Monday, June 30, 2014

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ


ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም
የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።
ትግላችን መስዋትነት እንደሚያስከፍል እናውቃለን። ከዚህ በፊትም ብዙ ጓዶቻችን መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ ወደፊትም ብዙ መስዋዕትነት መከፈሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። አሁን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰውና ወደፊትም ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ምሬታችን በማብዛት፣ ቁጣችንና ዝግጁነታችን ከማጠንከር በስተቀር ቅንጣት ታክል እንኳን ወደ ኋላ እንድናፈገፍግ እንደማያደርገን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለአባሎቻችንና ለደጋፊዎቻችን ሁሉ መግለጽ እንወዳለን።
መንግሥታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ። ኢትዮጵያና የመን ግን ጎረቤታሞች ሆነው መቆየታቸው የማይቀር ነው። የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም። በዚህም ምክንያት የየመን መንግሥት የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የቆየ ወዳጅነት የሚያደፈርስ እርምጃ ወስዷል። የየመን መንግሥት የየመንን የወደፊት የረዥም ጊዜ ጥቅም እንዲያሰላና ያገተብንን መሪ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንመክራለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመሪያችን ላይ ጉዳት ቢደርስ ወይም ለወያኔ አሳልፎ ቢሰጥ የመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የማይሽር ቂም ውስጥ የምትገባ መሆኑን የየመን መንግሥት አውቆ በጥብቅ እንዲያስብበት እናስጠነቅቃለን።
በየመን መንግሥት አልሰማ ባይነት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ተላልፎ ቢሰጥ በአካሉና በሕይወቱ ለሚደርሰው ሁሉ የወያኔ ፋሽስቶችን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ ከአሁኑ እናስጠነቅቃለን። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስና ሕይወት ላይ የሚደርሰው ማንኛውም ጥቃት ለነፃነታቸው ለመሰዋት ዝግጁ የሚሆኑ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እንደሚፈጥር ጥርጥር የለንም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስ እና ሕይወት ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ሁሉ በማንኛውም መንገድ በማንኛውም ቦታ የምንበቀል መሆኑንና ብዙ የወያኔ ሹማምንት ዋጋ የሚከፍሉበት እንደሚሆን እንዲያውቁት እናስጠነቅቃለን ።
በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ በጁን 29, 2014 መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ

ሔለን ንጉሤ/ ከኖርዌ

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ እ.ኤ.አ በጁን 29, 2014 ከተለያዩ የኖርዌ ከተሞች በመጡና በኦሎ የሚኖሩ በርካታ አባላቶቹ በተገኙበት መደበኛ ስብሰባውን በተሳካ ሁኔታ አከናወነ።

የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በአምባገነኑ የወያኔ ስርዓት  በግፍ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማስደረግ ፕሮግራሙን ያስጀመሩ ሲሆን በመቀጠል የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ዋና ሊ/ቀ መንበር የመግቢያ ንግግር አሰምተዋል። በንግግራቸውም የድርጅቱን አመሰራረትና አላማውን ጨምረው በዝርዝር በማስረዳት የድርጅቱ አላማ የጋራ ሰላምና መግባባት ቀናነት ያለበት መሆኑን በመጠቆም የምንታገልለትን ሀገራዊ ራዕይ ለማስፈፀምና የተጫነብንን የድህነት ቀንበር ለመስበር የምንችለው አንድ ሆነን ስንታገል ብቻ መሆኑ በማስገንዘብ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ለአባላቱ አቅርበዋል። ቀጥሎም የድርጅቱ ዋና ፀኃፊ የድርጅቱን አጠቃላይ የስድስት ወራት የሥራ ክንውን ሪፓርት በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ለፍትህ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ከሚታገሉ በውጪ ካሉ ድርጅቶች ግንባር ቀደም መሆኑንም ጠቁመዋል።

በመቀጠል የድርጅት ጉዳይ ኃላፊው የስድስት ወር ሪፓርታቸውን በዝርዝር ሲያቀርቡ በእቅድ የተያዙና የተከናወኑ ስራዎችን እንዲሁም በስራ ላይ ያጋጠሙ ችግሮችንና መፍትሄዎቻቸውን ጨምረው አስረድተዋል። በተለይ ቅርንጫፎችን በማስፋት የአባላት ምልመላን በተመለከተም ከእቅድ በላይ አባላትን መመልመል እንደተቻለ ተናግረዋል። በድርጅት ጉዳይ ስር የተዋቀሩ ንዑሳን ኮሚቴዎችም ያከናወኑትን ስራ በሪፓርታቸው አካተዋል። ባጠቃላይ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊው የተሰሩ ስራዎችን በምስል በማስደገፍ በፓወርፓይንት ሰፋ ያለ ማብራሪያ ለአባላቱ በማቅረብ የንዑሳን ኮሜቴና ከየቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ የመጡ ተወካዮችንም በመጋበዝ እራሳቸውን ለአባላት እንዲያስተዋውቁና ወደፊት ለመስራት ያሰቧቸውን ስራዎች በአጭሩ እንዲያስረዱ  አድርገዋል።
ከዚያም የድርጅቱ የሂሳብ ሪፓርት በሂሳብ ሹሟ የቀረበ ሲሆን በድርጅቱ ኦዲት ክፍልም የኦዲት ሪፓርት ቀርቧል። ከዚያም የምንደግፋቸውን ድርጅቶች አስመልክቶ በድርጅቱ የተወከሉ የድርጅቱ አባላት የሰማያዊ ፓርቲን፣ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን እንዲሁም የግንቦት7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄን የገመገሙበትን ሪፓርት በየተራ ለአባላቱ ያቀረቡ ሲሆን አባላቱም ሪፓርቱን ካደመጡና ከተወያዩ በኋላ በቀጣይ ሶስቱንም ድርጅቶች ለመደገፍ መስማማታቸውን ገልፀዋል።

በስብሰባው መሀል የሰማያዊ ፓርቲ ሊ/መንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በስልክ በመግባት ሰማያዊ ፓርቲ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ሐገር በሰላማዊ መንገድ ትግሉን ከሚያግዙ ድርጅቶች ጋር ትኩረት በመስጠት እየሰራ መሆኑንና ከዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ጋር ስራ ለመስራት በፓርቲው በኩል ህጋዊ ውክልና ለድርጅቱ መስጠታቸውን ገልፀው በተጨማሪ የሰማያዊ ፓርቲ ባዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ እለት ከዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ የገንዘብ ልገሳ እንደተደረገላቸው አረጋግጠዋል። ኢንጅነሩ ሲናገሩ በቀጣይም ትግሉን ወደፊት የሚያራምድ ስራ በጋራ እንዲሰራና ትግል ብዙ መስዋእትነት የሚጠይቅ መውደቅ መነሳት ያለበት እልህ አስጨራሽ በመሆኑ ጠንክረን በጋራ እንድንሰራ ጥሪያቸውን በማቅረብ መልክታቸውን
አስተላልፈዋል።


በመቀጠል የአባላት የውይይት ተደርጎ የድርጅቱ ሊቀመንበር የውይይት ጊዜውን በመምራት ከአባላት የተነሱ ጥያቄዎችን በተገቢው መንገድ ምላሽ በመስጠት የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችንም ከአባላት ተቀብለዋል። በመጨረሻም የድርጅቱ ም/ሊቀመንበር የመዝጊያ ንግግር አሰምተው ስብሰባው በተያዘለት ሰዓት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

መዝገቦቹ መልሰው ተቀራረቡ የእምነት ክህደት ቃል በኃይል አስፈርመዋቸዋል


Tsion Girma's photo.ጽዮን ግርማ
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በስድስቱ ጦማሪያንና በሦስቱን ጋዜጠኞች ላይ የፌደራል ፖሊስ የተለያየ ምክንያት እየሰጠ ቀጠሮ የሚያራዝመውን ሁለት መዝገብ አንዴ ሲያቀራርበው መልሶ ደግሞ ሲያራርቀው ቆይቶ አሁን ደግሞ መዝገቦቹን መልሶ አቀራርቧቸዋል፡፡እስረኞቹ ራሳቸውን መከላከል በማይችሉበት ኹኔታ ፖሊስ ያረቀቀውን የእምነት ክህድት ቃል ተገደው እንዲፈርሙ አድርጓቸዋል፡፡

የሦስቱ ብሎገሮች አቤል ዋበላ፣በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን ቀጠሮ ለዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲቀርቡ የሚል የነበረ ሲኾን ከጠዋት ጀምሮ ችሎቱን ለመታደም የመጣውን ቤተሰብ፣ጓደኞቻቸው፣ጋዜጠኞች፣ዲፕሎማቶችና የወጣቶች ደጋፊዎች በአጠቃላይ ወደ ሦስት መቶ የሚጠጋ ሰው ከችሎት ውስጥ የሚሰማውን አዲስ ነገር ለመጠበቅ በግቢው ውስጥ ቆመው ነበር፡፡ ከጠዋቱ አራት ሰዓት አካባቢ የእስረኞቹ ጠበቃ አቶ አመኃ መኮንን ተጠርተው የመዝግብ ቤት ጸሐፊዋ ስለሌለች ችሎቱ ለከሰዓት በኋላ እንደተዛወረ ይነገራቸዋል፡፡ እርሳቸውም ችሎቱን ለመከታተል ለቆመው ሰው መልዕክቱን ያስተላልፋሉ፡፡ ጥቂት ሰዎችም ይህን መልዕክት ሰምተው ግቢውን ለቀው ይወጣሉ ብዙኃኑ ግን እዛው እንደቆሙ መጨረሻውን ለማየት መጠባበቅ ይጀምራሉ፡፡

ሠላሳ ደቂቃ ያህል እንደተቆጠረ የእስረኞቹ መምጣት በጉምጉምታ መወራት ጀመረ፡፡ሁሉም ሰው ወደ ጓሮው በር ዐይኑን ተክሎ ቀረ፡፡ አቤል ዋበላ፣በፍቃዱ ኃይሉ እጃቸውን በሰንሰለት እንደታሰሩ ማኅሌት ፋንታሁ ከካቴና ውጪ ኾና እንደተለመደው በከፍተኛ የፖሊስ ጥበቃ ታጅበው ወደ ፍርድ ቤት ግቢ ውስጥ ዘለቁ፡፡ ወጣቶቹ ወደ ግቢው ፊታቸው ላይ የጥንካሬ መንፈስ የነበረ ሲኾን ተሰበሰበውም ሕዝብ በጭብጨባ ነበር የተቀበላቸው፡፡በዚህ መካከል እስረኞቹን አጅበው የመጡት ፖሊሶች ወደተሰበሰበው ሰው ዘለው በመግባት ፎቶ ስታነሳ ነበር ያሏትን ምኞት መኮንንን (የሰማያዊው ፓርቲ አባል) የተባለች ወጣት የያዘችውን ስልክ ቀምተው እየጎተቱ ወሰዷት፡፡ፖሊሶች በወጣቷ ላይ የሚፈጽሙት ማንገላት ያስቆጣው ዮናታን ተስፋዬ የተባለ ሌላ ወጣት ድርጊቱን በማውገዝ ለመገላገል ሲጠጋ እርሱንም ጨምረው ወስደውታል፡፡

