራ እንዲዘጋጅ ይደረጋል፡፡በአንጻሩ ደግሞ ድክመት የታየበት አባል እንዲያስተካክል የተለያዩ ተግባራት ይከናወናሉ፡፡ለምሳሌ ያህል ሂስ ይደረጋል፣እንደየሁኔታው በማስጠንቀቂያም ይታለፋል፡፡ የተመደበበት የስራ ቦታ ከብቃቱ ጋር የማይመጣጠን ሆኖ ከተገኘ ከቦታው ተነስቶ የሚችለው ስራ መደብ ላይ ይቀየራል ”ሲሉ አስረድተዋል፡፡
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት ትልቅ ችግር አድርጎ የሚያየው የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብን ነው ያሉት አቶ ደስታ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እየተባባሱ አለመምጣታቸውን፣እንዲያውም ወደመልካም አስተዳደር በጉዞ ላይ ነን በማለት እርስ በርሱ የተምታታ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ጥር ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-

Thursday, January 30, 2014

ኢህአዴግ ልማቱን ለመጨረስ ከ40 እስከ 45 አመት ያስፈልገዋል ሲሉ አቶ በረከት ተናገሩ


የጠ/ሚንስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ አማካሪ የሆኑት አቶ በረከት ስምዖን ይህን የተናገሩት ለኢህአዴግ ከፍተኛ ካድሬዎች ነው። ለማንኛውም የመገናኛ ብዙሃን ዝግ በሆነው የካድሬዎች ስብሰባ ላይ ጥናታዊ ወረቀታቸውን ያቀረቡት አቶ በረከት፣ ኢህአዴግ የህዝቡን የነፍሰ ወከፍ ገቢ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ለማድረስ  ቢያንስ ከ40 እስከ 50 ዓመታት እንደሚያስፈልገው ገልጸዋል።

አቶ በረከት የወደፊቱ የህዳሴ መንገድ በሚል ባቀረቡት ጽሁፍ ፣ ግንባሩ የኢትዮጵያ ህዳሴ በስንት ዓመታት ሊጠቃለል ይችላል የሚለውን ከእነኮሪያና ታይዋን ልምድ በመውሰድ መስራቱን ተናግረዋል። አገሮች ከዝቅተኛ ወደ መካከለኛ ከዚያም ወደ ከፍተኛ ገቢ ለመድረስ ከ40 እስከ 50 ዓመታት መውሰዳቸውን ገልጸዋል ።
አቶ በረከት መካከለኛ ገቢ የሚባለው ከገቢ አንጻር ሲሰላ ዝቀተኛው 1000 ዶላር ከፍተኛው ደግሞ 5 ሺ ዶላር መሆኑን ጠቅሰዋል። ባለፈው 10 አመታት የጀመርነውን እድገት ከቀጠልን በሚቀጥሉት 10 አመታት የመካከለኛው ገቢ ዝቀተኛ ጣራ ከሆነው 1000 ዶላር የነፍስ ወከፍ ገቢ ደረጃ ላይ እንደርሳለን የሚሉት አቶ በረከት፣ የመካከለኛ ገቢ ከፍተኛ ጣራ ከሆነው 5 ሺ ዶላር የነፍስ ወከፍ ገቢ ለመድረስ እንደገና ተጨማሪ 15 ወይም 20 አመታት ይወስድብናል ብለዋል;፡
የከፍተኛው ገቢ የመጨረሻው ደረጃ ለሆነው የ10 ሺ ዶላር የነፍስ ወከፍ ገቢ ደረጃ ለመድረስ ሌላ ከ15-20  ተጨማሪ አመታት እንደሚያስፈልግ አቶ በረከት አክለዋል። ይህንን ጊዜ ለማሳጠር ብንፈልግ ልናሳጥረው አንችልም የሚሉት አቶ በረከት ፣ እድገቱ አንዳንዴም ልክ ቱኒዚያ፣ ታይላንዳና ማሌዢያ እንደተቋረጠባቸው ሊቋረጥ ይችላል ብለዋል።
ይህን እደገት ለማስቀጠል ፈተናዎች አሉ ያሉት አቶ በረከት፣ አንደኛው ፈተና  እድገቱን ህብረተሰቡ ሳይሰለች ማስቀጠል ይችላል ወይ  የሚለው ነው ሰሉ ተናግረዋል።
“ነባሩ አመራር  በእድሜ፣ በጤናና በመድከም ከሃላፊነት የሚወጣ በመሆኑ አዲሱ ትውልድ በተመሳሳይ ትኩረትና ፍጥነት እድገቱን ይዞት ሊሄድ ይችላል ወይ?’ የሚለው ጥያቄ ያልተመለሰና መመለስ ያለበት ነው ሲሉ ኢህአዴግ ያጋጠመውን ፈተና ገልጸዋል። ኢሳት የድምጽ መልእክቶችን በመላክ የሚተባበሩንን ከፍተኛ የኢህአዴግ አመራሮች ለማመስገን ይወዳል።

ምንጭ፡ ኢሳት ጥር 22፣ 2006

Wednesday, January 29, 2014

Ethiopia – Land for Sale


January 28, 2014

As the economy thrives, we examine the plight of Ethiopians forced from their land to make way for foreign investors.