ፍርድ ቤቱ ይህን ችሎት ማየት ከጀመረ ወዲህ እስረኞቹን አጅበው የሚመጡት ፖሊሶች ቀጠሮ ባለ ቀን ሁሉ ችሎት ለመከታተል የሚመጣውን ሰው ሲያንገላቱ፣ሲሰድቡና ሲዘልፉ ልክ እንደ መብታቸው የሚቆጥሩት ሲኾን እዛ ግቢው ውስጥ የተገኘው ሰው ችሎት ውስጥ ገብቶ በሚገባ መቀመጫ ቦታ ተሰጥቶት ችሎት የመከታተል መብት እንዳለው ቅንጣት ታክል አስበውት የሚያውቁ አይመስል፡፡ እንዲኹም ከችሎቱ ውጪ ፍርድ ቤት ግቢ ውስጥም ቢኾን ‹‹ፎቶ ማንሳት ክልክል ነው›› የሚል ማስጠንቀቂያ እስካልተለጠፈ ድረስ ከሁለት ሰው በላይ የኾነ ማንም ሰው የተሰበሰበበት ቦታ ላይ ፎቶ የማንሳት ሙሉ መብት እንዳለ የሚያውቁ አይመስሉም፡፡ በአጠቃላይ በዛ ቦታ ላይ ከእነርሱ ውጪ ሌላ ሰው የመቆም መብት ጭምር እንደሌለው ጠንቅቀው ስሚያውቁ ወደ ተሰበሰበው ሰው ተመልሰው፤‹‹ሁላችሁም ግቢውን ለቃችሁ ውጡ›› ሲሉ ትእዛዝ ሰጡ፡፡

ከፊት ለፊት ቆመው የነበሩት ሰዎች ከግቢው ላለመውጣት እንቢተኝነታቸውን አሳዩ፡፡በተለይ በእስር ላይ የምትገኛው ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ እህት እስከዳር ዓለሙ፣አባቷ አቶ ዓለሙ እና ሌሎች ወጣቶች አንድ ላይ ኾነው ግቢ ውስጥ መቆም መብት እንዳላቸው በመግለጽ ለመውጣት ፍቃደኛ ሳይኾኑ ቀሩ፡፡ የፖሊሶቹ ማስፈራሪያና ዘለፋ ግን ቀጠለ ሕዝቡ ግቢውን ለቆ የማይወጣ ከኾነ አድማ በታኝ ፖሊስ እንደሚጠሩ ጭምር በመግለጽ ማስፈራራት ቀጠሉ፡፡ፎቶ ማንሳት የተከለከለ እንደኾነ እና እንኳን ሰውን መሬቱንም ጭምር ማንሳት እንደማይቻል በማስፈራራት ጭምር በመግለጽ ሰውን ከግቢው ውስጥ ገፍተው ወደ ውች አስወጡት፡፡

ግንቦት ዘጠኝ ቀን 2006 ዓ.ም ውሎ በነበረውና ከዚያም ቀጥሎ በነበረው ችሎት ላይ እያንዳንዱ ተጠርጣሪ የወከለው ቤተሰብ አባል ወደ ችሎት እዲገባለት ተደርጎ የነበረ ሲኾን አሁን ግን ይህም መብት ተከልክሎ ችሎት ውስጥ በእስረኞቹ በኩል ከጠበቃቸው ከአቶ አመሐ መኮንን በስተቀር ማንም ችሎት ሳይገባ ቀርቷል፡፡ችሎት ከገቡም በኋላ ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተጠማሪ ሃያ ስምንት ቀን እንዲፈቀድለት የጠየቀ ሲኾን ፍርድ ቤቱ፤‹‹ከዚህ በኋላ የሚሰጣችሁ ሃያ ስምንት ቀን የለም ዐሥራ አራት ቀን ይበቃችኋል፡፡ ችሎቱም ከዚህ በኋላ እሁድ ስለማይሰየም ቀኑ አንድ ቀን ተቀይሮ ሰኞ ሐምሎ 7 ቀን 2006 ዓ.ም›› ሲል ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

የጊዜ ቀጠሮው መዝገብ ሲከፈት የአቤል ዋበላ፣በፍቃዱ ኃይሉና የማኅሌት ፋንታሁንን ጉዳይ የያዘው መዝገብ ከሌሎቹ ከስድስቱ አስረኞች ጋራ በአንድ ቀን ይለያይ የነበረ ሲኾን በመካከሉ አንዲት ዳኛ የሃያ ስምንት ቀን ጥያቄውን ባለመቀበላቸው ጉዳዩ በዐሥራ አምስት ቀን ተለያይቶ እንደነበር ይታወሳል አሁን ደግሞ መዝገቦቹ መልሰው ተቀራርበዋል፡፡ የስድስቱ ቅዳሜ ሐምሌ 5 ቀን ይታያል የሦስቱ ደግሞ ሰኞ ሐምሌ ሰባት ቀን፡፡

በዛሬው ቀጠሮ በፍቃዱ ኃይሉ ያላመነበትን የእምነት ክህደት በኃይል እንዲፈርም መገደዱን ተናግሯል፡፡ እንደምንጮች ገለጻ ከኾነ አብዛኞቹን እስረኞች በከፍተኛ ጫናና በድብደባ በመርማሪ ፖሊሶች የተረቀቀውንና በእነርሱ ሐሳብ የተዘጋጀ የእምነት ክህደት ቃል ላይ ‹‹የሰጠሁት ቃል የኔ ነው ጥፋተኛ ነኝ›› ብለው እንዲፈርሙ ተደርጓል፡፡

የፍርድ ቤቱ መዝገቡን ማጠጋጋትና የእምነት ክህደት ቃሉ ፊርማ እስረኞቹን ለመክሰስ ዝግጅቱ መጠናቀቁን ማሳያዎች በሚል በሕግ ባለሞያዎች ተገምቷል፡፡

Sunday, June 29, 2014

ኢትዮጵያዊው-ኖርዌጂያን ኦኬሎ ኦካይ ኦቻላ ”ሞት ሊበየንበት ይችላል” -በሽብርተኝነት ክስ ሞት ተፈርዶባቸው ሞታቸውን የሚጠባበቁ 127 ሰዎች ኣሉ


በኖርዌይ ሃገር ውስጥ በኖርዌጂያንኛ የሚታተመው ዳግብላደት የተባለው ጋዜጣና ድረ-ገጽ ”ኢትዮጵያዊው-ኖርዌጂያን” ኦኬሎ ኦካይ ኦቻላ በሚቀጥለው ሳምንት ሞት ሊበየንበት ይችላል” ሲል ኣውጥቶኣል።

”ባለፈው ሳምንት ለማወቅ እንደተቻለው ዕድሜው 52  የሆነና  ኦኬሎ ኦካይ ኦቻ  የተባለ ኖርዌጂያን ኢትዮጵያ ውስጥ በሽብርተኝነት ተከሶ በእስር ላይ ይገኛል።” tiltalt for terror በማለት የጀመረው የኖርዌዩ ዳግብላደት ሲቀጥልም…”የኢትዮጵያ መንግስት ቃለ ኣቀባይ እንደሚለው ገንዘብ ኣሰባስቦና ኣጥቂ ቡድን መልምሎ ኣደጋ ለማድረስ ሲሞክር ያዝነው በማለት መከሰሱን ያትትና በበኩላቸው የኖርዌዩ የሰብኣዊ መብት ጥበቃም ሆኑ የዓለም ኣቀፉ ሰብኣዊ መብት ተሟጋቾች ድርጊቱን በጥብቅ ያወገዙት ሲሆን፣ ኣያይዘውም ለዚሁ ድረ-ገጽ ታሳሪው ግለሰብ ያለበት ሁኔታ ከወትሮው የከፋ እንደሆነም ስጋታቸውን እንደገለጹለት ያወሳል።

 ኢትዮጵያንም ሆነ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት፣ በኣሁኑ ወቅት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ውስጥ የሚገኙትን  ኦኬሎ ኦካይ ኦቻ ”በሚገባ ያውቃሉ” ያሉዋቸውን የሰብኣዊ መብት ተሟጋችና ኖርዌጂያን ፈሊክስ ሆርነ ን  ኣነጋግሮ ድረ-ገጹ ያገኘው መልስ ”ኖርዌጂያኑን ኦኬሎ በሚቀጥለው ሳምንት የሚሰየመው ችሎት ሞት ሊበይንበት ይችላል” በማለት የገለጹ ሲሆን ኣክለውም፣
”በሃገሪቷ ውስጥ በሽብር ወንጀል የሚከሰሱት ዜጎች የሚገጥማቸው የሞት ፍርድ ነው። ነገር ግን እነዚህ ሞት የሚፈረድባቸው ዜጎች ምንም ማስረጃ ያልቀረበባቸው ናቸው። በሽብር ክስ ስለተከሰሱ ብቻ ዕድላቸው ይሄው ነው። በሞት ቀጠና የሚገኙትን ዜጎች የሚዘግበው ዓለም ኣቀፉ ድርጅት በኢትዮጵያ በእስር ቤት ውስጥ በሞት ቀጠና (ሴል) የሚሰቀሉበትን ወይም የሚገደሉበትን ጊዜ የሚጠባበቁ 127  ዜጎች  ይገኛሉ ሲል ፈሊክስ ሆርነ ለድረ- ገጹ ገልጸዋል።
 ሌላው ኣምነስቲ ኢንተርናሽናል ውስጥ የሚሰሩት ጌራልድ ካዶርድ ”የኢትዮጵያ መንግስት ኦኬሎን እንደከሰሰው በሽብር ወንጀል ጦር ሲመለምልና ሲያደራጅ ኣግኝቶት ከሆነ፣ የሞት ቅጣት ይበይኑበታል የሚለው ስጋቴ ነው።የፍርድ ሂደቱን እንደምናየው የሞት ቅጣቱ በፍርድ ቤቱ ይለወጣል የሚል ዋስትና የለንም።” ኣያይዘውም ባለፈው ዓመት 8 ጋምቤላ ውስጥ ያሉ የተቃዋሚ ድርጅት ኣባላቶች በሽብርተኝነት ከሰዋቸውና የሞት ፍርድ በይነውባቸው ሞታቸውን በመጠባበቅ ላይ ናቸው።”
 ጭፍጨፋ
ኦቻላ ከሽብርተኛ ጋር ግንኙነት እንዳለው ኣላውቅም። ነገር ግን በጋምቤላ ውስጥ መንግስትን የሚቃወም ጠንካራ ተቃዋሚ ድርጅት የለም። መንግስትን ለመቃወም የሚነሱትንም ሽብርተኛ የሚል ስም በክልሉ መንግስት ይለጠፍባቸዋል።
 ኦቻላ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት የነበረ ጊዜ፣ massakre 13. desember 2003. የ 1000 በላይ  የኣባወራዎች መኖሪያ ቤቶች በገዥው ስርዓት ወታደሮች ሲቃጠልና ከ400 የኣኙዋክ ንጹሃን ተወላጆች በጥይትና በስለት ሲታረዱ በስፍራው  ነበር። ይሄንንም ተከትሎ ወደ ደቡብ ሱዳን ስልጣኑን በመተው መሰደዱንና ከዚያም ከቤተሰቡ ጋር  በኖርዌይ ”ትሮንዳሄም” በተባለ ቦታ  በስደተኝነት በመግባትና ፈቃድ ጠይቆ በ2009 ዓ.ም የኖርዌጂያን ዜግነት ተሰጥቶት ነበር።

  ቢሆንም  ከ 2012 ጀምሮ በጋምቤላ ውስጥ በሚከናወነው ሁኔታዎች ይረበሽ ነበር። በዚህም የተነሳ ወደዚያው ኣቅንቶኣል።ማድረግ ግን ኣልነበረበትም።በኣንድ ወቅት በክረምት ወራት የሱዳን የመረጃና ደህንነት ሰራተኞች በሱዳን ጁባ ውስጥ ያለን ኣንድ ሆቴል በድንገት ከበቡት። ከዚያም በውስጡ የነበሩትን የሱን ጓደኞች  ኣስረዋቸው ወደ ኢትዮጵያ  ልከዋቸዋል በማለት ድረ- ገጹ ኣትቶኣል።

ቶርቸር 

በኣሁኑ ሰዓት ኦኬሎ በእስር ቤት ውስጥ ባልተረጋገጠ መረጃ ውስጥ ይገኛል። ይህ ኖርዌጂያን በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ማወቅ ኣይቻልም። በኢትዮጵያ ውስጥ በሽብርተኝነት በእስር ቤት ውስጥ ሆኖ  የእናትነት እንክብካቤን ማግኘት ህልም ነው። እስረኞች ለቶርቸርና ስቃይ የተጋለጡ  መሆናቸውን ፈሊክስ ሆርነ  ለድረ-ገጹ ኣስረድተዋል።

የኦኬሎን የፍርድ ሁኔታ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኘው ሪፖርተር የተሰኘው  ጋዜጣ ችሎቱ  ጁላይ 1 ይውላል ብሎ ቢገልጽም፣ የእኛ Dagbaldet በሲዊድን ያለውን የኢትዮጵያ ኣምባሳደር ለማግኘት ሞክረን ያልተሳካልን ሲሆን፤ ዓለም ኣቀፉን የሰብ ኣዊ መብት ተሟጋች ድርጅትንም ሆነ በኣዲስ ኣበባ ካለውም የኖርዌይ ኤምባሲ ትክክለኛ የችሎት ጊዜውን ማረጋገጥ ኣልተቻለም።
የኖርዌይ የውጭ ጉዳይም ለኣንድ ኣዲስ ኖርዌጂያን በኣደጋ ውስጥ በሚሆንበት ጊዜ፣ ወይም ኣደጋ በገጠመው ወቅት እንዴት መከላከል  እንዳለበት ከድረ- ገጹ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ መስጠት ኣልፈለጉም። ድረ- ገጹ   ምላሽ በማጣቱም ይመስላል በኮንጎ ውስጥ ኖርዌጂያዊው Joshua French  በሞት ሲቀጣና፣  Shahid Azim  በኣስገድዶ መድፈር ወንጀል ፖኪስታን ውስጥ ተይዞ ሞት ሲፈረድበትም ኣላስጣሉትም በሚል ኣጣቅሰው ያለፉት። ቢሆንም ይላሉ የውጭ ጉዳይ ቃል ኣቀባይ ፍሮደ ኣንደርሰን፥ እስከኣሁን ከተከሳሹ ስለ ፍርድ ውሳኔውንም  ሆነ  ስለ ችሎቱ ቀን የምናውቀው የለም በማለት ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ያለው የኖርዌይ ኣምባሳደር  ኦኬሎ ኦካይ ኦቻላን በተመለከተ ተደጋጋሚ  ጥያቄዎችን ለኢትዮጵያ መንግስት ኣቅርቦኣል። ኦኬሎ ያለበትን ሁኔታ፣ የፍርድ ሂደቱን ለመከታተልና በእስር ቤት ለመጎብኘት፣ ቢሆንም  ከኢትዮጵያ መንግስት ምንም  ምላሽ  ኣልተገኘም። የኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ሁኔታውን በኣደገኛነት እንደሚያዩትም ሳይገልጹ ኣላለፉም።
ባለፈው ሳምንት 
የኦኬሎ ባለቤት ኦባ ኦድዋ ኦመት kona Obo Adwo Omot fram i Dagbladet  ”… ባለቤቴ ሽብርተኛ ሳይሆን የፖለቲካ እስረኛ ነው” በማለት ገልጻ ነበር። ይህችው የ ኣራት ልጆች እናት የሆነችው ባለቤቱ ባለፈው ሳምንት እንደገለጸችው፣ ”…በኣሁኑ ሰዓት በዚህ ጠባብ ክፍል ከኣራት ልጆቼ ጋር እገኛለሁ። ምንም የማውቀው ነገር የለም። ባለቤቴም የሚያውቀው ነገር የለም። የኖርዌይ መንግስት የተቻለውን ሁሉ ኣድርጎ ባለቤቴን ከእስር እንዲያስወጡልኝ እማጸናለሁ በማለት ነበር የገለጸችው።

Friday, June 27, 2014

ህወሓቶች የመቐለን ሰለማዊ ሰልፍ ለመከልከል ወስነዋል።

ትናንት ሐሙስ ማታ (ከምሽቱ 4:30) አንድ የህወሓት ባለስልጣን ደውሎ እንደነገረኝ ከሆነ ህወሓቶች የመቐለን ሰለማዊ ሰልፍ ለመከልከል ወስነዋል። ትናንት ማታ አስቸኳይ ስብሰባ የተጠራው “ሰልፉ በመቐለ እንዳይካሄድ፣ እንዳታዋርዱን፣ የህዝቡን ስሜት መረዳት እንዴት ያቅታችኋል? ነገሮች ሳይበላሹ ሰልፉ በሆነ ምክንያት እንዲቀር አድርጉ! ተብሎ ተደውሎልናል” ብሎ ነገረኝ። ማን ለማን ነው የሚደውልለት? አልነገረኝም። ግን ከአዲስ አበባዎቹ ይሆናል ብለን እንገምት።
ህወሓት ሰልፉን ለመከልከል ወስኖ ከሆነ በጣም የሚያሳፍር ተግባር ነው። ከመጠን በላይ ፈርቷል ማለት ነው። የመቐለ ህዝብ ሰልፍ የማድረግ መብቱ ተነፈገ ማለት ነው። ድሮምውም ኮ የህዝብ ስሜት የሚያጤኑ የደህንነት ሰዎች በዝተዋል። ህዝቡ እንደሚሰለፍ ስለተረዱ ይሆናል። መረጃው ትክክል ከሆነ በቃ የትግራይ ህዝብ ሰለማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት የለውም ማለት ነው።
ግን ሰልፉን መከልከላቸው በደብዳቤ እስኪያሳውቁን ድረስ ሰልፉ እንደሚካሄድ ነው ታሳቢ የምናደርገው። ዉሳኔው ትክክል ስለመሆኑ የሚያረጋግጥ ደብዳቤ ያስፈልገናል። እውነት ግን ሰልፉ አይደረግም ብለው ደብዳቤ ሊሰጡን? አላምንም። ደብዳቤ ካልሰጡን ደግሞ ሰልፉ ይደረጋል። ስለዚህ እናያለን።
ደብዳቤው ከሰጡን ለሰልፉ መከለክል ምክንያቶች ለማወቅ ጓጉቻለሁ።
አብርሃ ደስታ/ከመቀሌ

Wednesday, June 18, 2014

‹‹ይህ ሽልማት የእኔ ብቻ አይደለም፣ የእናንተም ነው›› እስክንድር ነጋ

በኤልያስ ገብሩ ጎዳና

ይህ ሽልማት የኔ ብቻ አይደለም የእናንተም ነው። 
በእስር ላይ የምትገኙ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖች የኔ ጀግኖች ናችሁ
እስክንድር ነጋ