NGO’s and policy advocates say the true consequences of the land grabs are almost all negative [Reuters]
NGO’s and policy advocates say the true consequences of the land grabs are almost all negative [Reuters]
Just a few decades ago, Ethiopia was a country defined by its famines, particularly between 1983-1985 when in excess of half a million people starved to death as a consequence of drought, crop failure and a brutal civil war.
Against this backdrop, it is impressive that in recent years, Ethiopia has been experiencing stellar economic growth. The headline statistics are certainly remarkable: the country is creating millionaires faster than any other in Africa; output from farming, Ethiopia’s dominant industry, has tripled in a decade; the capital Addis Ababa is experiencing a massive construction boom; and the last six years have seen the nation’s GDP grow by a staggering 108 percent.
But it is not all positive news, because for all the good figures there are still plenty of bad ones.
Around 90 percent of the population of 87 million still suffers from numerous deprivations, ranging from insufficient access to education to inadequate health care; average incomes are still well below $1500 a year; and more than 30 million people still face chronic food shortages.
And while there are a number of positive and genuine reasons for the growth spurt – business and legislative reforms, more professional governance, the achievements of a thriving service sector – many critics say that the growth seen in agriculture, which accounts for almost half of Ethiopia’s economic activity and a great deal of its recent success, is actually being driven by an out of control ‘land grab’, as  multinational companies and private speculators vie to lease millions of acres of the country’s most fertile territory from the government at bargain basement prices.
At the ministry of agriculture in Addis Ababa, this land-lease programme is often described as a “win-win” because it brings in new technologies and employment and, supposedly, makes it easier to improve health care, education and other services in rural areas.
“Ethiopia needs to develop to fight poverty, increase food supplies and improve livelihoods and is doing so in a sustainable way,” said one official.
But according to a host of NGO’s and policy advocates, including Oxfam, Human Rights Watch and the Oakland Institute, the true consequences of the land grabs are almost all negative. They say that in order to make such huge areas available for foreign investors to grow foodstuffs and bio-fuels for export – and in direct contravention of Ethiopia’s obligations under international law – the authorities are displacing hundreds of thousands of indigenous peoples, abusing their human rights, destroying their traditions, trashing the environment, and making them more dependent on food aid  than ever before.
“The benefits for the local populations are very little,” said renowned Ethiopian sociologist Dessalegn Rahmato. “They’ve taken away their land. They’ve taken away their natural resource, because these investors are clearing the land, destroying the forest, cutting down the trees. The government claims that one of the aims of this investment was to enable local areas to benefit by investing in infrastructure, social services … but these benefits are not included in the contract. It’s only left up to the magnanimity of the investor.”
And those investors, he continued, are simply not interested in anything other than serving their own needs: “They can grow any crop they want, when they want it, they can sell in any market they want, whether it’s a global market or a local market. In fact most of them are not interested in the local markets.”
He cited as an example a massive Saudi-owned plantation in the fertile Gambella region of south west Ethiopia, a prime target area for investors: “They have 10,000 hectares and they are producing rice. This rice is going to be exported to the Middle East, to Saudi Arabia and other places. The local people in that area don’t eat rice.”
But the most controversial element of the government’s programme is known as ‘villagisation’ – the displacement of people from land they have occupied for generations and their subsequent resettlement in artificial communities.
In Gambella, where two ethnic groups, the Anuaks and the Nuers, predominate, it has meant tens of thousands of people have been forced to abandon a traditional way of life. One such is Moot, an Anuak farmer who now lives in a government village far from his home.
“When investors showed up, we were told to pack up our things and to go to the village. If we had decided not to go, they would have destroyed our crops, our houses and our belongings. We couldn’t even claim compensation because the government decided that those lands belonged to the investors. We were scared … if you get upset and say that someone stole your land, you are put in prison. If you complain about being arrested, they will kill you. It’s not our land anymore; we have been deprived of our rights.”
Despite growing internal opposition and international criticism, the Ethiopian government shows no sign of scaling the programme back. According to the Oakland Institute, since 2008, an area the size of France has already been handed over to foreign corporations. Over the next few years an area twice that size is thought to be earmarked for leasing to investors.
Source: ALJAZEERA

Tuesday, January 28, 2014

America Watch Jawar Mohammed Muslim extremist


Documentary video exposing Mr. Jawar Mohammed Ethiopian born ethnic Oromo Muslim extremist (currently American citizen) who insisting hate and violence against none Muslim Ethiopians.