አሁን ደስተኛ ነኝ
እስክንድርን ምግብ ማብሰል እያለማመድኩት ነው
አቶ አንዱአለም አራጌ

ከትናንት በስትያ ሰኔ 03 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ከቅርብ ጓደኛዬ እና የሙያ ባልደረባዬ ጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ ጋር ወደቃሊቲ ማረሚያ ቤት [እስር ቤትም ነው] አምርተን ነበር- ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆኑትን አቶ አንዷለም አራጌን ለመጠየቅ፡፡ የተለመደውን የፖሊስ ፍተሻ አልፈን ወደ ውስጥ ስንዘልቅ የሰማያዊ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፈ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ፣ አቶ ሳሙኤል የተባሉ አባልና የ‹‹ነገረ ኢትዮጵያ›› ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው እስክንድርን ሊጠይቁ ቀድመውን ደርሰው ነበር፡፡
Ethiopian political prisoners Eskinder Nega and Andualem Arage
…እስክንድርን እና አንዷለምን አስጠራናቸው፡፡ ሁለቱም ሲያዩን ደስ አላቸው፡፡ በተለይ በተለይ የእስክንድር ፈገግታ በጣም ደማቅ ነበር፡፡ ተከፋፍለን ከሁለቱም ጋር ሃሳቦችን መለዋወጥ ጀመርን፡፡
እስክንድር በዓለም የጋዜጠኞች እና የዜና አታሚዎች ማኅበር የዓመቱ የወርቅ ብዕር የ “pen Golden of freedom 2014″ ተሸላሚ በመሆኑ ‹‹እንኳን ደስ ያለህ›› አልኩት፡፡ ‹‹አመሰግናለሁ፡፡ ትናንት አንድ ልጅ ሊጠይኝ መጥቶ ነግሮኛል›› ካለን በኋላ ደግመን ስለሽልማቱ በጋራ ሃሳብ መለዋወጥ ቀጠልን፡፡ እስክንድር ሽልማቱ አዲስ መሆኑን አላወቀም ነበር፡፡
በመሆኑም ስለሽልማቱ ሁኔታ፣ ማን እንደሸለመው፣ ሽልማቱ የት እንደተደረገ፣ ሽልማቱን ማን እንደተቀበለለት [ሽልማቱን የተቀበለው በኢትዮጵያ በሽብርተኝነት ክስ ወንጀለኛ ተብሎ ከባልደረባው ፎቶ አንሺ ጋር 11 ዓመታት ከተፈረደበት በኋላ በይቅርታ የተለቀቀው ስዊድናዊ ጋዜጠኛ ማርቲን ሽብዬ ነበር]፣ የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ምን እንደሚመሰል፣ በሽልማቱ እነማን እንደተገኙ …ያወቅነውን ሁሉ ነገርነው፡፡
‹‹ይህንን አላዋኩኝም፣ ሰርካለም (ባለቤቱ) ለምን በቦታው አልተገኘችም?›› በማለት ጠየቀንና በድጋሚ ደስ ብሎት ጣቶቹን በሽቦ ውስጥ አሾልኮ ጨበጠን፡፡ ወዲያው ይህቺን መልዕክት ተናገረ፡-
‹‹ይህ ሽልማት የእኔ ብቻ አይደለም፡፡ የእናንተም ነው፡፡ የኢትዮጵያዊ ጋዜጠኞች ነው፡፡ ሁላችንንም ይመለከተናል፡፡ ለሁላንችም ይገባናል፡፡ ይሄንን ሽልማት የምመለከተው ሐሳብን በነጻነት ከመግለጽ የመብት ጥሰት አኳያ ብቻ አይደለም፡፡ ለሌሎች የዜጎች መብቶች ሲሉ ለታገሉ እና እየታገሉ ላሉ ፖለቲከኞች፣ የሕሊና እስረኞችም ጭምር ነው፡፡ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ከሌሎች ከተነፈጉ መብቶች ተለይቶ የሚታይ አይደለም፡፡ ሁሉንም መብቶች እናገኛቸዋለን፣ ወይም እናጣቸዋለን፡፡ ለዚህ ደግሞ ጸንተን እንታገል፣ ትግላችን ግን ሰላማዊ ብቻ መሆን አለበት፡፡ …››
እስክንድር ደስ ብሎት ሃሳቡን መናገሩን ቀጥሏል፡፡ እኔ ለተወሰኑ ቀናት በማዕከላዊ መታሰሬን ሰምቶ ስለነበረም ‹‹ማዕከላዊ እያለህ የታሰሩትን ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖች ለማግኘት ችለህ ነበር?›› ብሎ ጠየቀኝ፡፡ እነሱን በአካል ማግኘት አለመቻሌን ነገር ግን ከእነሱ ጋር ታሥረው የነበሩ ሌሎች ተጠርጣሪ ዜጎችን አግኝቼ በእስር ስላሉበት ሁኔታ መጠየቄን ነገርኩት፡፡
የታሰሩት ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖችን ቤተሰብ ማግኘት እችል እንደሆነና ከቻልኩም በእነሱ በኩል መልዕክቱ ይደርስለት ዘንድ በድጋሚ ጥያቄያዊ ሃሳቡን አቀረበልኝ፡፡ የተወሰኑ የእስረኛ ቤተሰቦችን ማግኘት እንደምችል አስረዳሁት፡፡
‹‹የታሰራችሁ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖች የእኔ ጀግኖች ናችሁ፡፡ አከብራችኋላሁ፡፡›› ብለህ ንገርልኝ አለኝ – ደጋግሞ፡፡ …
በዕለቱ ከሰዓታት በፊት ሰናይት ታከለ የምትባል ወዳጄም እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ እንደምሄድ በነገርኳት ጊዜ ‹‹እንደማከብረው እና እንደማደንቀው ንገርልኝ›› ያለችኝን መልዕክት ለእስክንድር አደረስኩላት፡፡
እሱ ግን ሳቅ እያለ ‹‹ተሳስተሻል! …ተሳስተሻል! …ተሳስተሻል›› ብለህ ንገራት አለኝ፡፡ ‹‹ለምን?›› አልኩት፡፡ ‹‹ገና ምን ሰርቼ?›› በማለት በዚያ ትሁት አንደበቱ መለሰልኝ፡፡ በእውነት መልሱ አስደመመን፡፡ ዋይ እስክንድር፣ ፍጹም የተለየ ታላቅ ሰው!!!
እስክንድርን እናናግረው የነበርን ጠያቂዎች ወደ አንዷለም አራጌ ዞርን፡፡ አንዷለም ጋር የነበሩት ደግሞ ወደ እስክንድር፡፡
አንዷለም የስፖርት ቲ-ሸርት ከቁምጣ ጋር ለብሷል፡፡ ጥቁር መነጽር አድርጓል፡፡ ረጋ ብሎ ፈገግ በማለት ‹‹ምን አዲስ ነገር አለ?›› በማለት ጨዋታ ጀመረ፡፡ አንዷለም የእስክንድርን ሽልማት ሰምቶ ኖሮ፣ ‹‹አሁን ከምሳ በኋላ ጣፋጭ የለውዝ ሻይ እሱን እና ጓደኞቻችንን በመጋበዝ ‹እንኳን ደስ ያልህ!› በማለት ሰርፕራይዝ አደርገዋለሁ፡፡ ምግብ ማብሰል እያለማመድኩት ነው፡፡ ብዙ ጊዜ እኔ ነኝ ሰርቼ የማበላው፡፡ በልጅነቱ በበርገር ያደገ ልጅ አሁን ሽንኩርት እና ቲማቲም መክተፍ ችሏል …›› በማለት በቀልድ ነገረን፡፡
‹እነማን ከእናንተ ጋር አሉ? በአንድ ክፍል ውስጥስ ስንት ናችሁ? ጊዜያችሁንስ እንዴት ነው የምትጠቀሙበት?›› የሚል ጥያቄ አቀረብንለት፡፡
‹‹ለረዥም ጊዜ፣ በጣም አስቸጋሪ ክፍል ውስጥ፣ መሬት ላይ ስንከባለል ነበር በእስር ያሳለፍሉት፡፡ አሁን አቶ ስዬ አብርሃ ታስሮ በነበረበት ጥሩ በሚባል ክፍል ውስጥ ለአምስት ታስረን እንገኛለን፡፡ አቶ መላኩ ተፈራ፣ አቶ መላኩ ፈንታ ና አንድ ባለሃብት አብረውን ናቸው፡፡ አሁን አልጋ ላይ መተኛት ጀምሬአለሁ፡፡ ይሄ ለእኔ እንደ አዲስ ሕይወት ነው፡፡ አሁን ደስተኛ ነኝ፡፡ …ጊዜያችንን በጥሩ ሁኔታ ከፋፍለን እየተጠቀምንበት ነው፡፡ እናነባለን፣ እንወያያለን፣ የምንፈልጋቸውን መጽሐፍት ግን በምንፈልገው ጊዜ አናገኝም፣ በዚህ በኩል መጠነኛ ችግር አለ፡፡ በተረፈ ደህና ነኝ፡፡ እኔ ተስፈኛ ነኝ፡፡ እናንተም በተሰማራችሁበት ዘርፍ የምትችሉትን ሁሉ ለሀገራችሁ ለውጥ መታገል አለባችሁ…››
ከሁለቱም ጋር የነበረንን የ30 ደቂቃ ቆይታ ሳንጠግብ ‹‹በቃችሁ›› የሚለው የፖሊስ ድምጽ ተሰማ፡፡ ‹‹እናመሰግናለን፣ በቃ ሂዱ›› ሲል አንዷለም በእርጋታ ተናግሮ በሽቦ ስር አሾልኮ እጆቻችንን ጨበጠን፡፡
እስክንድር ደግሞ ‹‹‹ሲመቻችሁ ብቻ መጥታችሁ ጠይቁን፣ ሥራ እንዳይበደል!፡፡ ሥራችሁን ሥሩ›› በማለት ለእኛም ያለውን አሳቢነት ከምክሩ ጋር ደጋግሞ ገለጸልን – ሁሉንም ሰላም በሉልኝ በማለት፡፡ እንግዲህ እስክንድርን የምትሉ ሁሉ ሰላምታውን በእኔ በኩል አድርሻለሁ፡

Saturday, June 14, 2014

ጦማርያኑ በፍርድ ቤት

Jailed blog9 bloggers in court

ለአብዛኛው ወጣት አዲስ አበባ ላይ ‹‹ቅዳሜ›› ትርጉም አላት፡፡ የሣምንቱን የሥራ ቀናት በየፈርጁ ያሳለፈው ኹሉም ወጣት ‹‹ቅዳሜ››ን ደግሞ እንደየ ምድቡ ይውልባታል፡፡ እንደሰማኹት ከኾነ ለዞን ዘጠኝ አባላትና ጓደኞቻቸውም ቅዳሜ ልዩ ቀን ናት፡፡ ለወጣቶቹ አብሮነት የጡመራ መድረኩ ቢያግዛቸውም ከዛ በላይ ግን ጓደኝነታቸው ቤተሰባዊነትን ፈጥሮላቸው አብዛኛውን ቅዳሜ እንደየ ቅርበታቸው አብረው ያሳልፋሉ፡፡
አብረው እስረኛ ይጠይቃሉ፣የታመመን ያጽናናሉ፣በጋራ ምሳ ይቋደሳሉ፣የተለየ ዝግጅት ካለም አብረው ይሳተፋሉ፡፡ ከዚህ የተረፈ ጊዜ ካላቸው ደግሞ ፈጣንንና ነጻ የገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት በሚገኝበት ሆቴል ገብተው ዓለም በምን ኹኔታ ላይ እንዳለች ለመከታተል ይሞክራሉ፡፡ አገሪቷ ውስጥ ባለው ከፍተኛ የኢንተርኔት ኮኔክሽን ችግር ምክንያት አብዛኛው ጋዜጠኛና ጥቂት ወጣቶች የእነዚህ ትልልቅ ሆቴሎች ገመድ አልባ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው፡፡ በቅዳሜ ወደእነዚህ ሆቴሎች ጎራ ያለ ከጦማሪያኑ ወይም ከጋዜጠኛ
Ethiopia bloggers in court
 አንድ ሰው ሊያገኝ ይችላል፡፡ በቃ ሲገናኙ ሰላም ተባብለው መቀላቀል ነው፡፡እናም በአንድ ጉዳይ ጨዋታ ጀመራል፡፡ አብዛኛው ጨዋታ በአገር ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሊኾን ይችላል፡፡ ኮምፒዩተሮቻቸውን እየነካኩ ስለ አገራቸው ግድ ያላቸውን ይነጋገራሉ፣ይከራከራሉ አሊያም ይጨቃጨቃሉ፡፡መሄጃው ሰዓት የደረሰበት ደግሞ ተሰናብቶ ይሄዳል፡፡በእነዚህ ሆቴሎች በቀጠሮ የሚገናኝ ሰው የለም፡፡‹‹የት ነህ? የት ነሽ?›› የሚለው የስልክ ጥያቄም ለመገናኘት በቂ ነው፡፡

የተስፋዓለም ቅዳሜ ደግሞ ሌላ ነበረች፡፡ሥራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ አብዛኛውን አርቦች ከእነ ለሊታቸው በሥራ ያጠፋቸዋል፡፡ቅዳሜንም ረፈድ አድርጎ ይነሳል፡፡ እናም የመጀመሪያ ሥራው ለሕትመት የበቁ ጋዜጣና መጽሔቶችን አበጥሮ ማንበብ ነው፡፡ በማንበብ ብቻም አያቆምም፤ ከዘገባዎቹ አብዛኖቹ የተሠሩት በጓደኞቹ አሊያም በሚያውቃቸው ጋዜጠኞች ስለሚኾን ስልክ ይደውላል፡፡ ከዘገባዎች ውስጥ ተስፋዓለምን የሚያስደስቱት በጣም ጥቂቶቹ ብቻ ሊኾኑ ስለሚችሉ የስልክ ልውውጦቹ ‹‹እንዲህ ብታደርግ/ብታደርጊ ኖሮ፣እንትናን ብታናግረው በዚህ ጉዳይ ላይ መረጃ ይሰጥህ ነበር፣እዚህ ቦታ እኮ እንዲህ ዓይነት መረጃ ነበር፣ይሄ እኮ ከዚህ በፊት እንዲህ ያለ ሕትመት ላይ ወጥቷል፣እውነቱን ለመናገር ይሄ ለሕትመት የሚበቃ ዘገባ ነው ብዬ አላምንም›› በሚሉ አስተያየቶች የተሞሉ
Jailed Ethiopian bloggers appeared in court
 ነበሩ፡፡ በዚያው ልክ ደግሞ የሚያስደስተውን ዘገባ ሲያነብ ወይም ፕሮግራም ሲሰማ አዘጋጁን አወቀው አላወቀው ስልክ አፈላልጎ በመደወል ያበረታታል፡፡ የተስፋዓለም ግማሽ ቅዳሜ የምታልቀው ይህን ሲያደርግ ነው፡፡