Mr. Jawar Mohammed Ethiopian born Muslim extremist
Mr. Jawar Mohammed Ethiopian born Muslim extremist

Monday, January 27, 2014

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ለራሱ ሲል ይጣፍጥ

ግርማ ሠይፉ ማሩ
የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የስራ እንቅሰቃሴን አሰመልክቶ አዲሱ የቦርዱ ስብሳቢ አቶ ሬዲዋን ሁሴን ሪፖርት ለምክር ቤት አቅርበው ነበር፡፡ እኔም የበኩሌን አሰተያየት እና ጥያቄዎች አቅርቤ ነበር፡፡ ሪፖርቱ ባጠቃላይ ሲታይ የምናውቀውን ደካማ ተቋም በግልፅ ያሳየን ነበር፡፡ በሪፖርቱ እንደመልካም ስራ የቀረበው ደግሞ ያፈርንባቸው ዶክመንተሪዎች መሆናቸው ሌላ ነጥብ ነው፡፡ እነዚህ ስራዎቸ ደግሞ በህዝብ የተወደዱ ናቸው ተብለናል፡፡ አስገራሚ ደግሞ በድርጅቱ የሚሰራውን ፕሮግራም የሚወደው ህዝብ ለቴሌቪዥን ኪራይ በዓመት አምሳ ብር ለመክፈል ያለመፈለግ ዝንባሌ ያሳያል መባሉ ነው፡፡ በእኔ አረዳድ የህዝቡ ያለመክፈል አዝማሚያ ምንጭ ህዝቡ በደረሰበት የዕድገት ደረጃ የሚመጥን የቴሌቪዥን አገልግሎት ስለማያገኝ ነው፡፡ አንድ የእግር ኳስ ጨዋታ ለማየት ህዝቡ ስንት እንደሚከፍል እናውቃለን፡፡

በዕለቱ ካቀረቡኩት ጥያቄ ምላሽ የተነፈገው ዋነኛው ጥያቄ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በሪፖርቱ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከማጠናከር አንፃር ስራዎች ተሰርተዋል በማለት ያቀረበው ልክ አይደለም የሚል ሲሆን፤ ለዚህ ማሳያም አንድነት እና ኢህአዴግ እኩል ፓርቲዎች ቢሆኑም የአንድነት ጠቅላላ ጉባዔ በሚዲያ ሳይዘግብ የኢህአዴግን ጉባዔ ግን ከባህርዳር በቀጥታ ስርጭት ጭምር ሲዘገብ እንደነበረ ያቀረቡክት ነው፡፡ ለዚህ ጥያቄ ክቡር ሚኒስትሩ እንደ ካድሬም ማሳሳቻ ነገር ስለ አልታያቸው በዝምታ ማለፉን እንደ ዘዴ መምረጣቸውን ወድጄዋለሁ፡፡

ሌሎችን አሰተያየቶችን በተመለከተ ደግሞ ሃሳቡን በማሳሳት ተርጉመው ለማሳሳት የሞከሩባቸውን ናቸው፡፡ በሪፖርቱ ውስጥ “ብሔራዊ መግባባት ለማጎልበት ጥረት ተደርጎዋል” ይላል፡፡ እኔ ይህን የሚደግፍ ሰራ በሪፖርቱ ውስጥ የሌለው መሆኑን አመልክቼ ይልቁንም ድርጅቱ ያለመግባባት ለማምጣት ነው የሚሰራ የሚመስለው የሚል ሃሳብ ስሰነዝር፡፡ አቶ ሬድዋን ግን የሚሰሙት መበታተን ብለው ነው፡፡ ኢህአዴግም ሆነ ካድሬዎቹ አንድ ጉዳይ ጠንከር ብሎ ከታያቸው መመሽጊያቸው ይህች ሀገር ልትበተን ነው ወደሚለው ፅንፍ መሄድ ነው፡፡ ኢህአዴግ በፈለገው አስማት ከዚህ ወንበር ቢነሳ፤ ይህች ሀገር ምንም ዓይነት የመበተን አደጋ የለባትም፡፡ ለምን ይህን ካርድ እንደሚወዱት አይገባኝም፡፡

ሌላው አዲስ የሰማሁት ፍልስፍና ደግሞ “መነሻችን ከተለያየ፣ መድረሻችንም ይለያያል” የሚለው ነው፡፡ በየትኛውም ህግ አንድ ቦታ ለመድረስ ከተመሳሳይ ቦታ መነሳት የግድ አይልም፡፡ በኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ያሰፈልጋል ብለን ከልብ የምናምን ሰዎች መነሻችን እንደሚለያይ ብቻ ሳይሆን፣ ልንሄድበት የምንፈልጋቸው መንገዶች በአብዛኛው የተለያዩ ቢሆኑ እንኳን መድረሻችን አንድ ወይም ተመሳሳይ ነው የሚል እምነት አለን፡፡ ይህውም የሀገራችን ዕድገትና ብልፅግና ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚሆነው ሰላም ዲሞክራሲ እና የዜጎች ሰብዓዊ መብት የሚከበርበት ሀገር እና የፖለቲካ ስርዓት ሲፈጠር እንደሆነ ጥርጥር የለንም፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ትግሉ፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያ “ትግል” የሚለውን ቃል ከፖለቲካችን ለማውጣት እና ድህነትን በጋራ ለምናደርገው ርብርብ ብቻ እንድንጠቀምበት ለማድረግ ኳሱ ያለው በኢህአዴግ እጅ ነው፡፡ ኢህአዴግ ከቆረበበት የአብዮታዊ ዲሞክራሲ/ግራ ዘመም ፖለቲካ መውጣት የግድ ይለዋል፡፡ ምክንያቱም የዚህ መስመር ተከታዮች ትንተና የሚያደርጉበት ማዕቀፍ ሁልጊዜ ተቃራኒ ወገን ይፈልጋል፡፡ ምቀኛ አታሳጣኝ ፍልስፍና ነው፡፡ ለውጥ ለማምጣት ደግሞ ይህ ተቃራኒ ወገን መጥፋት አለበት ብለው ያምናሉ፡፡ ለዚህ ነው ገድለው እንኳን እርግጠኛ ስለማይሆኑ መቃብር ላይ ግንብ የሚገነቡት፡፡ በዚህ ዓይነት የትንተና መስመር የሚመራ ፓርቲና መንግሰት የመድበለ ፓርቲ ሰርዓትን ከምር ሊወስድ አይችልም፡፡ ስለዚህ ድምዳሜው “መነሻችን ከተለያየ፣ መድረሻችንም ይለያያል” የሚል ፅንፍ የሚደርሰው፡፡