አኹን እነዚህ ወጣቶች ቅዳሜያቸውን በፌደራል ወንጀል ምርመራ መምሪያ (ማዕከላዊ) ፖሊስ ተነጥቀዋል፡፡ ሃምሳ ቀናት ታስረው ዘጠኝ ቅዳሜን አጥተዋል፡፡ እንዳሻቸው የሚያደርጓትን ቅዳሜ አኹን እነርሱ አያዙባትም፡፡ ከጠዋቱ ዐስራ ሁለት ሰዓት ሲል ከእንቅልፋቸው ይቀሰቀሳሉ፡፡ ለቁርስ ዳቦ በሻይ ይሰጣቸዋል፡፡ (ቤተሰብ የሚያወስድላቸው ምግብ ቁርስ ከበሉ በኋላ ነው የሚደርሳቸው) እናም ተመልሰው ገብተው ይዘጋባቸዋል፡፡አብዛኞቹ ለየብቻ ከሌሎች እስረኛ ጋር የታሰሩ ሲኾን ሁለት፣ ሁለት ተደርገው የታሰሩም አሉ፡፡እናም ከምርመራ የተረፈ ቀናቸውን በዝጉና በጨለምተኛው ክፍል ያሳልፋሉ፡፡ በአንዷ ቅዳሜ ደግሞ እንደዛሬው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡
አንዷን ቅዳሜ- በፍርድ ቤት
ሦስቱ ወጣቶቹ እነርሱ በማያዙባት ቅዳሜ እጆቻቸውን በካቴና ታስረው ፒያሳ በሚገኘው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ግቢ ውስጥ ሲደርሱ ከሌላው ጊዜ የበለጠ ቁጥር ያለው በዐይን ግምት ሦስት መቶ የሚደርስ ችሎት ተከታታይ በግቢ ውስጥ ተገኝቶ ነበር፡፡ የዛሬዎቹ ጠባቂ የፌደራል ፖሊሶች ባለፈው ጊዜ ከነበሩት ሻል ያሉ ስለነበሩ ቤተሰቦች ችሎት ውስጥ ገብተው እንዲታደሙ ባይፈቀድላቸውም ግቢ ውስጥ ከመቆም የከለከላቸው ወይም ያመናጨቃቸው አልነበረም፡፡ 
bloggers in court Addis Ababa, Ethiopia

ከጠዋቱ አራት ሰዓት ከሃያ ደቂቃ አካባቢ ሲኾን ችሎቱ በሴት ዳኛ በመሰየሙ፤ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎቹ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃነ እጃቸውን በሰንሰለት እንደታሰሩ ወደ ግቢው ገቡ፡፡ ዛሬ ወጣቶቹ በስስ ፈገግታ ‹‹አይዞአችሁ ደህና ነን›› የሚል የተስፋ ምልክት ለቤሰተቦቻቸውና ለጓደኞቻቸው አሳይተዋል፡፡ ከእነርሱ ቀጥለው በፖሊስ ታጅበው የገቡት ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስና የሕግ መምሕርና የዞን ዘጠኝ ጦማሪ ዘለዓለም ክብረት እጆቻቸው በካቴና እንደታሰረ ለቤተሰቦቻው ሰላምታን ሰጥተዋል፡፡ የእነርሱ ፈገግተኛ መኾን ለቤተሰቦቻቸው፣ለጓደኞቻቸውና ለወዳጆቻቸው ጥቂትም ቢኾን እፎይታን ሰጥቷል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ችሎት የቀረቡት እንደወትሮው ኹሉ በሁለት መዝገብ ተከፍለው ቢኾንም ፖሊስ ያቀረበው ምክንያትና መከራከሪያ አንድ ዓይነት ነበር፡፡ ችሎቱ ከተሰየመ በኋላ ፖሊስ በተሰጠው ጊዜ ቀጠሮ በርካታ ጉዳዮችን ሲመረምር መቆየቱንና አሁንም ያልተጠናቀቀ ምርመራ ስለሚቀረው ተጨማሪ ሃያ ስምንት ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡
ጠበቃው አቶ አመሐ፤‹‹ፖሊስ ከዚህ ቀደም በወሰደው ጊዜ ቀጠሮ ሰንድ ለማስተርጎም፣ የምስክሮችን ቃል ለመቀበል፣ኢሜሎቻቸውን ለመፈተሽ እንዲሁም ያልተያዙ
Ethiopian Jailed bloggers
 ግብረአበሮቻቸውን ለመያዝ ብሎ እንደነበርና አሁን ዝም ብሎ በጥቅሉ በርካታ ሥራዎችን ሠርቼያለሁ እንደገና ይጨመርልኝ ማለቱ አግባብ አይደለም›› ሲሉ አመልክተው ነበር፡፡ ዳኛው ፖሊስ የሠራውን ሥራና የሚቀረውን ምርምራ እንዲያስረዳ በማዘዛቸው፣‹‹ከሠራናቸው በርካታ የምርመራ ሥራዎች መካከል የተባባሪዎቻቸውን ቤት ፈትሸናል፣ለተለያዩ ባንኮች የተጠርጣሪዎቹን ዝርዝር መረጃ እንዲሰጡን ጠይቀን ከተወሰኑት ምላሽ አግኝተናል፣የተወሱ ምስክሮችንን ቃል ተቀብለናል፣ ከትርጉም ሥራውም የተወሰነውን ሠርተናል፡፡ ግብረአበሮቻቸው ወደ ክፍለ ሃገርና ወደ ተለያዩ አገራት እየሸሹ መያዝ ስለተቸገርን የፖሊስ ኃይል አሰማርተን እያፈለግናቸው ነው እነርሱንም መያዝ ይቀረናል፡፡›› በማለት ተናግሯል፡፡

አቶ አመሐ በበኩላቸው፤‹‹ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ካዋለ ሃምሳ ቀናት ሞልቶታል፡፡ እነዚህ የሚላቸውን ነገሮች አጠናቆ ለመጨረስ የነበረው ጊዜ ከበቂ በላይ ነው፡፡አሁንም ቢኾን እነዚህን ምርመራዎች ለማድረግ የደንበኞቼን አስሮ ማስቀመጥ አስፈላጊ አይደለም ስለዚህም ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብቻውን ሊያከብርላቸው ይገባል፡፡ ይህን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ባይቀበለው እንኳን ከዚህ በኋላ ፖሊስ በሚሰጠው ሃያ ስምንት ቀናት ጊዜ ውስጥ ምርመራውን አጠናቆ እንዲመጣ፤አጠናቆ ባይመጣ ደግሞ ጥያቄው ተቀባይነት እንደማይኖረው ተደርጎ ይመዝገብልን›› በማለት ጠይቀዋል፡፡
ዳኛዋ አቤቱታውን ካደመጡ በኋላ፤ፖሊስ ከዚህ በኋላ ሲቀርብ ለተጨማሪ የምርመራ ቀነ ቀጠሮ መጠየቂያ አሁን የጠቀሳቸውን ምክንያቶች በምክንያትነት ይዞ እንዳይቀርብ በማሳሰብ የጠየቀውን የሃያ ስምንት ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ፈቅደዋል፡፡
zone9 bloggers in court
በዛሬው ዕለት ችሎት ከቀረቡት መካከል ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ ፤ከፍተኛ የኾነ የጀርባ ሕመም ስላለበት ወንበር እንዲገባለት መጠየቁንና እስካኹን ሊገባለት እንዳልቻለ ጠቅሶ ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እንዲሰጥለት አመልክቷል፡፡ ዳኛዋ ከምንም ነገር በላይ የጤና ጉዳይ ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ በማሳሰብ የጠየቀው ወንበር እንዲገባለት ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በችሎት የተገኘው መርማሪ ፖሊስ፤‹‹በአጋጣሚ የእርሱ መርማሪ እኔ ነኝ የጀርባ ሕመም እንዳለበት ነግሮኛል፡፡ ወንበር እንዲገባለት ግን አልጠየቀኝም፡፡ አሁን ቢኾን ይህ በጣም ቀላልና እዛው እኛው ጋር ሊያልቅ የሚችል ነገር ነው፡፡ ችግር የለም እናስገባለታለን›› ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡
እስረኞቹ ከችሎት ሲወጡ እንደ አገባባቸው በፈገግታ ሰላምታ እየሰጡ ሲኾን ችሎቱን ለመከታተል መጥቶ ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ ቆመው ሰውም እጁን በማውለብለብ ተሰናብቷቸዋል፡፡


ጽዮን ግርማ
tsiongir@gmail.com

Friday, June 13, 2014

የወያኔ ግፍ ለከቱን አልፏል!

የወያኔ ጉጅሌ ራሱ ከሳሽ፣ ፖሊስና ዳኛ ሆኖ በሚገዛት ሀገራችን ውስጥ የሚያካሂደው ግፍ አንድ ህዝብ ሊሸከመው ለሚችለው በላይ ሆኗል።

የወያኔ ሹማምንትና በዘር ለዝርፊያ የተሰማራው ድርጅታቸው በቅርቡ ደግሞ ስዘርፍ አያችሁኝ በሚል ቁጣ ከአንደበታቸው በላይ ምንም ባልታጠቁ የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ ከአካሄደው ጅምላ ጭፍጨፋ አልፎ ግለሰብ ተማሪዎችን በማሳደድ ሰቆቃ መፈጸሙን ቀጥሎበታል። በዚህ ሰአት በርካታ ተማሪዎች በታወቁና ባልታወቁ እስር ቤቶች ታጉረዋል። ብዙዎቹ ከትምህርት ገበታ ካላንዳች ጥያቄ ተባረዋል እየተባረሩም ይገኛሉ።
ከወያኔ ግፎች ሁሉ በእጅጉ የሚዘገንነው ሌሎችን በመወንጀል ማሰቃየትና መግደል በፈለገ ቁጥር ራሱ ወንጀል ከፈጸመ በኋላ ወንጀሉን በሌሎች ላይ ለማመኻኘትና ለመቅጣት የሚጠቀሙበት የሃሳብ ዘዴ ነው።
በአለምያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በተሰበሰቡበት አዳራሽ ውስጥ የደህንነት አባሎች ቦንብ አፈንድተው ጉዳት ካደረሱ በኋላ የሚፈልጓቸውን ወጣቶች ቦንብ ሲያፈነዱና ሲጠምዱ ያዝናቸው በማለት ከዚህ በፊት በዊክሊክ መረጃ እንደተለቀቀው የተለመደ በሰው ልጆች ላይ ሰቆቃ ይፈጽማሉ። ሌላው ቀርቶ ቦምብ አፈነዱ ተብለው የተከሰሱት ተማሪዎች በገዛ ጓደኞቻቸው ላይ ቦምብን የሚወረውሩበት ምክንያት የላቸውም።
ወያኔ ተማሪዎቹን አረመኔና እብድ ለማስመሰል የሰራው የራሱ ትንሽዪ ድራማ ወይም ሌላኛው አኬልዳማ መሆኑ ግልጽ ነው።
ወያኔ ደግሞ እንዲህ አይነት የወሮበላ ስራ እንደሚሰራ እንዳላዪ የሚያዩት ለጋሽ ሀገሮች ሁሉ ያጋለጡት፣ የሚያውቁት የአደባባይ ሚስጥር ከሆነ ሰንብቷል።
በዚህ መሰሪ ወንጀል ያዝናቸው ብለው ከአሰሯቸው ተማሪዎች ውስጥ የቦኮ ትቤ ተወላጅ የሆነ ኑረዲን ሃሰን የተባለ የአለመያ ዩኒቨርስቲ ተማሪ በድብደባ አሰቃይተው ከገደሉት በኋላ ራሱን ገደለ ብለው አስክሬኑን ለቤተሰቦቹ ሸጠውታል፡፡ በአሁኑ ወቅት ብዙ ተማሪዎች የደረሱበት እና የገቡበት ተፍጧል።
ይህ ሰቆቃ መጠኑን አልፏል! ግፍ በዚሁ እንዲቀጥል ከሆነ ደግሞ መቆም የሚችልበት ተግባር ባለመፈጸማችን ሁላችንም የዚያች ሀገር ልጆች ከታሪክ ወቀሳ እና ከህሊና ጸጸት አናመልጥም። ወያኔዎች በዘር ከፋፍለው በየተራ ስለሚያጠቁን ነው ይህ የሽብር አገዛዛቸው እድሜ ያገኘው። ይህን አደገኛ ክፍተት ካልዘጋነው መከራው ቀጥሎ ያሰቃየናል።
ግንቦት 7 የፍትህና የዴሞክራሲ ንቅናቄ አገራችን ይህን ሁሉ ግፍና መከራ ማስተናገድ እንዲበቃት ልጆቿ ተባብረን እንድንነሳ ደጋግሞ ጥሪውን ያቀርባል።
ለወያኔ የተመቸነው በየተራ ለመጠቃት አንዱን ብሄረሰብ በሌላው በማስፈራራትና ጥርጣሬ በመንዛት ለመግዛት የቀየሰው ዘዴ ሰለባ መሆናችን ነው።
ግንቦት 7 ንቅናቄ፤ የወያኔ የግፍ ቀንበር እንዲሰበር ሰፊ ህብረት ፈጥረን ከመታገል ውጪ አማራጪ የለንም ይላል።
የወያኔ ግፍ ይብቃ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Tuesday, June 10, 2014