ኢህአዴግ እና አባላቱ አብዮታዊ ዲሞክራሲ አመለካከት መያዝ ምርጫቸው ከሆነ መከበር ያለበት መብት ነው፡፡ ልናከብርላቸው ይገባል፡፡ ሆኖም ግን ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ አመለካከት መገንባት እያሉ በየሲቪል ሰርቪሱ እና መንግሰት ተቋማት በአብዮታዊ ዲሞክራሲ አስተሳሰብ ማጥመቅ፤ ህገ መንግሰታዊ ስርዓቱ የፈቀደውን የሃሳብ ልዩነትን መድፈር ነው፡፡ ለዚህ ሁነኛ ምሳሌ ደግሞ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አንዱ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህገ መንግሰት አንቀፅ 29/5 “በመንግስት ገንዝብ የሚካሄድ ወይም በመንግስት ቁጥጥር ስር ያለ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አሰተያየቶችን ለማስተናገድ በሚያስችል ሁኔታ እንዲመሩ ይደረጋል፡፡” ይላል፡፡ ይህን ህገ መንግሰታዊ ድንጋጌ ጥሰው የመንግሰት ሚዲያዎች ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ መንገድ ውጭ ሌሎች አመለካከቶችን ለማስተናገድ ለዜጎችም ሆነ ቡድኖች አንድም ክፍት ቦታ ለመስጠት ዝግጁ አይደሉም፡፡ ይልቁንም አቋም ይዘው የስም ማጥፋት ዘመቻ ይሰራሉ፡፡

በቅርቡ በተደጋጋሚ እየሰማነው ያለው “ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ መንግሰት” የሚለው ፍልስፍና መሰረቱ አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ የሚባለው የት መጤው የማይታወቅ ፍልስፍና እንደሆነ ቢታመንም አብዮታዊ የሚለውን ትተነዋል ማለት ጀምረዋል የሚል ነው፡፡ ይህ ጥሩ ሽግሽግ ይመስለኛል፡፡ ግልፅ መሆን ያለበት ግን ልማትና ዲሞክራሲ ግቦች ሲሆን እዚያ ለመሄድ የምንከተለው የፖለቲካ ፍልስፍና በግልፅ ነጥሮ መውጣት እና ለህዝብ ይፋ መሆን ይኖርበታል፡፡ እንደ አለመታደል ሆኖ የፖለቲካ ፍልስፍና አባታቸው በህይወት ስለሌሉ ይህ መንገድ ለኢህአዴጋዊያን ግራ ሳይሆን አይቀርም፡፡ አንድ ጓደኛዬ ከኢህአዴግ ሰፈር አዳዲስ ቃላት ጠፍቶዋል ነገሩ ምንድነው ብሎኝ ነበር፡፡ ይህን ነገር ልብ ብላችኋል?

ሌላው በኢህአዴግ ሰፈር ድንገት ከሚመዘዙት ካርዶች አንዱ ህገ መንግሰት መጣስ፣መናድ ወይም አለማክበር የሚለው ነው፡፡ ህገ መንግስቱን እንደ ቅዱስ መፅሃፍ የማይመለከቱ ብዙ ወገኖች አሉ እኔም አንዱ ነኝ፡፡ ምክንያቱም ሊሻሻሉ የሚችሉ ጉዳዮች እንዳሉት ሰለምናምን፡፡ ይህም ህገ መንግስታዊ ስለሆነ ነው፡፡ የህገ መንግሰቱ አንቀፅ 104 እና 105 ህገ መንግሰት እንዴት እንደሚሻሻል የሚገልፁ ድንጋጌዎች ናቸው፡፡ ለዚህም ነው አሁን ባለው ህገ መንግሰት ከምር በማክበርና በማስከበር ረጅም ርቀት ልንሄድ እንችላለን ብለን ገዢውን ፓርቲ እና መንግሰትን ህገመንግስቱን ለማክበር እና ለማስከበር በፅናት እንዲቆሙ የምንሞግተው፡፡ ከዚህ አንፃር የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ህገ መንግሰታዊ ድንጋጌዎችን በማክበር ሚዲያዎቹ የሁሉም ዜጎች የጋራ መጠቀሚያ መድረክ እንዲሆኑ መስራት የሚኖርባቸው፡፡ ይህ ግን በቅረቡ የሚሆን አይመስልም ምክንያቱም የድርጅቱ የቦርድ ስብሳቢ አቶ ሬድዋን በጀመሩት መስመር እንደሚቀጥሉ አበክረው ለምክር ቤቱ ገልፀዋል፡፡