በምርጫ 97 በግፍ ለተገደሉ ወገኖቻችን መታሰቢያ በኦስሎ ከተማ የሻማ ማብራት ስነስርአት ተካሄደ


በምርጫ 97 በወያኔ አጋዚ ጦር በግፍ ለተገደሉ ዜጎቻችንን ለማስታወስ   በጁን 8, 2014 በኦስሎ ከተማ የሻማ ማብራት ስነስርአት ተደረገ ። የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ይህንን የሻማ ማብራት ያዘጋጀበት ዋናው አላማ በምርጫ 97 የዲሞክራሲ ጥያቄ ባነሱና ድምፃችን ተሰርቋል ድምፃችንን መልሱልን ያሉ ንጹሀን ዜጎቻችን የተገደሉበት እለት በመሆኑ ለሞቱት ወገኖቻችን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ነው።


ዝግጅቱ በግፍ በወያኔ ታጣቂዎች ደረትና ግንባራቸውን ተብለው የተገደሉ ንፁሃን ወገኖቻችን በማስብ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ የተጀመረ ሲሆን በመቀጠልም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ምክትል ሊቀመንበር ምርጫ 97ትን አስመልክቶ ሰፋ ያለ የመግቢያ ንግግር አድርገዋል እደዚሁም የኢትዮጵያ ማህበር በኖርዌ ሊቀመንበርም አጠር ያለ መልክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶችም በምርጫ 97 ወቅት የነበረውን የግፍ ግድያ አስመልክቶ በየተራ መልክቶቻቸውን አስተላልፈዋል። በተጨማሪም ድርጅቱ በምርጫ 97 በግፍ ህይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችንን ለማስታወስ አጭር በፊልም የተደገፈ ምስል በስነስርአቱ ላይ ቀርቧል። በዝግጅቱ ላይ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ አባላትና ሌሎችም ኢትዮጵያዊያን ተገኝተዋል። ዝግጅቱ በኖርዌጅያን የሰአት አቆጣጠር ከምሽቱ 19፡00 ተጀምሮ 20፡30 ተጠናቋል።


ምርጫ 97ትን ሁላችንም ስናስታውስ ገዢው ፓርቲ እድሜያቸው ትንንሽ የሆኑ ልጆችን በአልሞ ተኳሾች  ግንባርና ደረታቸው ብሎ ካስገደለ በኋላ የሰጠን ምላሽ ዘራፊዎች ናቸው ባንክ ለመዝረፍ ሲሞክሩ ተገደሉ ይለናል የሞቱት ህፃናት እንኳን ባንክ የመዝረፍ እውቀትና አቅም ሊኖራቸው ቀርቶ ስለባንክ ቢጠየቁ ብዙም እውቀቱ የሌላቸው ህፃናት ነበሩ። ወያኔ እስከአሁንም ድረስ ንፁሃን ዜጎቻችንን በግፍ ከገደሉት ሎሌዎቹ አንዳቸውንም ለፍርድ ለማቅረብ ምንም አይነት ሙከራ አለማድረጉ ይታወቃል። ሐገራችን የወያኔ አድርባይ ግፈኞችና ወንጀለኞች የማይጠየቁባት እንደፈለጉ ወንጀል የሚሰሩባት በአንፃሩ ምንም ወንጀል ያልሰሩ ለሃገራችን ያገባናል የሚሉ ዜጎች ያለምንም ማስረጃ በተዛባ የፍርድ ሂደት በእስር የሚማቅቁባት የወንበዴዎች ሐገር ሆናለች። እነኚህን በምርጫ 97 የተገደሉ ወገኖቻችንን ሁሌም እንዘክራቸዋለን እናስታውሳቸዋለን ሆኖም ግን ሁሌ በየአመቱ ሻማ በማብራት ብቻ ሳይሆን ገዳዮቻቸውን ለፍርድ ለማቅረብም መስራት አለብን። በአጠቃላይ በሃገራችን የህግ የበላይነት እንዲኖርና ሁሉም ሰው በሃገሩ ያለምንም የዘር መድልኦ በነፃነት የሚንቀሳቀስበት ስርአት ለመፍጠር ይህ ስርአት መወገድ ስላለበት በዚህ ላይ ትኩረት አድርገን መታገል ይኖርብናል። ምክንያቱም ወያኔ በ97 ገደለ አሁንም እየገደለ ነው ዜጎች በየቀኑ ዛሬም እየሞቱ ነው ይህንን ሞት የምናቆመው ወያኔን ስናስወግድ ብቻ በመሆኑ ሁላችንም በመተባበር ሐገራችንን እንድናድን ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።

ኢትዮጵያ  በክብር ለዘላለም ትኑር  
ሄለን ንጉሴ

The moving message of Swedish journalist Martin Schibbye about Eskinder Nega


journalism_is_not_terrorism
WEF President Erik Bjerager told the ceremony that the world needs to watch the creeping threat of anti-terrorism legislation being used to target journalists. “Ethiopia continues to resort to anti-terrorism legislation to silence opposition and shackle the press. Alarmingly, beyond Ethiopia, countless states around the world are misusing anti-terrorism legislation to muzzle journalists, bloggers and freedom of expression advocates,” Bjerager said. “Research suggests that over half of the more than 200 journalists in jail last year were being held on ‘anti-state’ charges. Let me be clear: Journalism is not terrorism. Politicians should not abuse the notion of national security to protect the government, powerful interests or particular ideologies, or to prevent the exposure of wrongdoing or incompetence.”

Thursday, June 5, 2014

ጅቡቲን ውሃ ጠማት አለ /TPLF/

ሔለን ንጉሴ/ከኖርዌ

ገዢው ፓርቲ ወያኔ ጅቡቲን ውሃ ጠማት እሷን ከሚጠማት እኛን ይጥማን በሚል ይመስላል ጅቡቲ የኢትዮጵያ ድንበር አቋርጣ ሐገር ውስጥ ድረስ ገብታ ከድሬደዋ ሰባት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሽንሌ የከርሰምድር ንፁህ ውሃ በነፃ አውጥታ እንድትጠጣ መሬት ለመስጠት የሚያስችል ረቂቅ ወጥቶ በምክር ቤት ለውይይት የቀረበ መሆኑ ተሰማ። የራስዋ ሲያርባት የሰው ታማስላለች ይላሉ ይሄ ነው! ህዝባችን መቼ ውሃ ጠጣና ነው ለጎረቤት ማሰብ የተጀመረው ምላሹን ለራሳችን እንተወውና

በሐገራችን ቁጥር አንድ ችግር የውሃ እጥረት መሆኑ እየታወቀ ህዝብ በውሃ እጥረት ምክንያት ከፍተኛ ችግር ውስጥ መውደቁንና ውሃ በመሃል አዲስ አበባ ከተማ ሳይቀር በመጥፋቱ ዜጎች ውሃ ፍለጋ ከሰፈር ሰፈር እየተንከራተቱ መሆኑንና ህዝባችን በውሃ ችግር እየተሰቃየ እያለ ይህንን ችግር መፍታት አቅቷቸው ጅቡቲን ውሃ ጠማት የጅቡቲ ህዝብ የንፁህ ውሃ መጠጥ ያስፈልገዋል ብለው በምክር ቤት ውይይት መጀመራቸው እጅግ በጣም ያስገርማል። ወያኔ መሬት ቆርሶ ለጅቡቲ ውሃ ትጠጣ ብሎ ለሰላሳ አመታት የሚቆይ ኮንትራት ፈርሞ እንደሚሰጥ የቀረበው እረቂቅ የሚገልፅ ቢሆንም በአንፃሩ ኢትዮጵያ ይህንን መሬት በመስጠቷ በምትኩ የምታገኘው ጥቅም እንዳለ ቢጠየቅም ምላሹ የፓለቲካ ጥቅም እንዳለው ብቻ ከመናገር ውጪ ዝርዝሩን ለምክር ቤቱ ማስረዳት አልቻሉም። ጅቡቲ ይህንን መሬት ከኢትዮጵያ ለሰላሳ አመት ኮንትራት ወስዳ ህዝቦችዋን ንፁህ ውሃ ስታጠጣ ጅቡቲን ውሃ ለማጠጣት ከስፍራው የሚፈናቀሉ ዜጎቻችንስ እጣ ፋንታ ምን ሊሆን እንደሚችል ሁላችንም መገመት እንችላለን በየቦታው በልማት ሰበብ ከተፈናቀሉት ካለፉት ተፈናቃዮች ተሞክሮ አለንና በከፍተኛ ሁኔታ ሊታሰብበት ይገባል።

  
ጅቡቲ እንደሚታወው ከወደብ ኪራይ ከኢትዮጵያ በአመት አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር እንደምታገኝ ይታወቃል። ከዚህ በተጨማሪም በሐገራችን በከተሞች ሳይቀር የመብራት እጥረት  በከፍተኛ ሁኔት እየታየ ባለበት ሁኔታ ጅቡቲ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ታገኛለች። ኢትዮጵያ ከጅቡቲ የምታገኘው ምንም አይነት ጥቅም ሳይኖር ለምን የጅቡቲ ጉዳይ እንዲህ እንዳሳሰባትና ወያኔ በዚህ ዙሪያ ያለው ድብቅ የፓለቲካ አጀንዳ ምን እንደሆነ በግልፅ ባያሳውቀንም መገመት ግን እንችላለን። በሌላ መልኩ ወያኔ በማንአለብኝነት ሐገሪቷን እየሸነሸነ መሸጡን መቀጠሉን እያሳየን ነው ትላንት 17 ቀበሌዎችን ለሱዳን አሳልፎ በመስጠቱ የተፈናቀሉ ዜጎች ምን ያህል እንደተቸገሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ሆኖ ሳለ ዛሬ ደግሞ ጅቡቲ ሐገራችን ገብታ ውሃ እንድትጠጣ መሬት ተሰጣት ነገስ ማን ይሆን ባለተራው!!