በዚህ አጋጣሚ ስለ አቶ ሬድዋን የቦርድ ስብሳቢነት ስናወራ አንድ የማክያቶ ቡድን አባል የመንግሰት ቦርዶች መብዛት አንስቶ ካጫወተኝ በኋላ ውስጥ ለውስጥ በቦርድ አባልነት ሽኩቻ እንዳለ እና ምክንያቱም ከቦርድ አባልነት ጋር ተያይዞ ከግብር ነፃ የሆነ ከፍተኛ ገቢ እና ሌሎች ጥቅሞች እንዳሉ ገለፀልኝ፡፡ ለነገሩ ሚኒስትሮቻችን በቦርድ አባልነት በሚያገኙት ድጎማ ጭምር እንጂ በመንግሰት በሚከፈል ደሞዝ መኖር እንደማይችሉ ማን ያጣዋል በሚል ወሬው ተቋጭቶዋል፡፡ እሰኪ አንባቢያን የምታውቁትን በቦርድ የሚተዳደር መስሪያ ቤት እና የቦርድ አባላት ጥንቅር የሚከፈላቸውን አበል ጭምር ዘርዘር አድርጉና አስረዱን፣ ስለ ፍትሃዊነቱ ግልፅነት እንዲኖረን ብዬ ነው፡፡

በመጨረሻም አቶ ሬድዋን በሳውዲን ስለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የመንግስታቸውን አቋም የገለፁበት ቁርጥ አቋም ከአንድ ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር የሚጠበቅ ሆኖ አላገኘሁትም፡፡ በህገ ወጥ መንገድ ሳውዲ የገቡትን ዜጎች ህገወጥ ብሎ በስማቸው መጥራት ምንም ችግር እንደ ሌለው ይልቁንም በሌላ ስም ቢጠሩ ወይም ዝም ቢባል ልክ እንዳልሆነ አስረድተውናል፡፡ ይህ ደግሞ የፓርቲያቸውና መንግሰታቸው እውነት መሸፋፈን እንደማይወድ ማሳያ እንጂ ሌላ ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት አስመረውበታል፡፡ በእኔ አረዳድ በመኪና አደጋ ጉዳት የደረሰበትን ሰው በአደጋው ቦታ ተገኝቶ ለምንድነው ግራ ቀኝ አይተህ የማትሻገረው ብሎ እንደማላጋጥ ነው፡፡ በሳውዲ ሀረቢያ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖቻችን አብዛኞቹ ልክ በመሰላቸው መንገድ ከሀገር ስራ ፍለጋ መውጣታቸው የሚካድ አይደለም፣ ይህም በሳውዲ መንግሰት ዕይታ ሕገወጥ ለሆን ይችላል፡፡ የእኛ ሚዲያ በሳዊዲ መንግሰት ጎን ቆሞ ዜጎቹን ህገወጥ እያለ ማሸማቀቅ ተገቢ ነው ብሎዋል፡፡ ስለዚህም በሚዲያ በተደጋጋሚ “ህገ ወጥ” መሆናቸውን መንገር ተገቢና ትክክል ከደረሰባቸው ጉዳት የሚያገግሙት በስማቸው “ህገ ወጥ” ተብለው ሲጠሩ ነው ተብለናል፡፡ ስምተናል!! ግን መስማት መስማማተ አይደለም፡፡

ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅትን እንደ ድርጅት ልሳን እየተጠቀመበት እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም፤ ይህ ደግሞ ኢህአዴግ ከህግ አግባብ ውጭ የያዘውን የፓርቲ ሚዲያ ማለትም ፋና ብሮድካስትን ጨምሮ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉትን ትልልቅ ሚዲያዎች ተቆጣጥሮ ሀገሪቱን የአብዮታዊ ዲሞክራቶች መንደር ለማድረግ ነው፡፡ እርግጠኛ መሆን ያለብን ግን የፈለጉትን ያህል ሚዲያውን ቢቆጣጠሩት የኢትዮጵያ ህዝብ ሌሎች አማራጮችን ተጠቅሞ ከዓለም እኩል ይሆናል እንጂ በእነርሱ መንደር ውስጥ ሲርመጠመጥ አይገኝም፡፡ ይህን የአፈና መረብ ሊበጥሱ የሚችሉ ዜጎች እንደ አሽን እየፈሉ ይገኛሉ …….. ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ ነው፡፡

ኢትዮሚድያ - Ethiomedia.com
January 27, 2014

ለሚመለከተው ሁሉ …..! (አብርሃ ደስታ )

Abraha Desta the facebook


በዓዲግራት ከተማ በደረሰን ድብደባ በጣም አዝኛለሁ። ህወሓቶች በተግባራቸው ሊያዝኑ ይገባል። ህዝብን ፖለቲካ እንዲያውቅና ራሱ ከጭቆና እንዲከላከል ለማገዝ በምንሞክርበት ግዜ መንግስት ወደ ተራ የሽፍትነት ተግባር መሰማራቱ የሚያስደምም ነው። ህወሓት ከሽፍታ በላይ ነው። ምክንያቱም ሁሉም ሽፍቶች ሰለማዊ ሰውን ላይበድሉ ይችላሉና።
አብረሃ ደስታ
እኛ ለህዝብ ነፃነት ነው የምንታገለው። ትግላችን ሰለማዊ ነው። ወታደርና ፖሊስም የለንም። እኛ ያለን ህይወት ነው። ያለችንን ህይወት ለህዝብ ደህንነት ስንል መስዋእት አድርገናል። በህዝብ ፊት ተደብድበናል። በፖሊስና አስተዳዳሪዎች ፊት ተደብድበናል። እኛ መክፈል ያለብን ህይወትን ነው።
የድብደባው ዓላማ (አንድ) ከህዝብ ጋር እንዳንገናኝ፣ (ሁለት) ስንበትነው የነበረው የዓረና አጀንዳ ስሜት ኮርኳሪ ስለነበር፣ (ሦስት) የዓዲግራት ህዝብ ጥሩ አቀባበል ስላደረገልንና ህወሓቶች ስለሰጉ (አራት) እኛ ተስፋ ቆርጠን ቀጣይ ስብሰባዎቻችን እንድንሰርዝ ለማስገደድ ነበር።
ትግሉ ይቀጥላል። ቆርጠን ተነስተናል። ከዓዲግራት ድብደባ የባሰ ሊመጣ አይችልም። በዓዲግራት መስዋእት ሁነናል። የዓዲግራት ድብደባ የትግላችን አስፈላጊነት አረጋግጦልናል።
ተስፋ መቁረጥ የለም። ወደ ኋላ አንድም ኢንች ፍንክች አልልም። በዓዲግራት’ኮ ሙቻለሁ። አልቅሻለሁ። ሐዘኔን ጨርሻለሁ። ሁለተኛ ሞት የለም። ስለዚህ ካሁን በኋላ ሞት የለም። ትግሉ ይቀጥላል። ሰው ሁሉ ለነፃነቱ ይነሳ። ህወሓት ለማንም ሊሆን እንደማይችል አረጋግጠዋል።
(የዓድግራት ድብደባ ዝርዝር ጉዳይ እፅፋለሁ። አሁን ትንሽ ድካም ይሰማኛል)።
ምንጭ፡ ECADF

Sunday, January 26, 2014

የወያኔ የውሸት ዘገባዎች ሲጋለጡ


January 26, 2014
Ginbot 7 weekly editorial
“ኦክስፋም” በመልካም ሥራቸው ከታወቁ ትላልቅ ዓለም ዓቀፍ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አንዱ ነው። በቅርቡ አንድ መቶ ሀያ አምስት አገሮችን ያካተተ ከምግብ አቅርቦትና አጠቃቀም ጋር የተያያዘ ጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል። ጥናቱ አራት ዝርዝርና አንድ አጠቃላይ አመላካቾች አሉት።