ለማንኛውም ወያኔ ሐገሪቱን ሸንሽኖ ከመጨረሱ በፊት ሁላችንም ልናስብበት ይገባል ሐገር የማዳን ስራ መስራት ያለብን ወሳኝ ጊዜ ላይ እንገኛለን በመሆኑም እኛ ውሃ እየጠማን ለጅቡቲ ውሃ አንሰጥም ብለን ተቃውሟችንን ማሰማት መቻል አለብን ከሀገር ይልቅ ስለሌሎች የሚቆረቆር ወራሪ በመሆኑ ይህን ብልሹ አስተዳደር ተባብረን ከሐገራችን ማባረር መቻል አለብን እላለሁ።

ኢትዮጵያ ሐገራችንን እግዚአብሄር ይባርክልን

Ethiopia arrests 25 in 'terror' sweep

By AFP
Addis Ababa (AFP) - Ethiopian police arrested 25 people accused of plotting attacks in the country and suspected of having links to Somalia's Al-Qaeda-linked Shebab rebels, officials said Thursday.
Government spokesman Shimeles Kemal told AFP that those detained had been trained by the militants in Somalia and were planning a series of attacks in Jimma, about 305 kilometres (189 miles) southwest of the Ethiopian capital and where the arrests were made.
"About 25 people have been apprehended on suspicion of organising an underground terrorist cell," he said, adding that "a number of weapons" were also seized and the suspects likely to be charged.
Ethiopia, which shares a 1,600 kilometre border with Somalia, sent troops into the country in 2011 to help African Union and Somali defence forces fight the Shebab. It currently has around 4,500 troops in the country and has spearheaded a recent offensive against the Islamists.
Neighbouring Kenya has been a frequent target of attacks by Shebab rebels, who have demanded that Kenyan troops leave Somalia and claimed responsibility for last year's attack on the Westgate shopping mall in Nairobi that left at least 67 dead.
Uganda and Djibouti, both contributors to the AU force in Somalia, have also been attacked by the Shebab.
The US and British embassies have upgraded their travel warnings for Ethiopia in recent weeks, alerting visitors and residents to an increased threat of attacks.
Shimeles said while Ethiopia "has been and will remain vulnerable to terrorist attacks," the threat has not necessarily increased.
"I don't think that there is a special risk that warrants an extraordinary alert," he said.
Shebab leaders have vowed to attack Ethiopia to avenge the presence of its troops in Somalia, and last October two Somali nationals blew themselves up while crafting a bomb in Addis Ababa, which police said they planned to detonate at a crowded football match.

ኢ- ፍትሃዊው እስሬ! እየፈሩ ጋዜጠኝነት የለም! (ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ጎዳና )


June 5, 2014
Elias Gibru

(ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታችን ትልቅ አደጋ ላይ ነው)