1. አመላካች አንድ: የምግብ እጥረት
ይህ አመላካች “በየአገሮቹ ምን ያህል ለበላተኛው የሚበቃ ምግብ አለ?” የሚለውን ይለካል። በጥናቱ ውጤት መሠረት በምግብ እጥረት እጅግ የተጎዱ የመጨረሻዎቹ አስር አገሮች የሚከተሉት ናቸው: – ቡሩንዲ፣ የመን፣ ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ ናይጄሪያ፣ ላኦስ፣ ባንግላዴሽ፣ መካከለኛዉ አፍሪካ ሪፑብሊክ እና ህንድ። ኢትዮጵያ አገራችን ከመጨረሻ አራተኛ ናት።
2. አመላካች ሁለት: ለምግብ የመክፈል አቅም (Affordability)
ይህ አመላካች “የአገሩ ሕዝብ በአገሩ ዋጋ ምግብ ገዝቶ ለመብላት ምን ያህል አቅሙ ይፈቅድለታል?” የሚለውን የሚመልስ ነው። አሁንም ከመጨረሻ እንጀምር። አንጎላ፣ ዚምባቡዌ፣ ቻድ፣ ጉያና፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ኮንጎ፣ ኬንያ፣ ጋምቢያ እና ኢራን የየአገሩ ሕዝብ ምግብ መሸመት የሚቸገሩባቸው አገሮች ናቸው። አገራችን ኢትዮጵያ ከመጨረሻ አምስተኛ ናት።
3. አመላካች ሶስት: የምግብ ጥራት
ይህ የምግብ ይዘትንና የአያያዝ ንጽህናን የሚመለከት ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ሞዛምቢክ፣ ቻድ፣ ቶጎ፣ ዛምቢያ፣ ማሊ፣ ናይጄሪያ፣ ባንግላዴሽ፣ ሌሶቶ ከመጨረሻው እስከ አስረኛ ደረጃ ይዘዋል። ኢትዮጵያ በምግብ ጥራት የመጨረሻዋ አገር ናት።
4. አመላካች አራት፡ የሰውነት ውፍረት እና የስኳር በሽታ
ይህ አመላካች ከልክ ያለፈ ውፍረት ዓለም ዓቀፍ የጤና ችግር እየሆነ በመምጣቱ የገባ አመልካች ነው። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥሩ ውጤት ያመጣችሁ በዚህ አመላካች ብቻ ነው። ኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝቧ ቀጫጫ ነው፤ የስኳር በሽታም እንደሌላው አገር የተስፋፋባት አገር አይደለችም።
5. አማካይ ውጤት
የእነዚህ አራት አመላካቾች ድምር ውጤት አጠቃላይ ውጤትን ይሰጣል። በአጠቃላይ ውጤት: ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ አንጎላ፣ ማዳካስካር፣ የመን፣ ቡሩንዲ ናይጄሪያ፣ ሞዛምቢክ፣ ዚምባቡዌ፣ ሴራሊዮን ከመጨረሻ እስከ አስረኛ ወጥተዋል። ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛ ነች።
ይህ ምንን ያመለክታል?
ወያኔ ባለፉት አስር ዓመታት በተከታታይ ከ11% በላይ ኢኮኖሚውን አሳድጌዋለሁ ሲለን ነበር። እድገቱ ያተኮረው ገጠር፤ ምንጩም ግብርና ነው ብሎን ነበር። ሐቁ ግን ከላይ የተመለከተው ነው።
እርግጥ ነው የወያኔ ሹማምንት በከተሞች ሕንፃዎችን ይገነባሉ፤ በገጠሮች በመቶዎች ሄክታር የሚለካ ለም መሬት ይዘው ፈጣን ገንዘብ በሚያስገኙ የአበባ፣ የጫትና የቃጫ ምርት ላይ ተሰማርተዋል። ከራሳቸውም አልፈው ሀብታም የውጭ አገራት ሸሪኮቻቸውን በአገራችን ለም መሬት ይበልጥ ያበለፅጓቸዋል። የእነሱ የግላቸው፣ የቤተሰቦቻቸው፣ የዘመዶቻቸው እና የሸሪኮቻቸው ኢኮኖሚ እየተመነደገ መሆኑን እናውቃለን። ይህን በገዛ ዓይኖቻችን የምናየው ሀቅ ነው።
ሆኖም ግን የእነሱ ኢኮኖሚ ማደግ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ አለመሆኑ እናውቃለን። አገራችን ከጓረቤት አገሮች ጋር ስትነፃፀር ወደ ኋላ እየቀረች መሆኑ ያንገበግበናል። በቅርቡ አክስፋም በጥናት ያረጋገጠዉ የኢትዮጵያ ገበሬዎች በየቤታቸው ከወዳጆቻቸው ጋር በምስጢር የሚያወሩትን እውነት ነው።
ከሳምንት በፊት ደግሞ “ኢኮኖሚክ ኢንተለጀንስ ዩኒት” የተሰኘው ታዋቂ የምርምር ተቋም አንድ የጥናት ውጤት ይፋ አድርጎ ነበር። በዚህ የጥናት ውጤት መሠረት በዓለም በከፍተኛ ፍጥነት እያደጉ ያሉ አስር አገሮች በቅደም ተከተል ሞንጎሊያ፣ ሴራሊዮን፣ ቱርክሜንስታን፣ ቡታን፣ ሊቢያ፣ ኢራቅ፣ ላኦስ፣ ቲሞር-ሊስቲ፣ ኤርትራ እና ዛምቢያ ናቸው። በዝርዝሩ ውስጥ ኢትዮጵያ አገራችን የለችበትም።
በዓለም አቀፍ መድረኮችም የወያኔ መረጃዎች ውሸትነት እየተጋለጡ መሆናቸው በጎ ምልክት ነው። የሚያሳዝነው ግን ይህንን ሀቅ የሚያዉቁ ምዕራባዉያን ለጋሽ አገሮች አሁንም ወያኔን እየረዱና እየደገፉ ሥቃያችን የሚያራዝሙብን መሆኑ ነው።
ለዚህም ነው ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዘላቂ መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው በአገራችን መሠረዊ የሆነ የአስተዳደር ለውጥ ሲኖር ነው ብሎ የሚያምነው። የወያኔ አገዛዝ በዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እስካልተተካ ድረስ የኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝብ መደህየቱ፤ ጥቂት ሀብታሞች ደግሞ በብዙሀኑ ድህነት መበልፀጋቸው አይቀርም። የወያኔ ውሸቶች ለኢትዮጵያ ድሀ ምግብና መጠለያ አይሆኑለትም። ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ማምጣት የምንችለው ወያኔን አስወግደን በምትኩ ለሕዝብ ሁለተናዊ እድገት የሚጨነቅ መንግሥት መምረጥ ስንችል ብቻ ነው።
ስለሆነም ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በውሸት እድገት እያደናቆረን፤ በተግባር ግን እያደኸየን ያለውን ዘራፊውን ወያኔን አስወግደን በሕዝብ ነፃ ምርጫ የተመረጠ መንግሥት እንዲኖረን ትግላችን እናጠንክር ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Saturday, January 25, 2014

አብረሃ ደስታ በአዲግራት ድብደባ ተፈጸመበት


January 25, 2014
Ethiopian blogger Abraha Desta from Tigry, Mekele
አብረሃ ደስታ
(ECADF) አብረሃ ደስታ ፌስቡክን በመጠቀም ከመቀሌ (ትግራይ) በሚያሰራጫቸው ወቅታዊ መረጃዎች፣ የፖለቲካ ትንታኔዎች እና ዜናዎች በፌስቡክ ተጠቃሚዎች ዘንድ አብዝቶ ይታወቃል። የአረና-ትግራይ ፖለቲካ ፓርቲ አባል እንደመሆኑ ደግሞ የፓርቲውን ወቅታዊ እንቅስቃሴዎች ይዘግባል።
ሰሞኑን እንደተለመደው ዓረና እና መድረክ በዓጋመ (አዲግራት) ጥር 18 ስለሚያካሂዱት ህዝባዊ ስብሰባ እንዲህ በማለት ገልጾ ነበር፣
ዓረና መድረክ ከዓጋመ (ዓዲግራት) ህዝብ ጋር በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ለመወያየት ለእሁድ ጥር 18, 2006 ዓም በዓዲግራት ህዝባዊ አዳራሽ (ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ) ቀጠሮ መያዙ ይታወቃል…
የአብረሃ ቀጣይ ዘገባ እንደሚያመለክተው፣ በተቃዋሚዎች ህዝባዊ ስብሰባ መጥራት የተሸበሩት ህወሀቶች የስብሰባው ቀን ከመድረሱ በፊት እርምጃ መውሰድ መጀመራቸውን ነበር፣
ዓረና ፓርቲ በዓዲግራት ከተማ ለእሁድ ከጠራው ህዝባዊ ስብሰባ ጋር በተያያዘ ዛሬ ዓርብ ሁለት የዓረና አመራር አባላት (አቶ ዓምዶምና መምህር ገብረጨርቆስ) በዕዳጋ ሐሙስ ከተማ ፖሊስ ታስረዋል። የታሰሩበት ምክንያት ህዝብ በስብሰባ እንዲሳተፍ ቀስቅሳችኋል የሚል ነው። ህወሓቶች በተምቤን የፈሩትን ያህል በዓጋመ ፈርተዋል። በተምቤን ተመሳሳይ የእስር ሁኔታ አጋጥሞናል። ስብሰባ ፈቅደው ስለ ስብሰባው ህዝብ እንዳይሰማ ግን ከለከሉ። ይገርማል።
በማግስቱ አብረሃ ደስታ እና ታጋይ ጓደኞቹ በህወሀት ቅጥረኛ ወንጀለኞች፣ በፖሊሶች እና በከተማው አስተዳዳሪዎች ፊት ከፍተኛ ድብደባ ተካሄደባቸው። ሁኔታውን አብረሃ እንዲህ በማለት ገልጾታል፣
We are attacked by TPLF mercenary gangsters in front of administrators and police officers in Adigrat.
ሌሎች መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ አብረሃ ደስታን ጨምሮ አቶ አሰግድ ገብረስላሴ እና አቶ አምዶም ገብረስላሴም ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል፣ ከድብደባው በኋላ ሁሉም ወደ ፖሊስ ጣብያ ተወስደው ምርመራ የተደረገባቸው ሲሆን አቶ አሰግድ እና አቶ አምዶም ህክምና ለማግኘት ወደ ሆስፒታል መሄዳቸው ታውቋል።

Thursday, January 23, 2014

Police Arrest Suspect For Ethiopian Yosef Tulu Murder


 
GARLAND (CBSDFW.COM) – Yesterday 7-11 clerk Yosef Tulu was shot and killed. Today police arrested the teenager who they believe is responsible for the crime caught on tape.
Police arrested 18-year-old Colten Jon Moore without incident.
Officials say a tip received had enough credible information that a search warrant was obtained for a house in the 2900 block of Creek Valley Drive. Moore was arrested at the house that sits, which sits less than one mile from the 7-11 store where Tulu was murdered.
It was in the early morning hours of January 21 when a person wearing a mask and dark-colored jacket walked in to the convenience store at Firewheel Parkway and Pleasant Valley.
Video showed the person, believed now to be Moore, carrying a rifle by his side. The person immediately walked to the clerk and robbed the store. After shooting Tulu the killer walks out of the store carrying a bag. A deliveryman later discovered Tulu’s body.
Moore is being charged with Capital Murder.  His bond has been set at $1,000,000.
Stay tuned for the Suspect's Video

Murder of Ethiopian Yoseph Tulu insane and inhumane says his Family...

Roommate shares reaction on the death of #Ethiopia|n Yoseph Tulu in...