አርብ ግንቦት 15 ቀን 2006 ዓ.ም ከወዳጄ ጋዜጠኛ ዳዊት ሠለሞን ጋር ቀጠሮ ነበረኝ፡፡ ረፋድ 5፡25 ሰዓት ላይ የሞባይል ስልኬ ጠራች፡፡ ከአምባሳደር ወደአራት ኪሎ በሚጓዝ ታክሲ ውስጥ ተሳፍሬ ነበር፡፡ የመስመር (የቢሮ) ስልክ መሆኑን አየሁትና “ሃሎ” አልኩኝ፡፡ ‹‹አቶ ኤልያስ፣ የዕንቁ መጽሔት ዋና አዘጋጅ?›› የሚል የሴት ድምጽ ተሰማኝ፡፡ ‹‹አዎን›› ስል መለስኩላት፡፡ ብዙ ጊዜ አንባቢዎች ስለሚደውሉ፣ ምን ዓይነት ግብረ-መልስ (feed back) ይኖራት ይሆን ነበር ሀሳቤ፡፡ ሳይሆን ቀረ፡፡ ‹‹የምደውለው ከፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ነው፣ በአንድ ጉዳይ ላይ ስለምንፈልግዎት ቃልዎትን መጥተው እንዲሰጡን ነበር፡፡›› …‹‹እሺ፣ ሰኞ ጥዋት ልምጣ?›› በማለት ጠየኳት፡፡ ‹‹ቆይ አንዴ?›› ብላኝ ባልደረቦቿን ካነጋገረች በኋላ ‹‹ይቻላል›› አለችኝ፡፡ ቀጭን የጌታ ትዕዛዝ፡፡ ከዚህ የስልክ ጥሪ በኋላ የመጽሔቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ማኅተመወርቅ (ፍቄ) ደውሎልኝ ስለጉዳዩ ሐሳብ ተለዋወጥን፡፡ ሰኞ በጥዋት ለመገናኘት ተቀጣጥረን ስልኩ ተዘጋ፡፡
ለምርመራ መጠራቴ በኢትዮጵያ የነጻ ፕሬስ ሕይወት ውስጥ የሚያጋጥም፣ የተለመደ ጉዳይ በመሆኑ ብዙ አልተገረምኩኝም፡፡ በቀድሞ አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ እሰራ በነበረበት ወቅት አሸባሪ ተብሎ በፓርላማ በተሰየመው የ‹‹ግንቦት 7›› የፖለቲካ ድርጅት አመራሮች እና በአገር ውስጥ በነበሩ ከፍተኛ ጄኖራሎች፣ የመከላካለያ ሰራዊት አባላትና ሌሎች ዜጎች ላይ ከባድ ክስ ቀርቦ ነበር፡፡ የፍርድ ሂደቱን ተከታትዬ የምዘግበው እኔ ነበረኩ፡፡ እኔ ከሰራሁት ዘገባ ጋር በተያያዘ አቃቤ ሕግ ክስ አቅርቦ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ከባልደረባዬ ጋዜጠኛ ፍጹም ማሞ (ዋና አዘጋጅ የነበረ) ተጠርተን ቃል በመስጠት በ5000 ሺህ ብር ከወጣን በኋላ ፍርድ ቤት ቀርበን ነበር፡፡ ፍ/ቤቱም ክሱን ተመልክቶ ለእኔ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የሰጠኝ አጋጣሚ ስለነበረ ጉዳዩን አስታውሼ በአዕምሮዬ ለአፍታም ቢሆን ማሰላሰሌ አልቀረም ነበር፡፡
ሰኞ ግንቦት18 ቀን 2006 ዓ.ም ጥዋት ከባልደረባዬ ፍቃዱ ጋር ቀጠሮ ስለነበረን ወደ ቢሮ አመራሁ፡፡ በአጋጣሚ ፍቃዱ ያለወትሮው ቢሮ አልነበረም፡፡ ስልኩ ይጠራል፣ ግን አይነሳም፡፡ ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ገደማ ፍቃዱ ደወለልኝ፡፡ ሞባይል ስልኩን ያላነሳው ጓደኛው ቤት ረስቶት በመውጣቱ ምክንያት መሆኑን ነገረኝ፡፡ ከሰዓት የተጠራሁበት ቦታ ለመሄድ በድጋሚ ተቀጣጠርን፡፡ ከሰዓት በኋላ ጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ እና ነብዩ ሐይሉ ተቀላቅለውን አራት ሆነን ወደማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ሄድን፡፡
ምርመራ ቢሮ ቁጥር – 76
እኔ እና ፍቃዱ ተፈትሸን እና ሞባይላችንን ጥበቃ ጋር አድርገን ወደቢሮ ቁጥር 76 አቀናን፡፡ እኔ አንኳኩቼ ወደ ቢሮዋ ገባሁ፡፡ ፍቃዱ ውጭ ቁጭ አለ፡፡ አንድ ወንድ እና ሴት የመ/ቤቱ ባልደረቦች ቢሮ ውስጥ ነበሩ፡፡ ከየት እንደመጣሁ ነገርኳቸው፡፡ ‹‹ቁጭ በል›› ተባልኩ፡፡ ‹‹ጥዋት ነበር እመጣለሁ እኮ ያልከው?›› ብሎ ወንዱ ፖሊስ ሀሳቡን ሰነዘረ፡፡ ‹‹አዎን›› ካልኩት በኋላ ጠዋት ያልመጣሁት በሁኔታዎች አለመመቻቸት መሆኑን አስረዳሁት፡፡ በምን ጉዳይ ልጠራ እንደቻልኩ መረጃው ካለኝ እንድነግረው ፈገግ እያለ ወዲያው እኔኑ ጠየቀኝ፡፡ መረጃው እንደሌለኝ ነገርኩት፡፡ አንድ የክስ መዝገብ ሲገልጥ የመጽሔታችንን ቁጥር 113ኛ ዕትም አየኋት፡፡ በመጽሔቱ ፊት ገጽ ላይ ‹‹በቃን! የጠባብ ብሔርተኝነት ዘመቻ›› በሚል ትልቅ ርዕስ ሥር የቀድሞ ጠ/ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ፣ የቀድሞ ም/ ጠ/ሚንስትር አቶ ታምራት ላይኔ፣ የኤርትራ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ፣ የኦነግ መስራች አቶ ሌንጮ ለታ፣ የቀድሞ ም/ ጠ/ሚንስትር እና የብአዴን ሊቀመንበር አቶ አዲሱ ለገሰ፣ የቀድሞ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር እና የብአዴን ሊቀመንበር አቶ ተፈራ ዋልዋና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን ፎቶግራፎች አለ፡፡ ይህ ጽሁፍ መጽሔቷ ዝግጅት ክፍል የተሰራ እና ከወራቶች በፊት አቶ አለምነው መኮንን የአማራን ሕዝብ ጸያፍ ስድቦች መሳደባቸውን ተከትሎ መሰል ድርጊቶች ሥርዓቱ ሥልጣን ከያዘ ጀምሮ በተለያዩ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት፣ በኤርትራው ፕሬዚዳንት እና በቀድሞ የኦነግ መስራች መደረጋቸውን በማስታወስ ጠባብ ብሄርተኝነትን የሚቃወም እና ለችግሩ መፍትሄ ጠቋሚ ጽሁፍ ነበር፡፡
በዚያን ዕለት ለፖሊስ ቃሌን እንድሰጥ የተጠራሁትም በዚሁ ጽሑፍ መስሎኝ ነበር፡፡ መርማሪ መሆን አለመሆኑን ያላረጋገጥኩት እያነጋገረኝ ያለው ወጣት ግን የተጠራሁት በቅርቡ በኦሮሚያ ክልሎች በተነሳው ግጭት እና ብጥብጥ ጋር በመሆኑ ላይ ጥቁምታ ሰጠኝ፡፡ በአጋጣሚ በእጅ ላይ ሁለት የዕንቁ መጽሔት ዕትሞችን ይዜ ገብቼ ነበር፡፡ ወጣቱ ልጅ ‹‹አንዴ ልመልከታቸው?›› ብሎኝ ግንቦት 20 በተመለከተ ባለፈው ቅዳሜ የወጣውን የመጽሔቱን ዕትም ሰጥቼው እያገላበጠ ተመለከታቸው፡፡ ከሌላ ክፍል የመጣ አንድ መርማሪም ክስ ያቀረበብኝን ዕትም ከፋይሉ ውስጥ ነጥሎ በመውሰድ የሆነ ጽሑፍን በተመስጦ አንብቦ ክፍሉን ለቅቆ ወጣ፡፡
ወጣቱ ልጅ፣ ‹‹ያው ጥዋት እመጣለሁ ብለህ እኛም ስንጠብቅህ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ እኛ በተራችን እናስጠብቅሃለን፡፡›› አለኝ – ፈገግ እያለ፡፡ ፈገግታው ከልብ የመነጨ ነው ለማለት ግን እቸገራለሁ፡፡ ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ አንዲት ወፈር ያለች፣ የፖሊስ ማዕረግ ያለው የደንብ ልብስ የለበሰች ሴት ወዳለሁበት ክፍል መጣች፡፡ ‹‹ኤልያስ አንተ ነህ?›› አለችኝ፡፡
‹‹አዎን›› አልኳት፡፡
‹‹መጣሁ›› ብላኝ ከአፍታ ቆይታ በኋላ ተመልሳ በመምጣት እኔ የተቀመጥኩበት ወንበር ጋር ባለው ሰፋ ያለ ጠረጴዛ ትይዩ ተቀመጠች፡፡
‹‹ጥዋት ለምን አልመጣህም?›› የመጀመሪያ ጥያቄዋ ነበር፡፡
በአጋጣሚ በተፈጠረ ጉዳይ መምጣት አለመቻሌን አስረዳኋት፡፡ በዚህ ጊዜ ወጣቱ ልጅ አድራሻዬን፣ ዜግነቴን፣ የትውልድ ቦታዬን፣ የተማርኩባቸውን ትምህርት ቤቶች እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ የሰራሁባቸውን የሚዲያ ድርጅቶች፣ የትዳር ሁኔታ …እየጠየቀኝ ፎርም ላይ እየሞላ ነበር፡፡
‹‹ብሔርህስ?›› አለኝ፡፡ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› አልኩት፡፡
‹‹ያ’ማ ዜግነት ነው፣ መናገር አለብህ›› አለኝ፡፡ በግሌ የማልወደው ጥያቄ መሆኑን ነገርኩት፡፡ [የሰው ልጆች በሙሉ ምንጫችን አንድ ነው ብዬ አጥብቄ ስለማምን የዘር ጥያቄ ከልጅነቴ ጀምሮ የማይመቸኝ እና የማላምንበት የግል ጉዳይ ነው] ስለብሄር ሊያስረዳኝ ሞከረ፡፡ መታወቂያዬ ላይ የተጻፈውን ነገርኩት፡፡
ወ/ሮ በላይነሽ የተባለችው ምርማሪዬ ፋይሉን ተቀብላ እና በመጽሔቱ የተከሰስኩበትን ጉዳይ ነገረችኝ፡፡ በታሪክ አምድ ሥር ‹‹የተገነቡት እና በመገንባት ላይ ያሉት የመታሰቢያ ሐውልቶች የእነማን እና ለእነማንስ ናቸው?›› በሚል ርዕስ ሰዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን የተባለው ጸሐፊ በጻፈው ጽሑፍ ውስጥ የኦሮሞን ብሔር የሚያጥላላ፣ ዘርን ከዘር የሚያጋጭ፣ የኦሮሞ ሕዝብ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ የመጣ መሆኑን የሚጠቅስ፣ ለኢትዮጵያ እንግዳ ሕዝብ መሆኑን የሚናገር …ወዘተ በጣም ጥሩ ያልሆነ ጽሑፍ መሆኑን ነገረችኝ፡፡ አያይዛም ይህን ጽሑፍ ተከትሎ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ቁጣ መቀስቀሱን፣ ተማሪዎች ጽሑፉን የጻፈው ግለሰብ ለሕግ እንዲቀርብ ሁለት ጊዜ ያህል ለዩኒቨርሲቲው የሚመለከተው አካል በደብዳቤ ቢያሳውቁም መልስ ሳይሰጣቸው በመቅረቱ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣታቸውን፣ መስታወቶች መሰባበራቸውን፣ ንብረቶች መውደማቸው፣ በሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን፣ ሆስፒታል ገብተው በሞት እና በሕይወት መካከል ያሉ ተማሪዎች መኖራቸውን፣ የመማር ማስተማር ሒደት መስተጓጎሉን …ወዘተ ዘርዝራ አስረዳችኝ፡፡
እኔም እኛ (የመጽሔቱ አዘጋጆች እና ባልደረቦች) ኢትዮጵያን አንድ የሚያደርግ እንጂ ዘርን ከዘር የሚከፋፍል ሥራ አለለመስራታችንን፣ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 29 መሰረት ሕግን በማክበር ጽሑፎችን መጻፋችንን እና የተለያዩ ግለሰቦችን ሐሳቦች ማስተናገዳችንን፣ ይህንንም መመልከት እንደሚቻል ከጠቀስኩላት በኋላ የተባለው ጽሑፍ የመጽሔቱ ሳይሆን የግለሰቡ የግል ግለ-ሀሳብ መሆኑን አሰረግጬ ነግሬያት ነበር፡፡
መርማሪዬም ‹‹ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በሕገ-መንግሥቱ ተደንግጓል ብላችሁ የመጣላችሁን ጽሑፍ በሙሉ ታትማላችሁ ማለት ነው?›› በማለት ቆጣ በማለት ለመናገር ሞከረች፡፡ የመጡልን ጽሑፎች ሁሉ እንደማይታተሙ፣ እንደዋና አዘጋጅነቴ መስተካከል ወይም መታረም ያለባቸውን ጽሑፎች በአግባቡ እንደምመለከት፣ ሌሎች የመጽሔቱ አዘጋቾችም መሰል ሥራዎችን ተጋግዘን እንደምንሰራ ረጋ ብዬ አስረዳኋት፡፡
በክፍሉ ውስጥ ያሉት ሶስቱም የፌዴራል ፖሊስ ባልደረቦች በጽሑፉ ምክንያት የጠፋ ንብረት እና የአካል ጉዳት መኖሩን አጽንኦት በመስጠት ‹‹አጥፍታችኋል›› በሚል ተቆጥተው ሊናገሩኝ ሞከሩ፡፡ የእኔም ስሜት በተወሰነ ደረጃ መቀየር ጀመረ፡፡ እመን አትመን ክርክር ውስጥ ለአፍታም ቢሆን ገባን፡፡ ‹‹እነዚህ ሰዎች የፍርድ ቤትንም ሥራ ደርበው ይሰራሉ ወይ?›› ስል ታዘብኩ፡፡
ንግግሬን ቀጥያለሁ፡፡ በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተፈጠረ ለተባለው ነገር መጽሔታችን መነሻ መሆኑን ለመቀበል እንደምቸገር፣ መጋቢት ወር ላይ የወጣ ጽሁፍ አደረሰ የተባለውን ችግር ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት እዚህ ምርመራ ክፍል ውስጥ መሆኑን፣ በጽሑፉ የተቆጡ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለዝግጅት ክፍላችን አለመግለጻቸውን፣ ተማሪዎቹ ያቀረቡትን ቅሬታ ዩኒቨርስቲው መደበኛ በመሆነ መልኩ ለመጽሔታችን ዝግጅት ክፍል ምንም ነገር አለማቅረቡን፣ ቅሬታ ቀርቦ ቢሆን ኖሮ ተፈጠረ የተባለውን ችግር ለመፍታት እኛም የራሳችንን ሥራ መስራት እንችል እንደነበረ፣ ማስተባበያ ጽሁፍ ወይም ጽሑፉን የሚተች ሌላ ጽሑፍ ቢመጣ ኖሮ በተመሳሳይ ገጽ እና ይዘት እንደምናስተናግድ፣ ለዚህም ኃላፊነት እና ግዴታ እንዳለብን ተናገርኩ፡፡
በዚህም ብቻ አቆምኩም፣ በዚሁ መጽሔት ላይ የፖለቲካ አቀንቃኑ እና የኦሮሞ ጉዳዮች ዋነኛ ተማጋች መሆኑ የሚታወቀው ጃዋር መሐመድ የኦሮሞን ሕዝብ ጥያቄዎች ከነመፍትሄዎቹ በተመለከተ የሰጠንን ሰፊ ቃለ ምልልስ ማስተናገዳችንን፣ አቶ ኦባማ አንሰርሙ የተባሉ ጸሐፊም ስለኦሮሞ ሕዝብ ታሪክ ሰፊ ጽሁፍ አቅርበው በመጽሔታችን ላይ ማስተናገዳችንን ዋቢ በማድረግ አስረዳኋቸው፡፡ እኔም ብሆን በግሌ የትኛውም ዘር ከየትኛውም ዘር እንደማይበልጥ እና እንደማያንስ፣ የኦሮሞ ሕዝብ ረዥም ታሪክ ያለው ትልቅ ህዝብ መሆኑንና ከገዳ ሥርዓትም ዓለም ዴሞክራሲን እንደተማረ የግል ዕምነት እንዳለኝ ሀሳቤን ሰነዘርኩ፡፡
በቢሮው ውስጥ የፖሊስ ልብስ ለብሳ ኮምፒውተር ላይ ጽሑፍ በመተየብ ላይ ያለች አንዷ የተቋሙ ባልደረባ ጽሑፉ ግጭት ማስነሳቱን እና ጉዳት ማድረሱን ደጋግማ በመናገር ጥፋተኛ መሆናችንን ለመናገር ጥረት አድርጋ ነበር፡፡
እዚህ ጋር ለፖሊሷ ምሳሌ አነሳሁላት፣ አቶ መለስ ዜናዊ ‹‹የኢትዮጵያ ታሪክ የ100 ዓመት ነው›› ብለው ተናግረዋል በሚል በአንድ ወቅት መስማቴን በመጥቀስ ይህ የግላቸው ዕምነት መሆኑን፣ እኔ ደግሞ ኢትዮጵያ ከ3000 ዓመታት በላይ ታሪክ እንዳላት እንደማምን እና የሳቸውን ሀሳብ መቃወም ካለብኝ መስታወት በመስበር እና ብጥብት በማስነሳት ሳይሆን በሀሳብ ሞግት ብቻ መሆን እንዳለበት አስረዳኋት፡፡ ምሳሌዬ ባይወጥላትም ዝም አለች – ሌላም ምሳሌ አንስቼላት ነበር፡፡ አቶ መለስ ‹‹የአክሱም ሐውልት ለወላይታው ምኑ ነው›› ብለው ነበር፡፡ ስላት፡፡ ‹‹አዎን፣ ምኑ ነው›› ብላ በፈጥነት መለሰችልኝ፡፡ ግን ትሰማኛለች እንጂ አታዳምጠኝም፡፡ ምናልባት እርሷንም ያስከስሳት ይሆን ማድመጧ!
…ሰዓቱ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ሆነ፡፡ መርማሪዬ ወደቤቷ ለመሄድ የቸኮለች መሰለኝ፡፡ ቃሌን ለመስጠት በነጋታው ከእሷ ጋር ተቃጣጠርን፡፡ በዋስ መውጣት እንደማልችል አረዳችኝ፡፡ እኔም በክፍሉ ውስጥ ካደረግነው ንግግር እና ፊታቸውን በማንበብ ቀድሜ ተረድቼ ነበር፡፡ ባልደረባዬ ፍቃዱን አስጠራሁት፡፡ ዋስትና መከልከሌንም ነገርኩት፡፡ ለእናቴ ስለጉዳዩ ነግሮ እንዲያረጋጋት ስልኳን በወረቀት ላይ ጽፌ ሰጠሁት፡፡ የቤቴን ቁልፍ ለአናንያ ሶሪ እንዲሰጥልኝ ነግሬም ቻው ተባብለን ተሰናበትኩት፡፡ እንግዲህ እንዲህ ነው እስር፣ በስልክ ጠርቶ ቡና ከበጋበዝ ይቀላል – ለመንግሥታችን፡፡
…ይቀጥላል!